Quantcast
Channel: Amharic News – Medrek
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2265

ብአዴንና አለቃው ሕወሓት – ወንደሰን በየነ

$
0
0

ብአዴን ከተከታይነት ለመውጣት በሚሊተሪው፤ በሕዝብ ደህንነቱ እና በሃብት በሕገመንግስቱ መሰረት እንኳን የሚጋእትን አላገነችም ስለዚህ ገና በቅንፍ ውስጥ ናት የራሷን ሃሳብ ለማደረግ የሚያስችል አቅም የላትም። ገና ከተከታይነት አልወጣችም።

ብአዴንና አለቃው ሕወሓት
“የትግራይ ሕዝብም ሆነ የሕወሐት አባላት ማወቅ ያለባቸው የወልቃይት ጥያቄ የብአዴን ጥያቄ አይደለም” 
አዲሱ ለገሠ ከትግሬዎች የወይን መጽሔት ጋር ካደረገው ቃለ ምልልስ ። እዛው ጽሑፍ ላይ ብአዴን ውስጥ ችግር እንዳለና በአሁኑ ስዐት ሕብረተሰቡ ከብአዴን እንዳፈነገጠ ያትታል ።
ይህ እንግዲህ የምናየው ነገር በመሆኑ ክርክር አይኖረንም ። ከሰሞኑ አንድ ያላማረኝ ነገር እያስተዋልኩ ነው ። ብአዴንን አትንኩ ፤ ለብአዴን ጠበቃ እንቁም ዓይነት ነገር ። እንደኔ እንደኔ ብአዴን እንደ ድርጅት የዐማራ ሕዝብ ጠላት ነው ። በመካከለኛ አመራር ላይ ያሉ ዐማራዎች ቁጭቱ ቢኖርባቸውም ምንም ሲያደርጉ አላየንም ። ይህም በድርጅቱ ላይ ምንም ዓይነት ተጽዕኖ መፍጠር ስለማይችሉ ነው ። እንደ ድርጅት ስናወራ ደግሞ ድርጅቱ እንደ ድርጅት ከሚያደርገው አንጻር ነው ።
ለምሳሌ አያሌው ጎበዜ መሬት ለሱዳን ይሰጥ ብለህ ፈርም በተባለ ጊዜ መሬት ይሸጥ ብየ እንኳ አልፈርምም ነበር ያላቸው ። ይህንኑ ተከትሎ ብአዴን እንደ ድርጅት አቅም ስለሌለው አያሌው ጎበዜ ሲባረርና ደመቀ መኮንን ሲተካ መከራከር አልቻለም ።
እዚህ ላይ ሁለት ነገር እንይ ፦
በመጀመሪያ አያሌው ጎበዜ መሬት ይሰጥ ብየ አልፈርምም ቢልም በሌላ አቋሙ ላይ ብታዩት ከድሮው ዘመን እያነፃፀረ ዐማራን የምድር ገነት እንደፈጠሩለት አድርጎ ይቀባጥር ነበር ።
ሁለተኛው ነገር አያሌው ጎበዜ ይህን በማለቱ ለዐማራው አንድም ለውጥ አላመጣለትም (ድርጅቱ የማይረባ ስለሆነ ሊያግዘው አልቻለም) ።
ከሰሞኑ ንጉሥ ጥላሁን የተባለ ምንም ዓይነት ርሕራሔ እንዳታሳዩዎቸው በማለት ከቀባጠረ ዓመት ሳይሞላው ለገዱ ጥብቅና ቆመ ተብሎ ንጉሥ ጥላሁንን ትልቅ ነገር አድርጎ ማናፈስ ። አንድ ሰው ቀድሞ በነበረው ስራው እንወስነው እያልኩ አይደለም ። ነገር ግን ንጉሥ ጥላሁን ላይ ምንም ዓይነት አስተያየት ሳንሰጥ ማለፍ እንችላል ።
ገዱ ። የገዱም ነገር የተያያዘ ነው ። ገዱ ምንም እንኳን እንደሌሎቹ ባይቀባጥርም አሁንም ገዱ ብቻውን ወይንም አንዳንድ ሰዎች በድርጅቱ ውሳኔ ላይ ተፅዕኖ መፍጠር እስካልቻሉ ድረስ ብአዴንን ጠነከረ ሊያስብሉት አይችሉም ። አንዳንድ ሰዎች እንደግለሰብ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ በግለሰብ ደረጃ ያላቸውን ሕዝባዊነት እንጅ ያሚያሳየው ድርጅቱን ሊወክል አይችልም ። ድርጅቱን ሊወክል የሚችለው የእነርሱ ሐሳብ በድርጅቱ ላይ ሲንፀባረቅ ብቻ ነው ። ገዱ ትግሬ ባሕርዳር ላይ ዐማራን ሲገድል ከስልጣን አንሱኝ ብሎ ነበር ያለቀሰው ። ምክኒያቱም ምንም ማድረግ ስላልቻለ ። ገዱ ነገ ሊገሉት ይችላሉ ፤ ሊያስሩት ይችላሉ ድርጅቱ ምንም ሊያስጥለው አይችልም ።
አንዳንዶቻችን በውስጥ መስመር በምንገናኛቸው የብአዴን ልጆች ይመስለኛል ድርጅቱን የምናይበት መነፀር ። ይህ ስሕተት ነው ። ብአዴን ውስጥ ያለው አብዛኛው ዐማራ ለዐማራነቱ እንደሚያደላ ግልፅ ቢሆንም አመራሩን እንደገና ማዋቀር እስካልቻለ ድረስ የድርጅቱን ቅርፅ ሊቀይረው አይችልም ። አሁን ባሉበት ሁኔታ ይህን ነገር ማድረግ ይችላሉ ? አይችሉም !! ከቻሉም ደግየ ።

The post ብአዴንና አለቃው ሕወሓት – ወንደሰን በየነ appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2265

Trending Articles