Quantcast
Channel: Amharic News – Medrek
Viewing all 2265 articles
Browse latest View live

አደገኛውና ታክቲክ አልባው ድርድር – ሚኒሊክ ሳልሳዊ

$
0
0

የፓርቲ አመራሮቹ በእስር እንዲቆዩላቸው የሚፈልጉ የፓርቲ ኣባሎቻቸው እንዳሉ ለወያኔ ራሳቸው ከሰጡት መረጃ ለማወቅ ተችሏል

የሕዝብ ውክልና ያሌላቸው የፖለቲካ ድርጅቶች ከባለጠበንጃው ወያኔ ጋር የሚያደርጉት ድርድር ይሁን ውይይት ይባል ክርክር የስልጣን ጥመኝነታቸውን እንጂ የችግሮች መፍቻ ቁልፍ አለመሆናቸው ይታወቃል፤ ወያኔ ኣፏጭቶ የጠራቸው በሙሉ ፓርቲ ነን የሚሉ ሁሉ ባለፉት አመታቶች ዛሬና ነገን ጨምሮ ምንም ለውጥ ያሌላቸው ከወያኔ ጋር ሲሞዳሞዱ የኖሩ ፣በወያኔ ድጎማ የሚንቀሳቀሱ ፣ የውስጥ ችግሮቻቸውን ያልፈቱ ፣ጠንካራ አባሎቻቸውን አሳልፈው ለእስር የዳረጉ ፣ በሕዝብ ዘንድ ደረጃቸው የወረዳ የማይፈለጉ ሲልም የማይታወቁ ተለጣፊ አደርባይና አስመሳይ ተቃዋሚዎች ናቸው።

ወያኔ ደግሞ ስለ ድርድር ያውራ እንጂ በፍጹም መተርጎም የማ ይችል የደንቆሮውች ስብስብ ነው። ወያኔ ጊዜ መግዣ ማደናገሪያ እና ማዘናጊያ የፖለቲካ ብልሃቱ ይችው ብቻ ስለሆነች ውይይት ድርድር ክርክር የሚሉት የፖለቲካ ጢባጢቤ የሚጫወተው የውስጥ ጉዳዮቹን ለማጥራት ሕዝቡን ፀጥ ለማሰኘትና የራሱን የስልጣን እድል ለማስረዘም ነው።ከወያኔ መልካም ነገር መጠበቅ የዋህነት ነው። የፖለቲካ እስረኞችን ከመፍታት ይልቅ ድርድር ውይይት ክርክር በተባለበት በዚህ ወቅት ነገር ከማለዘብ ምሕዳር ከማስፋት ይልቅ በበለጠ መልኩ እስሩን አፈናውንና ማስፈራራቱን ቀጥሏል። ታዲያ ከእንደዚህ አይነት መዥገር ማፊያ ቡድን እንዴት ድርድር ይጠበቃል ፓርቲዎቹ ይህን ጥያቄ ከመመለስና ከመወያየት በፊት ራሳቸውን የኣምባገነኖች ገጸበረከት ስላደረጉ የሚሰማቸው የለም።

ወያኔ ምናልባት ነገ መልሶ የሚያስራቸውን በጣት የሚቆጠሩ እስረኞች ሊፈታ ይችላል ። ይህን የፖለቲካ እስር ማስቆም የሚቻለው ፓርቲ የለም። ይብስ ብሎ በፓርቲዎች ውስጥ ያለ ሽኩቻ ለወያኔ ሌላው መጠቀሚያ ሲሆን የፓርቲ አመራሮቹ ራሳቸው በእስር እንዲቆዩላቸው የሚፈልጉ የፓርቲ ኣባሎቻቸው እንዳሉ ለወያኔ ከሰጡት መረጃ ለማወቅ ተችሏል።ፓርቲዎቹ የመተማመኛ ድምጽ ይሁን በሕዝብ ዘንድ ስም የላቸውም ይህ ብቻ ሳይሆን እርስ በእርስ ስምምነት የላቸውም።ሕዝቡ በፍፁም ታማኝነት አይቀበላቸውም።ይልቅ የሃገር ውስጥ ፓርቲዎች ስልጣን ከሚይዙ ወያኔ ይቆይልን የሚሉና በዲያስፖራ ፓርቲዎች ላይ ተስፋ የጣሉ ይበዛል።በዚህ ሁኔታ ውስጥ እየተጓዝን እንዴት ድርድር ውይይት ክርክር የሚባሉ ነገሮች እንደሚደፈሩ በፖለቲካ መስመር ታክቲክ አልባነትን ያመላክታሉ።


በከፋኝ ሃይል ላይ የወያኔን የስለላ ስልት የሚያጋልጥ መረጃ እጃችን ገብቷል። – አስናቀው አበበ

$
0
0

ወያኔ የጎበዝ አለቆችን/የነፃነት ኃይሎችን የሚያጠቃበት ድብቅ ዘዴ መረጃው እንደደረሰኝ ከሆነ እንደሚከተለው ነው።

በመጀመርያ ረብጣ ብር በአካውንታቸው የሚቀመጥላቸው ለገዳይ ወይም ያሉበትን ከእነሙሉ መረጃ የሚያቀብል ወሳኝ ውስጡ አረመኔ ወያኔ ታጋይ መስሎ ይቀላቀላል። ከቻለ ዞር ዞር ብሎ መደዋወል የውሎ ዘገባ እያደረሰ እንደ ታጋዮች እየተራበ እየተጠማ አብሮ ይመርጃል፡፡ ስለዚህ ይህኛው ብስለት እና ጥርጣሬ ያላቸው ታጋዮች መረጃ በማውጣት ያስመቱናል ብለው ከፍተኛ ክትትል የሚያደርጉ ሲሆን ደግሞ ምስኪኑ ታጋይ አማራ በማይገምተው እና ከቴክኖሎጂው ጋር ወያኔ እራሱ ሰላይ/ገዳይ ብሎ ለላከው የወገን አሚኬላ ሰው እንኳ ሳይነግረው እያደረገ ያለውን ወሳኝ ክንውን ይህ ነው፡-

በመጀመርያ የሚልኩት እና ተልዕኮውን ለተቀበለው በሳንቲም ለተገዛው ከትምህርት ሒወት ጋ ያልተዋወቀ አርሶ አደር ወይም መሠል ግን የተሰጠውን ተልእኮ በትክክል ባይወጣ እንኳን ወያኔ ስልቱን እየቀያየረ ይቀጥላል።

ቅጥረኛው ያለበት ቦታ የሚፈልጓቸው ታጋዮች እንዳሉ የተልእኮው ግብ ስለሆነ ቢዋሻቸው እንኳ ዘመን ያፈራቸውን የቴሌኮሞ ለመረጃ የሚጠቅማቸውን ለምሳሌ ጂፒኤስ ወዘተ micro software የተጫነበት ስልክ ቀፎ እንዲሁም የተመዘገበ የስልክ መስመር አያይዘው በcenter point ታስሮ እንደሚዘወር …ይለቁታል፡፡

ከዚያ የመጨረሻዋ 100% ውጤታማ የሚያደርጋቸውን ድርሻ ለethio telecom በትግሬ ያውም እጅግ አመኔታ ለተሰጠው የወያኔ የመረጃ ቋት ሰብሳቢ ባለሙያ በNetwork የሳት ላይት ክትትል 24 ሰዓት እየተቀያየሩ ልክ እንደ አየር መቋወሚያ ራዳር ያለእረፍትት ሙሉ እንንቅስቃሴውን የፎቶ እና የVidio መረጃ ሲያዝ ይቆያሉ። ከዛ ለዚህ ተላላኪ ገዳይ/መራጅ ሰው ደውለው የት ነው ያሉ እንምጣ ይሉታል። እዚህ ላይ ማወቅ ያለብን በትክክል ያሉበትን ከእንቅስቃሴ መረጃቸው ከሰጠው ጋር ተመሳሳይ ከሆነ ክተት ብለው ያጠቋቸዋል።
ግን ባጋጣሚ መረጃውን ቢዋሻቸው እንኳ አይችልም፡፡ ምክንያቱም ቅድሚያ አወቀም አላወቀም በጫኑለት ጠቋሚ software አጋዥነት የሳትላይት መረጃ ሙሉውን ተከታትለው ስላስቀሩ አሁንም ክተት ብለው ራሱን ጨምረው ወሳኝ ያሉትን ጥቃት ይሰነዝራሉ፡፡ ይህን ከፍተኛ መረጃ አሳልፎ የሰጠው በዚህም የረቀቀ መረጃ ውጤት ዘማች ወንድም ዘመዴን እገላለሁ በማለት ፀፀት የገባ የደህንነት ሰው ለመሆኑ የመረጃ ምንጮቻችን አስምረውበታል፡፡ ስለዚህ የሚደረጉ ጥንቃቄዎች ለጎበዝ አለቆች ይድረስ። ህዝቡም የጥንቃቄ እርምጃ ይውሰድ።
ህዝብ ያሸንፋል©!

የሃያ ሁለቱ ፓርቲዎች ክርክርና ድርድርን በማስመልከት ከዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ጋር የተደረገ ቆይታ

$
0
0

if(typeof(jQuery)==”function”){(function($){$.fn.fitVids=function(){}})(jQuery)};jwplayer(‘jwplayer-1’).setup({“image”:”http://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2017/03/negaso.jpg”,”file”:”http://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2017/03/893ec0cd-da15-44e5-8ec6-3e089d60d742_hq.mp3″});

በገዥው ፓርቲና በሀገር አቀፍ ፓርቲዎች መካከል ሊካሄድ የታቀደው ድርድር በበርካታ ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩር የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ተስፋቸውን ገልፀዋል፡፡

በተደራዳሪዎች ፓርቲዎች ብቻ ሊወሰኑ የማይገባቸው እና የሕዝቡን ይሁንታ ጭምር የሚጠይቁ ጉዳዮች ሊኖሩም እንደሚችሉም ጠቁመዋል፡፡

ገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ እና ሃያ አንድ ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች ለድርድር የሚያደርጉትን ዝግጅት ቀጥለዋል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክርና የድርድር የአሠራር ረቂቅ ደንብ በሚባለው ሰነድ ላይ የሚያደርጉት ውይይትም አልተቋጨም፡፡ እናም ተደራዳሪዎቹ በየትኞቹ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ ገና አልተወሰነም፡፡ የአብላጫ ድምፅ ሥርዓት የሚባለውን የምርጫ ሥርዓት ማሻሻል አንዱ ነጥብ ሊሆን እንደሚችል የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት እና የግል የፓርላማ አባል ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ይገምታሉ፡፡

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳን ያነጋገራቸው እስክንድር ፍሬው ተከታዩን ልኳል፡፡

 

አዲሱ የጉዞ ዕገዳ – ድጋፍና ተቃውሞ – ቪኦኤ

$
0
0

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ

ከአዲሱ የዩናይትድ ስቴትስ የጉዞ ዕገዳ ዝርዝር የተፋቀችው የኢራቅ መሪዎች አዲሱን የዕገዳ ትዕዛዝ ሲያሞካሹ፤ አሁንም በዝርዝሩ ውስጥ የቀረችው የሱዳን መሪዎች ግን ትዕዘዙን አውግዘውታል፡፡

ከአዲሱ የዩናይትድ ስቴትስ የጉዞ ዕገዳ ዝርዝር የተፋቀችው የኢራቅ መሪዎች አዲሱን የዕገዳ ትዕዛዝ ሲያሞካሹ፤ አሁንም በዝርዝሩ ውስጥ የቀረችው የሱዳን መሪዎች ግን ትዕዘዙን አውግዘውታል፡፡

የኢራቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አህመድ ጀማል ለአሶሺየትድ ፕሬስ የዜና አውታር በሰጡት ቃል “የኢራቅ ከዕገዳው ዝርዝር መፋቅ የእሥላማዊ መንግሥት ቡድን ፅንፈኞችን ለመፋለም በኢራቅና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል ያለውን ትብብር ያጠናክረዋል” ብለዋል፡፡

ኢራቅ ከዕገዳው ዝርዝር እንድትወጣ የተደረገው የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ከኢራቅ መንግሥት ጋር በመሆን የተጓዦችን ማንነት ለማጣራት የሚደረገው ሥራ እየተጠናከረ መምጣቱን ከልሶ ከፈተሸ በኋላ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሬክ ቲለርሰን ገልፀዋል፡፡

በሌላ በኩል ግን ከኢራን፣ ሶሪያ፣ የመን፣ ሊብያና ሶማሊያ ጋር ለመጭዎቹ ዘጠና ቀናት ለዜጎቻቸው ቪዛ እንዳይሰጥ በወጣው አዲስ ዕገዳው ዝርዝር ውስጥ የቀረችው የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ በትራምፕ አዲስ ትዕዛዝ የተሰማውን ቅሬታ ተናግሯል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የትረምፕ አዲስ ትዕዛዝ ምንነት በግልፅ ተለይቶ እስኪታወቅ ድረስ ዜጎቹ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ሊያደርጉ ያቀዱትን ጉዞ ወደ ሌላ ጊዜ እንዲያስተላልፉ የናይጀሪያ መንግሥት ጥሪ አውጥቷል፡፡

በውጭ ጉዳይና ግዩራን ጉዳዮች የናይጀሪያ ፕሬዚዳንት ልዩ ረዳት የሆኑት አቢኬ ዳዊሪ ኤሬዋ የመንግሥታቸው ማሳሰቢያ የወጣው “በቅርቡ ከዩናይትድ ስቴትስ አይሮፕላን ጣቢያዎች ሰዎች ወደየመጡበት እንዲመለሱ በመደረጋቸው ሰዉ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ለመምከር ነው” ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ይህንን የተከለሰው የፕሬዚዳንት ትረምፕ የጉዞ ዕገዳ ትዕዛዝ ብዙ ቁጥር ያላቸው የዩናይትድ ስቴትስ ሪፐብሊካን እንደራሴዎች እንደሚደግፉት በአድናቆት ቢገልፁም የዴሞክራቲክ ፓርቲው የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባል በርኒ ሳንደርስና በርካታ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድኖች “ዘረኛና ፀረ-ሙስሊም” ሲሉ አውግዘውታል፡፡

የተወካዮች ምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ ሪፐብሊካኑ ራያን ፖል አዲሱ ትዕዛዝ ዩናይትድ ስቴትስን ከአደጋ የመጠበቅን የጋራ ግባችንን ወደፊት ያራምዳል ሲሉ ያሞካሹት ሲሆን ሪፐብሊካኑ ሴናተር ሊንድዚ ግራሃም ደግሞ አዲሱ ዕገደ ካለፈው በተለየ ሁኔታ በሐይማኖት ላይ ያነጣጠረ ተደርጎ እንደማይወሰድና የሕግ ፍተሻዎችን ያልፋል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል፡፡

አዲሱ ሕግ የሚመለከተው ደኅንነታቸውና ፀጥታቸው ጥያቄ ውስጥ ከወደቀና በጨነገፉ መንግሥታት የሚነሱ ግለሰቦችን ነው ብለው እንደሚያምኑ ግራሃም ተናግረዋል፡፡

አሮጌውና አዲሱ የጉዞ ዕገዳ

አሮጌውና አዲሱ የጉዞ ዕገዳ

ዴሞክራቱ በርኒ ሳንደርስ ግን ከሪፐብሊካን ባልደረቦቻቸው ሃሣብ ጋር በሚቃረን ሁኔታ “ትዕዛዙ ሙስሊሞችን ነጥሎ ለመጉዳትና ሊከፋፍለን የታሰበ ነው” ሲሉ በብርቱ እንደሚያወግዙት አስታውቀዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በሃያ ስምንት የአሜሪካ ከተሞች ውስጥ ስደተኞችን የሚያሰፍረውና በአርባ ሃገሮች ውስጥ የሚንቀሣቀሰው ዓለምአቀፍ አዳኝ ኮሚቴ የሚባለው ቡድን የጉዞ ፍተሻዎቻቸውን ጨርሰው ለመንቀሣቀስ እየጠበቁ ያሉ ወደ ስድሣ ሺህ የሚሆኑ ስደተኞች ዕጣ ፈንታ በአዲሱ ትዕዛዝ ምክንያት አደጋ ላይ መውደቁን አስታውቋል፡፡

አምነስቲ ኢንተርናሽናል የሚባለው የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት ደግሞ አዲሱን ትዕዛዝ “በሌላ መጠቅለያ የቀረበ ያው የነበረው የጥላቻና የፍርሃት ጥቅል ነው” ብሎታል፡፡

እስከመቼ ሃይለማሪያም በነሳሞራ እየተናቀ ይኖራል ? #ግርማ_ካሳ

$
0
0
የአፍሪካ ኢንተሊጀንስ ጠቅሶ ዘሃበሻ የሚከትለዉን ዘግቧል። አፍሪአ ኢንተሊጄንስ የሚታመን ምንጭ ነው። ኢሕአዴእግ ስልጣን እንደያዘ ገና የአዲስ አበባ ቻርተር ሳይጸድቅ የኢትዮጵያ አወቃቀር ምን እንደምትመስል አፍሪካ ኢንተሊጀንስ ነበር ያወጣው። ብዙም አልቆይም በቻርተሩ ጸደ
 
ይሄ ሜዲያ ብዙዎቻችን ለአንባቢያን ለምሳየት ስንሞክር የነበረውን ነገር ነው በግልጽ ያስቀመጠው። በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለው ሁለት መንግስት ነው። አንደኛው በሃይለማሪያም ደሳለኝ የሚመራው ሲሆን፣ ሁለተኛ በጥቂት ህወሃቶች የሚመራውው፣ ደህንነቱን እና ሰርራዊቱን የሚቆጣጠረውው፣ እነ ኃይለማሪያም የማይታዘዝ ብቻ ሳይሆንን የሚንቅንና መመሪያዎች በጎን እየላከ ዉሳኔያቸውን የሚሰርዝ አካል ነው።
 
እና ሃይለማሪያም የአገር ችግር በድርድር እንዲፈታ ያለው ፖለቲካ እንዲለዝብ የሕዝብ ጥያቄ እንዲፌታ ይፈልግጋሉ። ይህ አሁኡንን ይደረጋል የተባለውንን ድርድር ያመቻቹት እነርሱ ናቸው። ግን የሕወሃቱ ሁለተኛው መንግስት ድርድር የሚባል ነገር አይፈለግም። እያሰረ፣ እየገድደለ፣ እያፈናቀል በጥጋብና በ እርብሪት መግዛት ነው የሚፈለገው። ለዚህ ነው ተቃዋምሚዎች ከድርድሩ እዲወጡ አመራሮችን እያሰረ ያለውና የሚከሰው።
 
ህወሃት ለ547 መቀመጫ 38 ብቻ ነው ድምጽ ያለው። በኢሕአዴግ ዉስጥ ደግሞ አንድ አራተኛ ብቻ ነው መቀመጫ ያለው። ታዲያ እንዴት በዚህ መልክ እየተዋረዱና መሳቂያ እየሆኑ ዝም ብለው ያያሉ ? እስከ መቼ ነው እነዚህ የታሪክ አተላዎችን ይታገሳሉ ? እስከመቼ ነው፣ ግድ የለም ለሌላው አይቁሞ ለራሳቸውና ለክብራቸው እንኳን የማይቆሙት ? እስከ መቼ እነ ሶሞራ እንደ ዉሻ እያዩዋቸው ዝም የሚሉት ?
 
አንድ ጊዜ በብአዴን ጉባዬ አባላቱ “እነርሱ ባልፎቅ ሲሆኑ እኛ ሎተሪ ሻጮች ነው የሆንነው” እያሉ ሲያማረርሩ ነበር። እስከመቼ ነው የሚያማርሩት ?
 
http://www.zehabesha.com/ethiopia-tigrayan-officers-defy-the-government/

መኢአድ እና ሰማያዊ በጋራ የአድዋን መንፈስ ያስታወሣሉ – የሚሊዮኖች ድምጽ

$
0
0

ገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ ላለፉት 25 አመታት በኢትዮጵያዊነት ላይ ዘምቶ፣ ህዝብን ከሕዝብ በማጋጨት፣ በዘር በመከፋፈል ፣ አንዳችንን በአንዳችን ላይ እንድንነሳ በመገፋፋት ፣ አገርን በዘር በመሽንሸን፣ ህዝብን የሚጎዱ ተግባራትን ሲፈጸም እንደነበረ የሚታወቅ ነው። አሁንም እየፈጸመ ነው።

ከመቶ ሃይ አንድ ዓመት በፊት ወራሪ ጣሊያን ሚሺነሪዎችን፣ ዲፕሎማቶች እያሰማራ፣ በጥቅምና በገንዘብ ለመደለል እየሞከረ ኢትዮጵያዉያን በአንድነት እንዳይቆሙ ብዙ መድከሙ የሚታወቅ ነው። ሆኖም በወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ዳግማዊ አጼ ሚኒሊክ፣ በዘዴና በጥበብ የተጣላቸውን እያግባቡ፣ የበድላቸውን ይቅር እያሉ፣ መኳኳንንቱን ህዝቡ ሁሉ አንድ አድርገው ጣሊያንን ገጠሙ። አንድነት ሃይል ነውና አንድነታቸው ሃይል ሆኗቸው ወራሪ ጠላትን ድባቅ አደረጉ። ለኢቱጵጵያ ብቻ ሳይሆን ለጥቁር ህዝብ ሁሉ ኩራት የሆነ ገድል ተፈጸመ።

አሁንም አገራችን ሊያፈራርሷት፣ ሊያጠፏት የተሰማሩ ጠላቶች አሏት። ድህነት፣ ጭቆና፣ ኢፍትሃዊነትት፣ ኢሠብአዊነት፣ ፍርድ ገምድልነት ፣ ዘረኝነትና አምባገነንነት…የመሳሰሉት። እነዚህ ጠላቶችን ማሸነፍ የሚቻለው በትብብርና በአንድነት ነው።

የመላው ኢትዮጵጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና የሰማያዊ ፓርቲ የፊታችንን ቅዳሜ በመኢአድ ጽ/ቤት፣ በጋራና በአንድነት ሆነው፣ የአድዋ በአልን ያከብራሉ። ሁለቱ ድርጅቶች በተናጥል የሚያደርጉት እንቅስቃሴ የትም እንደማያደርሳቸው ተረድተው ሪሶርሳቸውን በጋራ ለመጠቀም ፣ በጋራ ለመንቀሳቀስ አልፎም ለመዋሃድ ሃሳብና እቅድ እንዳላቸው ይነገራል። ይሄ በጋራ የአድዋ በአልን የማዘጋጀት ሂደቱን ይሄን ትብብራቸውን የሚያመላክት ነው።

የአደዋ መንፈስ የአንድነት መንፈስ ነው።ከፊታችን የተደቀነውን ፈተና ማለፍ የምንችለው በአንድነትና በመተባበር ነው። መኢአድ እና ሰማያዊ እያሳዩ ያሉትን የትብብር መንፈስ በጎነቱን እየገለጽን ግፉበት እንላለን።

የግንቦት ሰባት አመራራ አቶ አበበ ቦጋለ ከኦነግ፣ ኦብነግ ..ጋር እየተነጋገሩ እንደሆንነ ገለጽ

”ማርች 8” እና ኢትዮጵያዊቷ ሴት ዛሬ!

$
0
0
ጉዳያችን/ Gudayachn

ኢትዮጵያውያን በሳውዲ አረብያ ስደት ላይ

”ኢትዮጵያዊቷ  ሴት ለየት ያሉ ባህርያት አላት። በቅዱሱ መፅሐፍ ላይ ሙሴ ህዝበ አስራኤልን ይዞ ከግብፅ ወደ ተስፋይቱ ምድር ሲገባ በስራው ሁሉ የምትረዳው እና ለትዳሩ አጋር ያደረገው ኢትዮጵያዊቷን መሆኑን በቅዱስ መፅሐፍ ውስጥ ማንበቤን አስታውሳለሁ።’በምድር ከሚነሱት ነገስታት ማንም ያንተን ያህል ጥበብም ሆነ ሀብት አይኖረውም’ የተባለው ንጉስ ሰለሞን ልቡን ከፍቶ የሆዱን ያወራው ከኢትዮጵያዊቷ ንግስት ሳባ (አዜብ) ጋር ነው።ኢትዮጵያውያን ሴቶችልዩ ናቸው።ክብራቸው፣ዝምታቸው፣እርጋታቸው እና አስተዋይነታቸው ሁሉ የተለየ ድባብ ያላብሳቸዋል ።አዲስ አበባ ለስብሰባም ሆነ ለተመሳሳይ ሥራ ስሄድ ከምገባበት ኬክ ቤት ጀምሮ አስከ አየር መንገዳችሁ አስተናጋጆች ድረስ ያሉት ሴቶችሁ ልዩ፣አስተዋይ እና ብሩህ አእምሮ አላቸው።” ይህንን ያሉት ከአመታት በፊት ካምፓላ ውስጥ በሚገኘው  ማካራሬ ዩንቨርስቲ ውስጥ የልማት ጥናት ፕሮፌሰር ዩጋንዳዊው  ማተምቤ ለክፍል ተማሪዎቻቸው ነበር።

አዎን! ከተናገሩት ውስጥ አንድም የሚጣል እንደሌለው አውቃለሁ። ያንን ንግግር ዛሬ ላይ ሆኘ ሳየው በተለይ” ማርች 8 የሴቶች ቀን ታስቦ ዋለ” የሚለው ከኮሚንስቶች ፕሮፓጋንዳ ያላለፈ፣ የወረቀት እና ንግግር ማሳመርያ ዜና መሰል ነገር ከወደ  ሀገር ቤት ስሰማ ያስገርመኛል።ይህ ማለት ግን ”ማርች” ስምንት የሴቶች ቀን መከበር የለበትም የሚል ሃሳብ የለለኝ መሆኑን እንዳትዘነጉብኝ።አከባበሩ አንዳች የረባ የሴት እህቶቻችንን ሕይወት የሚያሻሻል ሥራ ተሰርቶ ቢሆን ጥሩ ነበር።ሁኔታው ተቃራኒ ሆኖ ሳለ ስለ በዓሉ ማውራት በራሱ በሴት እህቶቻችን ላይ ከመቀለድ አይተናነስም።

የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኮሚሽን ( UNHCR) ሰኔ 27/2011 አንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ”በ2011 የሰዎች ዝውውር በኢትዮጵያ” በሚል ርእስ  ባወጣው ሪፖርት ላይ አንዲህ የሚል ሰፍሮ ይገኛል።

”Young women, most with only three to four years of primary education, from various parts of Ethiopia are subjected to domestic servitude throughout the Middle East, as well as in Sudan, and many transit through Djibouti, Egypt, Libya, Somalia, Sudan, or Yemen as they emigrate seeking work. Some women become stranded and exploited in these transit countries, unable to reach their intended destinations. Many Ethiopian women working in domestic service in the Middle East face severe abuses indicative of forced labor, including physical and sexual assault, denial of salary, sleep deprivation, and confinement. Many are driven to despair and mental illness, with some committing suicide…..” 

”ከሦስተኛና አራተኛ ክፍል ያልዘለሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን ሴቶች ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች መጥተው ጅቡትን፣ግብፅን ፣ሊብያን፣ሶማልያን፣ሱዳንን ወይንም የመንን አርጠው ወደ መካከለኛው ምስራቅ አረብ ሃገራት ለመሄድ ይሞክራሉ።ብዙዎች ገና እነኝህን ሃገራት ሳይሻገሩ እዝያው ጉልበታቸውን ሸጠው እንድያድሩ ያረጋቸዋል….በመካከለኛው ምስራቅ በሥራ ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያን በከባድ የጉልበት ሥራ፣የአካልና የፆታ ጥቃት፣የለፉበትን የመነጠቅ ወዘተ ይፈፀምባቸዋል።በእዚህም ምክንያት ብዙዎች የአአምሮ ህመም ደርሶባቸው እራሳቸው ያጠፋሉ….”

”እማዬ ለምን ወለድሽኝ ?”

ዛሬ በሺህ የሚቆጠሩ እህቶቻችን በሊባኖስ፣ሳዑድአረብያ፣የተባበረው አረብ አምረት፣ኩዌት፣ወዘተ በቤት ውስጥ ሥራ እና በተለያዩ አስከፊ ተግባራት ተሰማርተው ይገኛሉ።አዲስ አበባ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቢሄዱ በሺህ የሚቆጠሩ እህቶቻችን ለአረብ ሀገር እንግልት ሲሳፈሩ ያገኛሉ። ይህ ብቻ አደለም በቅርቡ በአዲስ አበባው ራድዮ እንደተገለፀው ወደ አረብ ሀገር የሚያሰድዱት ደላሎች ከከተሞች ይበልጥ ሰፊ የመገናኛ መረባቸው  በገጠር ውስጥ መሆኑ እና ለምሳሌ  በወሎ ውስጥ በምትገኝ የአንድ ገበሬ ማህበር መንደር ውስጥ ለማህበራዊ ጉዳይ  ከተሰበሰቡት ገበሬዎች ለናሙና በተወሰደ መረጃ ከሃምሳ ገበሬዎች ውስጥ ሰላሳ ሁለቱ ልጆቻቸውን ለአረብ ሀገር እንግልት መላካቸውን ገልፀዋል። ከእዚህ ሁሉ  አሳዛኙ ነገር ደግሞ ሁሉም  የሴት ልጆቻቸውን ወሬ ሰምተው የማያውቁ መሆናቸውንና ግራ መጋባታቸውን በለቅሶ መግለፃቸው ነው ። የእህቶቻችን ጉዞ በአየርመንገድ ብቻ የምመስለን ካለን በጣም ተሳስተናል። በ እዚሁ የራድዮ ዘገባ መሰረት ባለፉት አምስት ወራት ብቻ በሱዳን በኩል የወጡት እህቶቻችን ብዛት በብዙ አስር  ሺዎች የሚቆጠር  መሆኑም ተነግሯል።

በአረብ ሀገር ያሉት እህቶቻችንን መከራ ና ስቃይ መተንተን በቃላት መቀለድ ሆነብኝ።ከፎቅ ላይ እራሳቸውን የወረወሩትን፣መርዝ የጠጡትን፣የፈላ ውሃ የተደፋባቸውን፣ምግብ ሳይበሉ በረሃብ ጠኔ ሕይወታቸው ያለፈውን፣እስር ቤት ተወርውረው ተረስተው የሞቱትን፣ ኩላሊታቸው  የቀዶ ጥገና ሕክምና አዋቂ ባልሆኑ ሰዎች ወጥቶ የተወሰደባቸውን (ከዓመት በፊት ‘ሲ ኤን ኤን’ የተሰኘውን የ አሜሪካ ቴሌቪዥን በኢትዮጵያውያን እህቶቻችን የኩላሊት መወሰድ ላይ ያሳየውን ዘገባ ልብ በሉ) እህቶቻችን ዛሬም ”እማዬ ለምን ወለድሺኝ?” እያሉ ነው።መከራን የምንረዳው እኛ  በዝያ መከራ ውስጥ ተገብተን አልያም በእህታችን ወይንም በሴት ልጃችን  ላይ ደርሶ ቢሆንስ? ብለን ስናስብ ብቻ ሊሆን ይችላል።

ኢትዮጵያዊት ሴት በአረብ ሃገራት ውስጥ የተዋረደችውን ያህል በታሪካችን ኢትዮጵያ የተዋረደችበት (ውርደቱ የአኔም፣የናንተም፣የሁላችንም መሆኑን ሳንዘነጋ) ጊዜ ነበር ለማለት አያስደፍርም ።በአረባውያኑ ምድር  ኢትዮጵያውቷን ሴት አይዞሽ ባይ ማጣት፣ግራ መጋባት፣ተስፋ መቁረጥ፣ግፍ እና መከራው አንገላተዋት ባዶ አውላላ ሜዳ ላይ የቀረች ብቸኛ ፍጥረት የሆነች ያህል እየተሰማት ያለችበት ጊዜ ነው። ሀገሮች በድንበር መካለል ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ በመካከላቸው  የሚኖረውን  ግንኙነት ከንግዱ  ዘርፍ ባለፈ የ ሰዎች ከቦታ ወደ ቦታ መዘዋወር ሌላው  የሚያገናኛቸው ጉዳይ ነው። ይህ ግንኙነት ደግሞ ዲፕሎማስያዊ ግኑኝነት እንድያዳብሩ ትልቅ በር ከፍቷል ።

ዲፕሎማስያዊ  ግንኙነት  በ ዘመናት ውስጥ የራሱን አድገት አያሳየ አሁን ካለንበት ዘመን ደርሰናል።የ ዲፕሎማሲ  ግንኙነት አጅግ ሚስጥራዊ  በሆነ መንገድ ሲሰራበት የነበረውን ዘመን  አልፎ ዛሬ ”public diplomacy” ”ግልፅና ሕዝቡን መሰረት ያደረገ” የዲፕሎማሲ  ዘመን ላይ እንገናኛለን። የሀገሮችን የዲፕሎማሲ ግንኙነት መልክ ለማስያዝና  ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት በሁዋላ  በሀገሮች መካከል የነበረውን ግንኙነት መልክ ያስያዘው ብሎም የዓለም አቀፍ ሕግን ቅርፅ የሰጠው አሁንም ድረስ በሥራ ላይ የሚገኘው የዲፕሎማሲ ሕግ የ” ቬና ኮንቬንሺን”(የቬና ውል) ይባላል። ይህ ውል በሚያዝያ 18/1961 እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር ወጥቶ በሚያዝያ 24/1964 አሁንም እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር ሥራ ላይ ዋለ።በአውሮፓውቷ ሀገር ኦስትርያ ዋና ከትማ ቬና ውሉ ሲፈረም ከፈረሙት ሀገሮች አንዷ በወቅቱ አብዛኛዎቹ  የአፍሪካ ሀገሮች በቅኝ ግዛት ስር በሆኑበት ዘመን ሀገራችን ኢትዮጵያ ግን የ ውሉ ቀዳሚ ፈራሚ ብቻ ሳትሆን በማርቀቅ ሂደቱም ሁሉ ተሳታፊ ነበረች።ዛሬ ግን የእዚህን ውል ዋና አካል የሆነውን አንቀፅ ሶስት የ አትዮጵያ መንግስት ከነመኖሩም የዘነጋው ይመስላል።

የ ቬና ውል አንቀፅ ሶስት ”b”  አንዲህ ይላል : –

Article 3
1.The functions of a diplomatic mission consist, inter alia, in:
(a) Representing the sending State in the receiving State;
(b) Protecting in the receiving State the interests of the sending State and of its nationals, within the limits permitted by international law; 2

”የአንድ ሀገር የዲፕሎማሲ ሉዑክ   አንዱ ተግባር በተቀበለው ሀገር ውስጥ የሃገሩን ጥቅሞችና የዜጎቹን ጥቅሞች የአለማቀፍ ሕግ ማቀፍን በተከተለ መንገድ ማስከበር ነው” ይላል።

የሀገራችን የወቅቱ የኢህአዲግ/ወያኔ መንግስት አባልነትን መሰረት ያደረገ እና ቅድምያ ለመንግስት ታማኘትን ማእከል ያደረገው የሀገራችን ወቅታዊ  የዲፕሎማሲ ስርዓት በመካከለኛው ምስራቅ ለሚሰቃዩት እህቶቻች በቁስል ላይ ቁስል ሆኖባቸዋል።

ዛሬ  ለእህቶቻችን  በሄዱበት ሀገር መብታቸውን ለማስከበር ኃላፊነት ያለበት  መንግስት መሆኑን የሚዘነጋው አይኖርም ።ይህ ደግሞ በአለማቀፍ ሕግ እንደ መንግስት ተቁአምነት ግዴታው ነው።የአንድ መንግስት ቀዳሚ ተግባር የሃገሩን ሉዓላዊነት ከማስከበር ጀምሮ የ ዜጎቹን ደህንነት (ዜጎቹ በየትኛውም የ ምድር ማአዘን ቢኖሩ) ማስጠበቅ  ነው። አሁንም ይህ ኃላፊነት በቀጥታ የሚመለከተው መንግስትን ነው።መንግስት በአረብ ሀገር እንባዋን የምታፈሰውን ኢትዮጵያዊት ሴት ለመርዳት  የወሰደው አርምጃ   ትንሿ ጅቡቲ በዲፕሎማሲ ተልኮዋ ከምትሰራው ሥራ ያነሰ ነው ሲሉ  ብዙዎች ይተቻሉ።ይህም ተራ በስሜታዊነት የተሞላ  ነቀፋ  ሳይሆን በገሃድ የታየ  እውነታ ነው።

በሶርያ፣ሊባኖስ፣ሳዑድ አረብያ፣ሱዳን የነበረውን ሁኔታ የሚያውቁና በሃገራቱ ውስጥ ያሉትንም ሆነ በአካባቢው ሃገራት ያሉትን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ በሮች ሲማፀኑ የነበሩት እህቶቻችን ቢናገሩት ይቀላል። የኢትዮጵያውቷ ሴት እሮሮም ይሄው ነው። እንዴት ሀገር እንደለለኝ፣ወገን እንደለለኝ፣የተከራከርልኝ  አጣሁ? ለምን በ አረብ ምድር ተገፋሁ? ዛሬም የሚሰማ ድምፅ ነው።

”ማርች ስምንት” የሴቶች ቀን በዓል በአረብ ሀገር የመከራ ቀን ለምትገፋው  ለኢትዮጵያውቷ ሴት የመራር ፌዝ ያህል ሆኖ ቢሰማት አይፈረደም።የዛሬ ሃምሳ ዓመት በፊት የ”ቬናን” ስምምነት የፈረመችው ሀገር ዜጎች ዛሬም መረር ያለ ዲፕሎማስያዊ እርምጃ ወስዶ” ዘጎቼ ተሰቃዩ” ብሎ የሚናገርላቸው መንግስት አጥተው ያለቅሳሉ።


እኛ ወደ ትግሉ ካልሄድን ችግሩ ወደኛ መምጣቱ አይቀሬ ነው – ባህር ከማል

$
0
0

እራስን ከጥቃት በመከላከል ሰላማዊ ህወት ለመምራት  ከሌሎች ሰዎች ጋር ተቻችሎና ተስማምቶ አብሮ የመሆን ባህርይ የሰው ልጅ በተፈጥሮ የሚያገኘውና በህወት ልምድም የሚያዳብር ችሎታ ነው ማለት ይቻላል።ይህ  አብሮ  የመሆን  ልምድ ከቤተሰብ  ጀምሮ በጉርብትና፤  በጎሳና ሀይማኖት መመሳሰል እያደገ  ሃገርን  እስከ መመሥረት ይደርሳል። በሂደትም  አንድነት ሃይል መሆኑንም ያረጋግጣል።  እነዚህ በየደረጃው ያሉት ስብስቦች በውስጣቸው ልዩነት መኖሩ አይካድም።ልዩነት በሀገር ደረጃ በተሰባሰቡ ሰዎች መሀከል ብቻ ሳይሆን በመንትዮች መሃከልም ይታያል። ህዝቦች ልዩነታቸው  አንደተጠበቀ ሆኖ በጋራ በሚያስተሳስራቸው፤ በሚያቀራርባቸውና ባሳለፏቸው ታሪካዊ አብሮነት ተመስርተው  አንድነትን ፈጥረው  በድንበር የተከለሉ ሃገራትን መስረተው አብረው ይኖራሉ።

ከአንድነት የሚገኙ በርካታ ጥቅሞች መኖራቸው በጣም ግልጽ ሆኖ ሳለ የህዝቦችን አንደነት የሚጠላ ግለሰብም ይሁን ስብስብ መኖሩ ብዙዎቻችንን ግራ የሚያጋባ ክስተት ነው። ሀቁ ግን አንድነትን የሚጠላ በአንድነቱ የማይጠቀምና የሚጎዳ ብቻ ነው። እርግጥ ነው አንዳንድ ሰዎች ስብስብን የሚፈጥሩት ለክፉ ነገርም ሊሆን ይችላል።  እንዲህ አይነት ስብስብ የሚፈጥሩት ግለሰቦች ግን ምንግዜም ቢሆን ሰው በዙሪያቸው የሚያሰባስቡት አንዱ ሌላውን እንዲጠላ በመስበክና ለሚቀሰቅሱት ህብረተሰብ ከነሱ ሌላ ወዳጃና መሪ እንደሌላቸ በመስበክ ነው። ለዚህም  እኛም መሀከል ለግል ጥቅም  ሲባልህዝብ ከህዝብ እያናከሱ አንቱ ተብለው ለመኖር ልዩነትን የሚያሰፉ ፕሮፖጋንዳ በመርጨት የተጠመዱ ወገኖች ያሉን።

ህወሃት  የህዝቦችን  አንድነት የሚፈራበት  ዋነኛው  ምክንያት ከኢትዮጵያ ህብረተብ ውስጥ በመቶኛ ሲሰላ  “ውክልናው” ከአናሳ የህብረተሰብ ክፍል በመሆኑ እራሱ በሚያቀነቅነው የፓርላማ  ዴሞክራሲ ቦታ ስለሚያሳጣው ነው። ለዚህም  እድሜን ለማርዘም በከፋፍለህ ግዛ ዘይቤው ህዝቦችንን መከፋፈልን ዋና መሳሪያው አድርጎት ይኸው  ሀያአምስት አመት አለፈው። ይሀንን ዘይቤ ከሞላ ጎደል በስኬታማነት እስከዛሬ  ለመጠቀም  የቻለባቸው ምክንያቶች ብዙ ቢሆኑም  ዋንኛው ግን ቀደም ሲል ለዘመናት የነበረውንና በተለያዩ ጊዜያት ብቅ ባሉት የገዥ  ክፍሎች  ወቅታዊ  ምላሽ ያላገኙትን የብሄር ጥያቄዎችን በ1936-42 ጣሊያን በሀገራችን በወረረችበት ወቅት ለተመሳሳይ መሰሪ አላማ የተጠቀመችበትን  ዘዴ (ከዚህቀደም ለማብራራት እንደሞከርትኩት) በመጠቀም የችግሩ ፈቺ  መስሎ በመቅረብ የአዞ እምባ በማንባት ነው።

ለዘመናት በአንድነት በመቆም ከውጭ ወራሪ ነጻነታችንን ጠብቀን የቆየን ብንሆንም ወያኔ  መከፋፈል ለእርሱ ስልጣን ላይ መቆያ ብቸኛ መፍትሄ እንደሚሆነ በመገመት ህዝባችንን የመከፋፈሉን ሴራ የጀመረው ጫካ ጠቅልሎ ከመግባቱ በፊት ነው። ታዲያ ለዚህ ከፋፋይ ሥራው እንቅፋት ሊሆንበት የሚችሉ ሁለት ሃይሎች የሃይማኖት አባቶችና ምሁራን ነበሩ ናቸውም። ሁለቱም ሃይሎች ህዝቡን በማንቃት ወደ ትክክለኛው መንገድ በመምራት ረገድ ተፅእኖ የመፍጠር አቅም ስላላቸው ውጥኑን ሊያከሽፉበት እንደሚችሉ ከጥዋቱ ተረድቶ ነበር። በመሆኑም እነዚህን የህብረተሰብ ክፍሎች በጠላትነት በመፈረጅ ለማንበርከክና ለማጥፋት ጥረት የጀመረው ገና ከትግራይ በረሃ ሳይወጣ ነበር።

ለዚህም የህወሃት የመጀመሪያ ኢላማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ናት። በታሪክ አጋጣሚ ቤተክርስቲያኒቷ በነበራት ሥፍራ ከአማራው ብሄር ጋር በማያያዝ አማራውን በጥቅል እንደ ጨቋኝና በዳይ በማቅረብ ከማጥላላት አልፎ የቤተክርታኒቷን መሬት በመንጠቅ ለደጋፊዎቹ አድሏል። መሪዎችንም ከአብተክርስትያን በማባረር ታዛዥ በሆኑት መሪዎች በመተካትና (ዶር.አረጋዊ በሪሄ ገጽ 302) እነሱንም ቢሆኑ የስለላ መዋቅሩን በቤተክርስታኒቷ ውስጥ ገዳማት ሳይቀሩ በመዘርጋት ሰላዮችን በመነኩሴነት በማስቀመጥ ይየሰልላቸው ነበር።

በወቅቱ በትግራይ የነበረው የሙስሊሙ ህብረተሰብ በቁጥር አነስታኛ ከመሆኑም በላይ ከክርስትና እምነት ታካታዮች በተለየ ሁኔታ ላይ ነበር (ዶር.አረጋዊ በሪሄ ገጽ 318)። የመሬት ባለቤትነት የሌለው ከመሆኑም ሌላ አብዛኛው ሙስሊም በንግድ ሥራ ላይ የተሰማራና  በከተሞች ውስጥ የሚኖር ነበር። የሙስሊሙ ህብረተሰብ ህወሃት (ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ) ሃይማኖቱን ሊያዳክምበት እንደመጣ በመገንዘብ እርኩስ አላማውን ለመቋቋም በተለይም  ከአፋር የእስልምና ተከታዮች (ገብረመድህን አርአያ ) ባደረገው ተጋድሎ የተነሳ ሀወሃት ከጥፋት ዘመቻው ጋብ ቢልም  ኋላ ላይ ግን  ይህንን  የህብረተሰብ  ክፍል  በፋሽስቱ  የጣሊያን ዘዴ “አዛኝ ቅቤ አንጓች” እንዲሉ አስመስሎ ከጎኑ ለማሰለፍ ስለመቻሉ መካድ ይከብዳል።

በተመሳሳይ መልኩ በምሁራን ላይም ዘመቻ በመክፈት በእንታረቅ ሰበብ በተኙበት ከመጨፍጨፍ አልፎ ውጊያ በመግጠም ብዙዎችን አስወግዷል። ለዚህም ከኢህአፓና ከኢዲዩ ጋር የነበሩትን ጦርነቶች መጥቀሱ ይበቃል። እነዚህ ግፎችና  ህወሃት ጫካ በነበረበት ወቅት የተከናወኑ ደባዎችና ፍጅቶች ሲሆኑ ያኔ አብሯቸው ከነበሩ የቀድሞ አባሎቻቸው ባይነገረን ወይም ባይፃፍ ኖሮ “ማን ያውራ የነበረ ማን ያርዳ የቀበረ” እንዲሉ እንኳንስ ሌላው ኢትዮጵያዊ ቀርቶ የትግራይም ህዝብ ባላወቀው ነበር።

በለስ ቀንቷቸው አዲስ አበባም ከገቡ በኋላ ይህንን እርኩስ አላማቸውን በመቀጠል እነዚህን ሁለቱን የህብረተሰብ ክፍሎችን በተጠናከረ ሁኔታ ኢላማቸው አድርገው እስከዛሬ ቀጥለውበታል። ለዚህም የኦርቶዶክስቤተክርስትያንን ቃኖና በመጣስ ጳጳስ በህይወት እያለ በሌላ በመተካትና ሲኖዶሱን ለሁለት መክፈል፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዬች ጠ/ምክር ቤትን (መጅሊስ) ለመቆጣጠር በ1987 በአንዋር መጂድ በየፀጥታ ሃይሎች የተፈጠረው እልቂትና እስካ እዛሬ ድረስ ለሙስሊሙ ህብረተሰብ ፈተና የሆነውና ለድምፃችን ይሰማ ንቅናቄ መፈጠር ምክንያት የሆነው ፤ ብዙዎች የተሰውበት፤ ብዙዎች የታሰሩበትና የተሰቃዩበት “ከአንዮታዊ ዴሞክራሲ ጋር ሊሄድ የሚችለውን የአህባሽ ሃይማኖት ተቀበሉ” ወከባ መጥቀሱ በቂ ነው። ህወሃት ለመሰሪ አላማው ያሰጉኛል ያላቸውን ምሁራንንም ለማስወገድ የመጀመሪያ ኢላማው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነበር።

ወያኔ/ኢህአዴግ በኢትዮጵያ ኦርቶዶች ተዋህዶ ቤተክርስትያንና  በምሁራን ላይ ያደረሰውናን እያደረሰ ያለውን ጥቃትና ይህ ጥቃት በበኩሉ ለነፃነት በሚደረገው ትግል ላይ ያሳደረውን ተፅእኖ ከቀላል አይደለም።ይህንን በተመለከተ   ሰፊ ሃተታ የሚያሻ በመሆኑ  ለጊዜው  በይደር  ልለፈውና ሃሳቤ ላካፍላችሁ ወዳቀድኩበት ጉዳይ ላይ ብቻ ላትኩር።

በ1987 የተፈጠረው ሁኔታ በአንዋር መስጊድ 29 ምዕመናን በ”መንግስት” የፀትታ ሀይሎች ሲገደሉ በሁኔታ በማሳበብ ወያኔ/ኢህአዴግ  የኢትዮጵያ እስልምና  ጉዳዬች ጠ/ምክር ቤት (መጅሊስ) በእጁ ከማስገባቱም ሌላ የተለያዩ የሙስልም በጎ አድራጎት ድርጅቶችን (NGO ) በመዝጋት የሙስልሙን የእምነት ነጻነትን የማፈኑን ተግባር ተያያዘው ።ቀደም ሲል በነበሩት 5 አመታት ለሙስሊሙ ማህበራሰብ የቆመ በመምሰል የሌላው ህብረተብ እምነት በተለይም የክርስትያኑን ለማዳከምና በጁ ላማስገባት ለጊዜ መግዢያነት ተጠቅሟል።

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህወሃት እስልምናን ለማዳከም የተያያዘው ጥረት  ሙሉ በሙሉ ባለማሳካቱ ተስፋ ባለመቁረጥ ክፍፍሉን በማጠናከር በሁለቱ ተላላቅ ሃይማኖቶች መሃል ጥርጣሬን ማጠናከር ነበር።ለዚህም ሙስሊሞችን “እስላማዊ መንግስት ሊመሰርቱ ነው” ክርስትያኑን ደግሞ “የድሮውን ስርአት ሊመልሱ ነው” ብሎ “ለተለያያዩ” አድማጮቹ (Audiences)  ማሰማት ነበር። ይህም ለተውሰነ ጊዜ የሰራለት መስሎ ታይቶት ነበር።  በእውናታ ላይ ያልተመሰረተ የፈጠራ ወሬ መልሶ ወረኛውን ስለሚጎዳ ወያኔ/ኢህአደግ የወረወረው ድንጋይ መልሶ መታው፤ እንግሊዞች (Pissing in the wind) እንደሚሉት፣ የበለጠ ጥላቻን አተረፈለት።

አምባገነኖች በህዝባቸው ጫንቃ ላይ በቆዮ ቁጥር የስልጣን ጥማት ስካራቸው እያየለ ይሄዳል በዚያው መጠን አሮጋንቲነታቸውና ለህዝባቸው ያላቸው ንቀት ይጨምራል።የሚገዙት ህዝብ እንዴት እንደሚበላ፤ እንዴት እንደሚናገርና ከማንጋር እንደሚናገር፤የትና ወዴት መሄድ እንዳለበት፤መንፈሳዊ እምነቱ ምን መሆን እንዳለበት በአጠቃላይ በዚች አለም ላይ እንዴት መኖር እንዳለበት ሊወስኑለት ይቃጣቸዋል።ወያኔ/ኢህአዴግም  ሁሉንም ለማድረግ ሞክሯል “እንደኛ ሃይማኖት አልባ መሆን ካልቻላችሁ ለኔ የሚስማማኝን ሃይማኖት(sect) ልጥመቃችሁ” ብሎ አህባሽ የተባለ ከእስልምና እምነት ፈር የለቀቀ  አምጥቶ በሙስሊሙ ህብረተሰብ ላይ በጉልበት ለመጫን ሞከረ።

ይህም ተገቢ አለምሆኑንና እሱ እራሱ የሚመጻደቅበት “ህገመንግስት” የመንግስት በሃይማኖት ጣልቃ መግባትን  የማይፈቅድ መሆኑን  የሙስሊሙ ህብርተሰብ ኮሚቴ በማቋቋም ችግሮቹን ለማስረዳት ቢሞክርም ህወሃት/ኢህአዴግ  የመናገርና የማዘዝ እንጂ የማዳመጥና”ህገመንግስቱ” የመተገበር በህሪዪ ያልተካነ “መንግስት” በመሆኑ የመንግስታዊ ህይማኖት ጫናውን ለማቆም ፍቃደኛ አልሆነም።

ሰላማዊ ትግልን መታገል ለሚሹ አርአያ ለመሆን በሚችል አለም አቀፍ ተቋማት እውቅናን ባገኘው  ሰላማዊና መራር በሆነው ትግልሙስሊሞች ህወሃት/ኢህአዴግ ድምጻቸውን እንዲሰማና ለጥያቄያቸው መልስ እንዲሰጥ ግፊት ለመፍጠር ቢሞክሩም መልሱ ህዝቡ በፊርማው የመረጣቸው የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የእስር ብቻ ሳይሆን የድብደባ፣ የግርፋት፣ የማዋረድ፣ የሰብዓዊ መብትም መገፈፍ ሰለባ ማድረግ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናንን ማሰር፣ መግረፍ፣ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ደግሞ ለሰደት መዳረግ ነበር። ከዚያም አልፎ ሰላማዊ ዜጎች በግፍ ጥይት እየተደበደቡ ለሞት መዳረጋቸው ሊካድ የማይችል የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡

ምንም እንኳን  ከህወሃት/ኢህአዴግ ካንጋሩ ፍርድ ቤት ፍትሃዊነት ባይጠበቅም የህብረተሰቡን ለመደለል የተደረጉ ሞከራዎች ውስጥ አንዱና ዋንኛው በራሱ ተለቪዢን ዘጋቢ ፊልሞችን አዘጋጅቶ ማሰራጨት ነበር፡፡እነዚህ “ዘጋቢ” ፊልሞች ማለትም “አሸባሪው አል ሸባብ ኢትዮጵያ ውስጥ የራሱን ሕዋስ (cell) ለመዘርጋት ጥረት እያደረገ ነው” ( አዲስ ግንባር )፤ “በኢትዮጵያ የተገኘው ሁለተኛው የአልቃይዳ ሕዋስ” ( ጂሃዳዊ ሃራካት )፤ “ሸህ ኑሩን ወሃቢስቶች  ገደሏቸው” (ሀዘን ለመድረስ … ጉዞ ወደ ደሴ )፤ ከእስልምና እና ከሽብርተኝነት ጋር ተያይዘው የቀረቡት የጥፋት መልዕክተኞችናየማንቂያ ደወል የህዝብ ገንዘብ አለአግባብ ከማባከን በስተቀር ለህወሃት/ኢህአዴግ ያተረፈለት ነገር የለም ይልቁንም የስርአቱ ማንነት የበለጠ የተጋለጠበት አጋጣሚ ነው ማለት ይቻላል። ከህወሃት/ኢህአዴግ ባዚሁ ሳያበቃ በትግሉ ላማዳከም   የይቅርታና የእርቅ ኮሞቴ “የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ” የሚባል አካል አዋቃሮ   በሙስሊማን ላይ  ከጅምሩ የከሸፈ”ተጸዕኖ” ለማሳደርም ሞክሯል።

በርግጥ የስርአቱ ሰለባ የሆንነው እኛ ሙሊሞች ብቻ ሳንሆን በዚያች ምድር የሚኖር  ክርስትያኑም፤አይሁዲውም፤ዋቄፈቻውም፤ኢ-አማኑ፤ ኦሮሞውም፤ አማራውም፤ ጉራጌውም፤ ኦጋዴኒውም፤ ትግሬውም፤ ከምባታውም፤ ሃዲያውም፤ ወላይታውም…… ነው። ለሙስሊሙም ሆነ ለሌላው መብት መከበር አንድ ላይ ሆኖ ለሥርአት ለውጥ መታገል ወሳኝ ነው።የእያንዳንዳችን ነጻነት ሲከበር እንደሙስሊም ወይም እንደሌላው የህበረተሰብ ክፍል አባልነታችን ልዩነታችን እንደተጠበቀ ሆኖ  የጋራነጻነታችን ይከበራል።ለነጻነት የሚደረገውን ትግል የፖእቲካ ሥራ ነው ብለን ካልን፤ከፖሊቲካ ነጻ የሆነ ግለሰብ ወይም ማህበረስብ አለ ለማለት ባያስደፍርም አላህ (ሱ.ወ ) የሰጠንን አንጻራዊ ነጻነትን የነፈገንን አካል መታገል ሃይማኖታችን (42:39) የሚፈቅድልን ይመስልኛል።የ”ድምጻችን የሰማ” እንቅስቃሴም የመብትና የነጻነት ጥያቄ ነውና። የህዝብን ድምጽ የማይሰማ አካል ካለ እንዲሰማ መገደድ ይኖርበታል።አሊያም ቦታውን ለቆ ህዝብ በሚመርጠው መተካት አለበት።አንድ የመንግስት አካል የሚመረጠው ህዝቡን ሊያገልግል እንጂ በህዝቡ አንዲገለገል ከዚያም አልፎ መብቱንና ነጻነቱን እንዲነፍገው አይደለም።በአጭሩ መንግስት የህዝብ ተቀጣሪ አገልጋይ ደሞዝተኛ ነው።

አንድ ሙስልም የመጀምሪያ ግዴታው ከሁሉም በላይ  ሃይማኖቱ (ዲኑ)የሚያዘውን ተግባራዊ  ማድረግ ነው።በመሆኑም ከሌሎች ጋር አብሮ ለመስራት በጋራ ሊተገበሩ የሚችሉ ጉዳዮች ከዚህ ከየ እለቱ የሃይማኖት (ዲን) ግዴእታዎች ጋር የሚጋጩ ከሆነ ችግሮች ሊፈጠሩ ይችላሉ።ከነዚህም ከብዙ በጥቂቱ፤የየ እለት የሰላት ሰአታት፤የአርብ (ጁምአሰላት)፤የረማዳን ወር  ጾም ፤የወንዶችና ሴቶች አንድ ላይ  መሰባሰብና የመሳሰሉት ናቸው።የሁሉንም የተለያዩ እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያንን ተሳትፎ ለማጎልበት የጋራ መድረኮች ከቤተ እምነቶች ሰበካ ቢፀዱ መልካም ነው የሚሉም አሉ።ስብስቦቻችን በነሱ ባይባረኩ ምንም የሚጎላቸው ነገር አይኖርም። የእምነት አባቶች ከምዕመናን ጋር በየሚሰበሰቡበት ስፍራና ቤተኢምነቶች ለህዝባችን የሚያደርጉት ፀሎት በቂ ነው ይላሉ።

እነዚህን አንደየ ሁኔታቸው ማስተናገድ (Accommodate) የሚቻል የመስለኛል።ከዚህ ውጭ መሰራታዊ የሆኑና ለአብሮ መስራት እንቅፋት የሆናሉ ተብለው የሚታሰቡ ያሉ አይመስለኝም።ካሉ ግን ፊትለፊት መነጋገር መፍትሄ ለማግኘት የበጃል ብዬ አምናለሁ።ይህ ካልሆነ ግን እርስበርሳችን እየተጠራጠርን ሁላችንም ነጻነታችንን እንደ ተነፈግን ኖረን ለልጆቻችን “ባርነትን” አስረክበን እናልፋለን።ይህ ደግሞ የማንንም አባት ወይም እናት ፍላጎት አለመሆኑ ግልጽ ነው።

እስልምና አብሮመስራትን ነው የሚያስተምረን።የሃገርችንን ሁኔታ ስንመልከት ዘርና ጾታን ሳይለይ ምስራቅ ያለው ለምዕራቡ፤ ደቡብ ያለው ለሰሜኑ፤እንዲሁም ለመሃል አገሩ ሙስሊምና ሌሎች የሃገሩ ህዝቦች መብት መከበር ተቆርቋሪና ለተግባራዊነቱ መታገል ይኖርበታል።አንዱ የህብረተሰብ ክፍል ነጻነት ከተነፈገ   የሁሉም ነጻነት እንደተነፈገ ይቆጠራል።በአንድ ሃገር ያሉ ህዝቦች የሚኖራቸው ነጻነት እኩል መሆን የኖርበታል።ከታሪክ እንደምንረዳው እስልምና የሚያስተምረን ይህንኑ ነው።

ይህ  ከሆነ ታዲያ ለነፃነት በሚደረገው ትግል እኛ  ሙስልማን እያደረግን ያለው አስተዋጽኦ በቂ ነው ማለት ይቻላል? ይህንን ጥያቄ የማቀርበው ለራሴ ጭምር ነው።

ኢትዮጵያ እስልምናን ከተቀበለች ለአስራ አራት ምዕተ-አመት ቢሆንም የቀድሞ ገዢዎቻችን 30% (በዚህ ቁጥር የሚከራከሩም አሉ) ሙስልም ወደ ጎን በመተው ኢትዮጵያ የክርስትያን ደሴት ናት ይሉ ነበር ዛሬ ግን ወያኔ ህንን ቀይሯል ብለን ከሆነ ተሳስተናል። ይልቁንስ ሃይማቶት የለሹ ወያኔ ሁሉም ሃይማኖቶች የተደፈጠጡባት የመከራና የአፈና ደሴት ነው ያረጋት።እርግጥ እድሜ ለቴክኖሎጂ ወጣቱ ትውልድ የእስልምና መጽሃፎችን በሃገራዊ ቋንቋ በቀላሉ ማግኘት በመቻሉ እራሱ ለማስተማር ችሏል።ወያኔ ቀደም ሲል እንደተገለጸው ለራሱ ጊዜ መግዢያ  እስከ 1987 ድረስ ለቀቅ ባደረገው አንጻራዊ ነፃነት መስድጂዶችና የመማሪያ ተቋማት ሊገነቡ ቢችሉም በኋላ ላይ  ግን በመጅሊሱ አማካይነት አህባሾች እንዲቆጣጠሯቸው ተደርጓል።ይህ ማለት ደግሞ ሁሉም በወየኔ ቁጥጥር ሥር  ነው።

በኢትዮጵያ በእስልምና ተቋም (Institution) ደረጃ ባይሆንም በመካሄድ ላይ ባለው የነፃነት ትግል ውስጥ በግልም ሆነ ሃይማኖታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ በመሳተፍ ላይ ያሉ ብዙ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን  አሉ ።ለዚህም በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች የተደረጉና እየተደረጉ ያሉ ትግሎች በቂ ምሳሌዎች ናቸው።

መሪዎች በግልም ሆነ በስብስብ (Congregational) ሌላው ቢቀር እየተፈጸመ ያለውን ግፍና ሰቆቃ በማውገዝ ረገድ በሀገር ውስጥ ባለው የወየኔ/ኢህአዴግ ጫና ከባድ ቢሆንም ያ ስጋት በሌለበት በውጭ አለም በምንኖር በጋራም ሆነ በግል ለነፃነትና ለፍትህ ለሚደረገው ትግል ተሳትፎአችን በጣም አነስተኛ ነው ማለት ይቻላል።ምክንያቶቹ ግን ከመላምት ባሻገር (በግልጽ ሥርአቱን የሚደግፉ እንዳሉ ሆነው) ይህ ነው ማለት ያስቸግራል።

ከመላምቶቹ መሃከል የተሻለች የሁሉም መብት የተከበረባት ኢትዮጵያን ለመገምባት በመታገል ላይ ያሉትን ሃይሎች በቅርበት ካለማወቅ የተነሳ በጥርጣሬ አይን የማየት፤የወያኔን መሰሪነት ካለመረዳትና ከትናንቱ መገፋት (marginalization) በመነሳት ከልብ ስርአቱ እስልምና የቆመ አድርጎ መውሰድ፤”የባሰ ይመጣ ይሁን?” ጥርጣሬ፤”እኔ ምናገባኝ ድሮም አልነበርኩበትም”፤ እያወቁ ለጊዜያዊ ጥቅም መሸነፍን…….የመሳሉትን ያጠቃልላል።

ሃይማኖታችን ለሃቅና ለፍትህ እንድንቆም ያስገድደናል።በጎሳና በነገድ ሳይሆን እንደ ህዝብ  አንድ ላይ ሆነን በደልን እንድናወግዝና ከተበዳዮች ጎን እንዲንቆም ያዘናል።

አላህ (ሱ.ወ) የሰጠንን አንፃራዊ ነፃነት የሱ ፍጡር በሆኑት አምባገነኖች ተነጥቀን ሲያዋክቡን፤ሲያሰድዱን፤ሲያስሩን፤ሲያሰቃዮንና ሲገሉን መሪዎቻችን ምንም እንዳልተፈጠረ ፈታቸውን ወደ ሌላ አቅጣጫ በማዞር ዝምታን መምረጣቸውና አዳንዳንዶቹም ከነዚህ አምባገነኖች ጎን  መሰላፋቸው ተገቢ አይመስለኝም።

የዛሬ 77  አመት የጣሊያ ወራሪዎች መጠቀሚያ እንዳደረጉን ህወሃት/ኢህአዴግ እንዲደግም መፍቀድ የለብንም።የግለሰቦች ነፃነት ሲረጋገጥ የሁላችንም  ነፃነት እንደ ግለሰብም ሆነ አንደ ሰብሰብ ሰለሚረጋገጥ የነፃነት ትግሉ የሙስሊሞችም ነው።ዛሬ በትግሉ መሳተፍ ስንችል ነው ነግ “ይህ የዛሬ ነፃነት እኔም ትናንት የታገልኩለትና ወንድሞቼ፤ እህቶቼ ፤ አባቴና እናቴ መስዋእትነት የከፈሉበት ነው ” ብለን በሙሉ ልብ መናገርና የነፃነቱ ባለቤትነት ሊሰማን የሚችለው።

ትግሉን መቀላቀል የሚንችለው እኛ ወደ ትግሉ በመሄድ እንጂ ብቻ ነው፤እኛ ወደ ትግሉ ካልሄድን ችግሩ ወደኛ መምጣቱ አይቀሬ ነውና።ቀደም ሲል የተጠቀሱት የሃይማኖታችን የዕለት ተዕለት ተግባራት (ዕባዳ) ጋር የተያያዙ የጊዜና ቦታ ጉዳዮችን ማስተናገድ የሚቻል ከሆነ ከዚህ ውጭ ያሉ እንዳንቀራረብ የሚያደርጉን ጉዳዮች ካሉም በግልፅ በመወያየት መፍትሄ ማግኘት ይቻላል።ከዛም ባለፈ ባጋራ ሊያስማሙን በሚችሉ ጉዳዮች ላይ አብሮ በመስራት ለነፃነት መብቃት የሚቻል ይመስለኛል።

ሓይማኖታችንን ፈጣሪያችን ባዘዘን መልኩ በትክክል መተግበር ያሚቻለው ነፃነት ሲኖር ነው።ነፃነትና ሀገር ደግሞ ተለያይተው አይታዩም፤አንዱ ከሌለ ሌላኛው  ትርጉም ያጣልና።

ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉት የተለያዩ ሃይማኖቶች በተለይም በክርስትናና በእስልምና እምነት ተከታዮች መሃከል በጥርጠሬ መተያየቱ ሊኖር ይችላል።እርግጥ በተለያዩ ዘመናት በሌላው የዓለም ክፍሎች ከታዮትና እየታዩ ካሉት የሃይማኖት ግጭቶች  የራሱ በሆኑ ምክንያቶች  በባህሪየም ሆነ በይዘቱ የተለየ ቢሆንም ግጭቶችም ሆኑ በጥርጣሬ መተያየቱ የነበረና ዛሬም ያለ መሆኑን መካድ አይቻልም።ይህም ዝምብሎ በአንድ ጀምበር የተከሰተ ሳይሆን ለብዙ ዘመናት አብረን የኖርን ቢሆንም በዚያው መጠን በተለያዩ ጊዚያት በሃገሩቷ ውስጥ የተነሱት ገዚዎች ለስልጣን መቆናጠጫና ስልጣኑ ላይ ለመቆያ ሁለቱን ታላልቅ ሃይማኖቶችን በመሳሪያነት በመጠቀማቸው እርስ በርስ ጦርነት መሳበቅ የተደረሰባቸው ጊዚያት መኖራቸውና የበላይነትን የተቀዳጀው ክፍል በዚያው ለመቀጠል ያደረጋቸው  ጥረት የወለደው የማግለልናን የመገለል ሂደቶች የጥርጣሬ ምንጭ ሊሆኑ ይችላሉ።

ወያኔ የኢትዮጵያን ሙስሊሞች  ፅንፈኛች ፤መሪዎችን ደግሞ (እጅ የሰጡትን ሳይጨምር) አሸባሪዎች እንደሚላቸው ሳይሆን፤በተለይም የወጣቱ ትውልድ መሰረታዊ ባልሆኑ (ሰለፊ፤ሱኒ፤ተብሊጊ… )ላይ ከማተኮር ቁርአንና የነቢዩን (ሠ.አ.ወ) ሱናን በመከተል ትክክለኛና ጥሩ ሙስሊም መሆንን የመረጠ በመሆኑ በጥቅሉ መጠርጠር ተገቢ አይሆንም።

እርግጥ በማንኛውም ሃይማኖት ሆነ የፖለቲካ እምነት ውስጥ ካለማወቅም ሆነ አውቀው ለተለየ አላማ  ከትክክላኛው መንገድ ወጣ ያለ የፅንፈኝነትን አቋም የሚያቀነቅኑ አንዳሉ ሁሉ በሙስሊሙም ህብረተብ ከላይ ከተጠቀሰው ባልተለየ ምክንያት መኖራቸው መካድ አይቻለም።ሆኖም እነዚህቡድኖች ጥቂቶች በመሆናቸው የስጋትና የጥሪጣሪ ምንጭ መሆን የለባቸውም።እንዚህንም የመወጋት የሙስሊሙ ህብረተሰብ መሰረታዊ ተግባር ነው።

የመልእክቴ መሰርታዊ አላማ ችግሮች ካሉ ለችግሮቹ መፍትሄ ለመሻት እንዲቻል ለውይይት ለመጋበዝ እንጂ  ስለ እስልማና እውቀት አለኝ ብዬ በድፍረት ያልቀረብኩ መሆኔና ተሳስቼም ከሆነ ፈጣሪዬን ይቅርታ እየለመንኩ ለመታረምም ዝግጁ መሆኔን ላንባቢያንም ለመግለፅ እወዳለሁ።

ምንም እንኳን እንደ ህወሃት  ላሉት (የዶክተር መራራ ቃል ልዋስና) እነሱ ከጫካ ቢወጡም ጫካ ከነሱ ውስጥ ላልወጣ ቡድኖች የማይሰራ ቢሆንም  ዛሬ አለም በደረሰበት ዘመን መነጋገር፤መወያየትና በሰጥቶ መቀበል መርህ ላይ የተመረኮዘ የችግር አፍታት ዘይቤ ከፍተኛ ሥፍራ አለው ብዬ ስለማምንም ጭምር ነው።እንኳንስ ሃገርን የሚያህል ግዙፍና የህልውና ጉዳይ ቀርቶ በቤተሰብ መሃከል  ለሚፈጠረው ችግር እንኳን በመነጋገርና በጋራ በመስራት ነው መፍትሄ የሚገኘው።በተናጠል ለጠላት ከመመቸት በስተቀር  የትም አንደርስም።

አላህ ወደተቃናው መንገድ ይምራን።

አላህ ኢትዮጵያን ከነ ህዝቦቿ ይጠብቃት።አሚን።

ባህር ከማል

የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሺነር በአርባ ሀገሮች የመብት ይዞታን በተመለከተ መግለጫ ሰጡ – ቪኦኤ

$
0
0

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሺነር ዘይድ ራአድ አል ሁሴን

ጠቅላላው የሰብዓዊ መብቶች አጠባበቅ ሥርዓት በሽብርተኛነት፣ በመጤ ጠሎችና ዝናን ናፋቂ በሆኑ ፖለቲከኞች፣ ከፍተኛ ጥቃት ሥር ወድቋል ሲሉ፣ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳዮች ከፍተኛ ኮሚሽነር ዘይድ ራአድ አል ሁሴን አስገንዝበዋል።

ጠቅላላው የሰብዓዊ መብቶች አጠባበቅ ሥርዓት በሽብርተኛነት፣ በመጤ ጠሎችና ዝናን ናፋቂ በሆኑ ፖለቲከኞች፣ ከፍተኛ ጥቃት ሥር ወድቋል ሲሉ፣ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳዮች ከፍተኛ ኮሚሽነር ዘይድ ራአድ አል ሁሴን አስገንዝበዋል።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሺነር ዘይድ ራአድ አል ሁሴን በሪፖርታቸው በአሁኑ ወቅት ከአርባ ሀገሮች በላይ የሚታየውን የመብት ይዞታ ዘርዝረዋል፡፡

ከእነዚህ መካከል አራቱን ሀገሮች ጋምቢያ፣ ኡዝቤክስታን፣ ቱኒዚያ እና ግሪክን ጠቅሰዋል፡፡

ከፍተኛ ኮሚሸነሩ ዓመታዊ ሪፖርታችውን ካቀረቡበት የመሥሪያ ቤቱ ጠቅላይ ቢሮ ከሚገኝበት ጄኔቫ ሊሳ ሽላይን ያጠናቀረችውን ዘገባ አዲሱ አበበ ያቀርበዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

if(typeof(jQuery)==”function”){(function($){$.fn.fitVids=function(){}})(jQuery)};jwplayer(‘jwplayer-1’).setup({“image”:”http://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2017/03/368C36C8-41DF-4311-8932-8F6069CB97D9_w1023_r1_s.jpg”,”file”:”http://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2017/03/56944c55-15c3-443f-95a6-64079613016e_hq.mp3″});

 

“የሀገሬ ህዝብ ይፍረደኝ” የኑሃሚን እናት – ቪኦኤ

$
0
0

ዕለቱ ማክሰኞ ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ ነበር ፤ ሜክሲኮ ዲ’አፍሪክ ሆቴል አካባቢ በርካታ ሰዎች ታክሲ የሚጠብቁበት ግርግር የበዛበት ቦታ። የ16 አመቷ ኑሃሚን ጥላሁን በየዕለቱ እንደምታደርገው ከትምህርት ቤት ከመጣችበት ታክሲ ወርዳ ወደ ቤቷ በእግሯ እያቀናች ነበር። ጥቂት እርምጃዎች እንደተራመደች ግን ያልጠበቀችው አደጋ ገጠማት።

 

የኢትዮጵያ ሴቶች ፖለቲካዊ ተሳትፎ ትናንትና ዛሬ – ፋሲካ ገ/ጻዲቅ ወ/ሰንበት

$
0
0
ሰላም ክቡራትና ክቡራን ኢትዮጵያዊያን ወገኖቼ፤ በዛሬው ዕለት የምናገርበት ርእስ ስለሴቶች በብዛት ወደ ነጻነት ትግሉ ጎራ አለመቀላቀል ቢሆንም እግረመንገዴን በወንዶች የተመላው እና የሴት ያለህ የሚለው የትግል ጉዞአችን ለምን እንደሚጠየቀው ጾታዊ ስብጥር የለውም የሚለውን ሃሳቤን አካፍላችሁዋለሁ። እንደመንደመሪያ፤ የሴቶች ሚና በሃገራችን የታሪክ ሂደት ውስጥ ምን ይመስል እንደነበረ ጥቂት እውነታዎችን፤ እንዲሁም ባለፉት 25 ዓመታት በተደራጁትና ህወሃት መራሹን ስርዓት በሚቃወሙት ድርጅቶች ውስጥ፡ የሴቶች ተሳትፎ ለምን ሊበረታታ እንዳልቻለ የበኩሌን እይታ እገልጻለሁ። ዓላማዬም ካለፉት ድክመትና ጥንካሬዎቻችንን ተምረን ነገን ብሩህ ለማድረግ፤ ፍትህ እኩልነት፤ ሰብዓዊትና የዜግነት መብት የተከበረባት ኢትዮጵያን፡ እኔ እንደማልማት እንድታልሟት ራዕዬን ማካፈል ነው።

ሴት ልጅ በጡንቻ ካልሆነ በቀር በማንኛውም ነገር ከወንድ ልጅ አታንስም፤ እሱንም ስፖርት ካዘወተረች ትደርስበታለች። ሴት ልጅ ተፈጥሮዋ ሆኖ ሊሆን ይችላል፡ ትራራለች፤ ትሳሳለች፤ ላመነበችበት ዓላማ መስዋዕትነት ትከፍላለች፤ እጅግ ትታገሳለች፤ ሲበቃት ደግሞ አራስ ነብርን ታስንቃለች። ሴት ልጅ እቤት የምትውለው ሳታውቅ ቀርታ፤ ዝም የምትለው ፈርታ፤ አይዞህ የምትለው ሳይከፋት ቀርታ፤ ዝቅ የምትለው መከበር ጠልታ አይደለም። ኑሮዋን፤ ልጆችዋን፤ ዓላማዋን፤ ከፍ ሲልም የማህበረሰቧን ሰላምና ደህንነት ቅድሚያ ሰጥታ እንጂ። በአንድ ወቅት በካናዳ የቀድሞዋ የሚሲሳጋ ከንቲባ ሄዘር ማካሊዮን፡ በቅጽል ስማቸው ኸሪኬን ሄዘር፤ 12 ጊዜ በህዝብ ተመርጠውና ለ36 ዓመታት በከንቲባነት አገልግለው በ93 አመታቸው በበቃኝ ለምርጫ መወዳደር ከማቆማቸው በፊት CBC ሬድዮ ላይ ቀርበው በስራ ዘመናቸው ከወንዶች በኩል ምን ያህል ፈተና እንደደረሰባቸው ሲጠየቁ የሰጡት መልስ፤ የሳቸውን የሃላፊነት ተግባር ለመቀበል የሚያንገራግሩት ከወንዶች ይልቅ ብዙ ጊዜ ሴቶች እንደነበሩ ተናግረው ነበር። እምነታችንም፤ ትምህርታችንም፤ ማህበረሰባችንም ስለ ሴት ልጅ ክብር፤ እኩልነትና አስተዋጽኦ እዚህም እዚያም ቢጠቃቅስም፡ በተግባር ግን ሴት ከወንድ እኩል መሰለፍ መቻሏን ለመቀበል፡ ዲሞክራቲክ የሚባለው ካናዳ ውስጥ እንኳን መቸገራቸውን የኸሪኬን ሄዘር ተሞክሮ አንድ ምሳሌ ነው።

ወደ ሃገራችን ጉዳይ ስንመለስ፤ በኮ/ል አሌኸንድሮ ዴል ባዬ ተጽፎ በ ዶ/ር ተስፋዬ መኮንን ባይለየኝ በተተረጎመው ቀይ አንበሳ በሚባለው መጽሃፍ ውስጥ (1992፤ ገጽ 183፤84) ጸሃፊው የአለማየሁ ባሪያ ወይም “ማሚቴ” ብሎ እንደሚጠራት የትግራይ ሴት፤ በታሪካችን ሂደት ለሃገራቸው የተለያዩ አስተዋጽኦዎችን ያበረከቱ እንዲሁም ሃገራቸውን ከጠላት ወረራ ለመታደግ በተደረጉ የጦርሜዳ ውሎዎች የተሳተፉ ነገር ግን ስማቸውን እንኳ በውል የማናውቃቸው ብዙ ባለውለታ ሴቶች ነበሯት፤ ዛሬም ከመጋረጃው ጀርባ ብዙ ስራዎችን እንደሚሰሩ ጥርጥር የለኝም።

በአንጻሩ፤ ገድላቸው ከተከተበላቸው ነገስታት መሃከል፡ በቅድሚያ ንግስት እሌኒን ለማንሳት እወዳለሁ። ንግስት እሌኒ በፖለቲካና ዲፕሎማቲክ ብስለታቸው የሚደነቁ፡ በ16ኛው ክ/ዘመን ሊፈቱ የሞከሩት ችግር ዛሬም ያልተፈታ፡ የምስራቅ አፍሪካንና የመካከለኛው ምስራቅን አካባቢያዊ ቅራኔ እንዲሁም የአውሮፓዊያንን አሰላለፍ ያስተዋሉና የአለምአቀፍ ግንኙነት አካሄዱ ጠንቅቆ የገባቸው ሴት ነበሩ። ንግስት እሌኒ አባታቸው ገራድ አህመድ የተባሉ የደዋሮ ሰው ነበሩ። በዚያን ጊዜ ደዋሮ ተብሎ የሚጠራው ከሸዋ በስተምስራቅና በስተሰሜን፤ የዛሬውን አዳማን ጨምሮ፤ በስተምስራቅ ከአዳል ሡልጣናዊ ግዛት በኩል እያጠቃለለ የሚዋሰን የነበረው ስፍራ ሲሆን፤ አብዛኛው ህብረተሰብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነበረ ይሉናል አቶ ይልማ ደሬሳ (የኢትዮጵያ ታሪክ በአስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን 1959፤ ገጽ 13፤14)።

እሌኒ አጼ በዕደ ማሪያምን አግብተው ንግስት የሆኑ ሲሆን፡ ባለቤታችው በሞት ከተለዩዋቸው በኋላ፡ ለዐጼ እስክንድርና አጼ ያዕቆብ በእንደራሴነት፤ ልጃቸው ዳግማዊ ዐምደ ጺዮን ነግሶ ህይወቱ ሲያልፍ ደግሞ፡ ለልጃቸው አጎት ለዐጼ ናዖድ የበላይ አማካሪ ሆነው በወቅቱ በቱርኮች የተቃጣውንና ለኢትዮጵያ ህልውና አስጊ የነበረውን ሁኔታ፡ ፖርቹጋሎችን እርዳታ በመጠየቅ፤ ከአካባቢያችን አረብ ሃገሮች ጋር ጥሩ ጉርብትና እንዲኖር በመስራት፤ እንዲሁም ከአዳል ሱልጣኔቶችና ከሌሎችም አሚሮች ጋር ቤተሰባዊ ዝምድና ስለነበራቸው፡ ከማዕከላዊ መንግስቱ ጋር የአስታራቂነትና የዲፕሎማቲክ ሚና በመጫወት፤ ለ400 አመታት የቆየን ግጭት ወደ ሰላማዊ ግንኙነት ለመቀየር አስችለዋል (ይልማ ደሬሳ የኢትዮጵያ ታሪክ በአስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን 1959፤ ገጽ 18፤19፤21፤24፤25)። ንግስት እሌኒ የሃይማኖት ልዩነት ሳይበግራቸው እስላሙን፤ ኦርቶዶክስና ካቶሊክ ክርስቲያኖችን፤ ሃገራቸውን ከጎረቤት አፍሪካ ሃገሮችና ከአረቦች እንዲሁም ከአውሮፓዊያንን ጋር አግባብተው መስራት የቻሉ ተራማጅና፤ አርቆ አሳቢ ሴት ነበሩ።

በመቀጠል፡ የዐጼ ባካፋ ባለቤት የነበሩት የቋራ ተወላጅዋ እቴጌ ምንትዋብን ብንወስድ፡ በጣና ደሴት ላይ ዛሬ የቱሪስት መስህብ የሆኑትን፡ የወንዶች ብቻ የሆነውን ክብራን ገብርኤልን ጨምሮ፤ ትልልቅ አድባራትና ገዳማትን ያሰሩ ሲሆን፤ በልጃቸው በዐጼ እያሱ ብርሀን ሰገድ ዘመንም በሞግዚትነት ነግሰው ትምህርት እንዲስፋፋ ለማድረግ ከአረቢኛ ወደ ግእዝ ያስተረጎሟቸውን መጽሃፍት፡ ተማሪዎች ከሸዋ፤ ከትግሬና ከጎንደር ወደ ደሴቷ መጥተው ለቀለባቸው ሳያስቡ ለዓመታት መጽሃፍቶቹን እንዲያጠኑ አስችለዋል (ተክለጻዲቅ መኩሪያ የኢትዮጵያ ታሪክ ከዐጼ ልብነድንግል እስከ ዐጼ ቴዎድሮስ 1961፤ 4ኛ ዕትም ገጽ 256 እና 281)።

በሌላ በኩል፤ እቴጌ ጣይቱም በበኩላቸው ከአድዋ ጦርነት በፊት ኮንት አንቶኔሊን “ማን የሚደነግጥልህ አለ ጦርነቱን በፈቀድክ ጊዜ አድርገው እኛም ከዛው እንቆይሃለን” ብለው በመለሱለት መልስና በሌሎች ቆራጥና ብልህ ምክራቸው የበለጠ የሚወደሱ ቢሆንም፡ አፈወርቅ ገብረየሱስ እንደጻፉት፡ ኮንት አንቶኔሊ የውጫሌ ውል ተርጓሚውን ግራዝማች ዮሴፍን እፊታቸው መሳደቡን በመቃወም፤ ስህተት ካለ የመገሰጽ መብት የኢትዮጵያዊያን ብቻ መሆኑን ማስገንዘባቸው ስለዜጎች መብት ያላቸውን የህግ ግንዛቤ ሲያሳይ፤ በአንጻሩ ደግሞ፡ ዛሬ በሃገራችን ለዜጎች መብት የሚቆም መንግስት አለመኖሩ ምን ያህል ጉዞአችን የኋልዮሽ እየሄደ እንደሆነ ያመለክተናል (አጤ ሚኒሊክ 1901፤ገጽ 76፤77)።

በተጨማሪም፤ ምንም እንኳ ከ1909-1922 በንግስና ቢቆዩም፡ እምብዛም ታሪካቸው ሲነገር የማንሰማው ንግስተ ነገስታት ዘውዲቱ፤ በ7 ዓመታቸው ለ12 ዓመቱ የአጼ ዮሃንስ ልጅ፡ ራስ አርአያ ዮሃንስ፡ ለሃገር አንድነትና ደህንነት ሲባል ልጅነታቸው መስዋዕት ተደርጎ ነበር የተዳሩት። በንግስናቸውም ዘመን ዛሬ ለተለያዩ የእምነት ተከታዮች አገልግሎት በቀብር ስፍራነቱ የሚታወቀውን የአዲስ አበባውን ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያንን ጨምሮ እጅግ በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን አሳንጸዋል። እንዲሁም ዘውዲቱ ሆስፒታልን የሴቶች ማዋለጃ አገልግሎት እንዲሰጥ ያሰሩትም እኒህ ንግስት ነበሩ። በዘመኑ የፊታውራሪ ሃ/ጊዮርጊስና የአልጋ ወራሽ ወገን እየተባባለ የነበረውን መካረር ሰላም ወዳዷ ንግስት ዘውዲቱ፡ በማስማማትና በታላቅ ትእግስት ያበርዱት እንደ ነበረ የዓይን ምስክርነት ቃላቸውን ደጃዝማች ከበደ ተሰማ በጽሁፍ አኑረዋል (የታሪክ ማስታወሻ 1962 ገጽ 31፤36፤39፤43)።

ሌላዋና፡ የሃገራችን የመጨረሻዋ ንግስት ሆነው ያለፉት እቴጌ መነን፤ በየካቲት 3 1938፤ የእቴጌ መነን የሴቶች ትምህርት ቤትን የመሰረት ድንጋይ በማኖር፡ የሃገራችን ሴቶች ዘመናዊ ትምህርትን እንድንቀስም የሚያበረታታ መሰረት ጥለዋል። በ1942 ደግሞ 14 ቅዱሳን መጽሃፍት እንዲተረጎሙ እና 3800 ቅጂዎች እንዲሸጡ አርገው $12 ሺህ ብር፡ አቅም ለሌላቸው ህጻናት መማሪያ እንዲሆን ለቅዱስ ጳውሎስ የስዋስው
ትምህርት ቤት አበርክተዋል። እቴጌ መነን በሃገራችን የመጀመሪያው የህክምና ትምህርት ቤት፤ ልእልት ጸሃይ ሆስፒታል እንዲሰራ፡ የእናታቸውን ርስት በስጦታ የሰጡ ሲሆን፤ ልጃቸው ልእልት ጸሃይ እንግሊዝ ሃገር የነርስነት ትምህርት ሲከታተሉ የተዋወቋቸው የኢትዮጵያ ባለውለታ ወ/ሮ ሲልቪያ ፓንክረስትም ለሆስፒታሉ ገንዘብ በማሰባሰብ ተባብረዋቸው፤ የእቴጌዋ የበጎ አድራጎት ተግባር እንደታቀደው ሊከናወን ችሏል። በነገራችን ላይ የእቴጌ መነን እናት፡ የወ/ሮ ስህን አባት፡ ንጉስ ሚካኤል፤ የነቢዩ መሃመድ 5ኛ ትውልድ ከሆኑት ከአብዱላህ ቢን ሙሃመድ አል ባኪር የዘር ሃረጋቸውን እንደሚስቡ Anjahli Parnell ጽፈዋል (The Biography of Empress Menen Asfaw: The Mother of the Ethiopian Nation 2011፤ ገጽ 101፤105፤174)።

ሌላዋ ተደናቂ ሴት ወ/ሮ ሸዋረገድ ገድሌ ሲሆኑ፡ ወ/ሮዋ የጣሊያን ወታደሮችን ዕቅድ ለአርበኞች በማድረስ፤ የከተማ ውስጥ አርበኞችን በማስተባበር፤ ለአርበኞች ጠመንጃ፤ ጥይትና ስንቅ በማቀበል የታገሉ ስመ ጥር አርበኛ ሴት መሆናቸውን ጀ/ራል ጃጋማ ኬሎ መስክረውላቸዋል። ወ/ሮ ሸዋረገድ ገድሌ፡ በወቅቱ የሚናቀውን የንግድ ስራ በትጋት በማከናወን፡ የዘይት ማምረቻ፤ የአልኮል ፋብሪካ፤ የእንጨት ስራ፤ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርት በመሳሰሉ የንግድ ስራዎች ላይ በግላቸውም ሆነ ከግሪኮች ጋር በሽርክና በመስራት፡ ስራ ፈጣሪ እና ባለሃብት ሴት መሆናቸውን ደራሲ ሺበሺ ለማ ጽፈዋል (ሸዋረገድ ገድሌ የአኩሪ ገድላት ባለቤት የህይወት ታሪክ 1878-1942 2007፤ ገጽ 200፤201፤206፤207)።

እነዚህ የጠቀስኳቸው መልካም ስራን ሰርተው ያለፉ ኢትዮጵያዊያን ሴቶች ታሪክ እንደሚያሳየንም ሆነ፤ የሰላም ጥናት አባት ተብለው የሚወደሱት ኖርዌጂያዊው ዮሃን ገልታንግ እንደጻፉት፤ አርክቴክቶችና ኢንጅነሮች በትምህርትና በስልጠና የሚያገኙትን፡ ልዩነቶችን አቻችሎ፤ ቅራኔዎችን ፈቶ የማለፍን ጥበብ፤ ሴቶች ግን በተፈጥሮ እንደታደሉት ጽፈዋል (Peace, and Development: Theories and Methodologies 2015፤ ገጽ 31፤ 32) ። የቀደምት ሴቶች ኢትዮጵያዊያንን ገድል የዘረዘርኩት ለመመጻደቅ፤ ለመበላለጥና ከወንዶች ጋር ለመፎካከር ሳይሆን፡ የእኛም ሆኑ የሌሎች ዓለም ማህበረሰቦች፡ ይህንን የሴትን ልጅ ልዩ ክህሎትና ተፈጥሮ፡ የተሻለ፤ መፈቃቀርና መከባበር የነገሰባት ሰላማዊ ዓለም ለመገንባት አለመጠቀማችን፡ “ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር ይቆረጣል” የሚለውን ብሂልን እንዲያስታውሰን ብዬ ነው።

ወደ ዘመናችን የሴቶች ፖለቲካዊ ተሳትፎ ስንመጣ ደግሞ፡ ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ የኢህአዲግ ቀይ እስኪብርቶ በሚል ርዕስ በ2004 ዓም ባሳተመችው መጽሃፍ፤ የሴቶች ተሳትፎ በሃገራችን የፖለቲካ ማህበረሰብ ዘንድ፡ በህወሃትም ሆነ በተቃዋሚዎች መንደር ባዶ መሆኑን ጠቁማለች። ከዚህ በተለየ መልኩ የቀድሞው አንድነት ፓርቲ ብቻ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን ለፓርቲ ሊቀመንበርነት በመምረጥ ፈር ቀዳጅ ቢሆንም፤ ይኸው ፓርቲ በወቅቱ 20 ከሚሆኑት የስራ አመራሮቹ መሃል 2ቱ ብቻ ሴቶች እንደደሆኑ ጽፋለች (ገጽ 201፤202)። በበኩሌ የወያኔን ስርዓት መብት በመንፈግ የሚያክለው ባይኖርም፡ “የድርጅቱን” ሚስት፤ አዜብ መስፍንን ግን፡ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እንድትነግስ ለክፉ ስራም ቢሆን ዕድል መስጠቱ፡ ከተቃዋሚዎች አሰላለፍ እጅግ በጥቂቱም ቢሆን ለየት ያደርገዋል እላለሁ። የኢትዮጵያን ፖለቲካ ነፍስ ካወቅኩባቸው አመታት ጀምሮ በርቀት፤ ላለፉት አስራ ሁለት ዓመታት ደግሞ በቅርበት እንዳስተዋልኩት፤ በነጻነት ጥማትና በአልገዛም ባይነት ትግል የማህበረሰባችንን ትብትብ አመለካከት ጥሰው ከወጡትና ከማደንቃቸው እህቶቼ፡ ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል እና ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ውጪ፤ የዘመናችን የፖለቲካ ማህበረሰብ አበረታቶ፤ መርጦ፤ እደጉ ተመንደጉ ብሎና ፈቅዶ ያፈራቸው፡ ለሌሎቻችን አርአያ የሚሆኑ፤ ትውልዱን ሊቀርጹ የሚችሉ ሴቶችን፡ ለመቁጠር ብፈልግ እምብዛም ላገኝ አልቻልኩም።

ለዚህም ምክንያቱ ምን ይሆን ብዬ ራሴን ስጠይቅ ያገኘሁት መልስ፤ በህወሃትም ሆነ በተቃዋሚ ጎራ ያላችሁት “አብላጫዎቹ” ወንዶቻችን የኋላውን አሰራራችንን ሁሉ ኋላቀር ብላችሁ፤ በዘመናዊ ትምህርት ጫና ከበጎ ባህላችን ጋር ጭምር ቅራኔ ውስጥ ገብታችሁ፤ ራሳችሁም ገና ከአውሮፓዊያን የበላይና የበታች አስተምህሮ ነጻ ስላልወጣችሁና የሃገራችሁን ነባር የአስተዳደር ጥበብ፤ ባህልና አሰራር፡ በተወሳሰበና መተማመን በጎደለው፡ የፓርቲና የድርጅት የተውሶ አወቃቀር፤ ሙሉ በሙሉ በመተካታቹ ነው። በሌላ በኩል ማህበረሰባዊ ፍትህንና እኩልነትን ለማስፈን፤ ነጻ አስተሳሰብና አመለካከት መጀመሪያ ከራስ፡ ብሎም ከቤታችን ይጀምራል። ለሌሎች መብት ለመጮህ፡ መጀመሪያ የግል ህይወታችን የሰው ልጆችን ሁሉ መብት በማክበር ጽንሰ ሃሳብ የተዋቀረ ሊሆን ይገባዋል። በየግል ህይወታችን ከሰዎች ጋር ያለን ግንኙነት ቅጥፈት፤ ተንኮልና አድሎ የተመላበት ከሆነ፤ በሸንጎ ስለፍትህ ብንመክር፡ በአደባባይ ስለ መብት ብንጯጯህ፤ ባዶ የመንፈስ ርካታን ካልሆነ በቀር፡ ማህበራዊ ፍትህንና እኩልነትን አያጎናጽፈንም። የሃገራችን የፖለቲካ መድረክ እኔነትና ራስወዳድነት የነገሰበት የዓለማችን ነጸብራቅ ነውና ወደ ማንነታችን ካልተመለስን
ችግራችን ይቀጥላል። ከአውሮፓ በፊት ስልጣኔን ያጣጣመች፤ የነሉሲ መገኛ፤ የአክሱም፤ የላሊበላ፤ የፋሲለደስና፤ የሶፍ ሁመር ዋሻ ባለቤቷ ኢትዮጵያ ውስጥ፤ ለዛሬ ትውልድ የሚበጅ የአስተዳደር ጥበብ ተፈልጎ ይጠፋል ብዬ አላምንም።

በዚህ አጋጣሚ ይልማ ደሬሳ በገዳ ስርዓት መሰረት፡ የኦሮሞ ሴቶች ካገቡ በኋላ እንደ ወንድ በፈረስ ተቀምጠው እንደሚሄዱና ሃሳባቸውንም በነጻነት ሲናገሩ ተደማጭነት እንደሚያገኙ፤ በባላቸውም ትዳር የማዘዝና የማስተዳደር መብት እንዳላቸው ጽፈዋል (የኢትዮጵያ ታሪክ በአስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን 1959፤ ገጽ 247)። ዛሬ በዘመናችን የፖለቲካ ፈረስ ላይ የሚቀመጡ፡ በርካታ የኦሮሞ ሴት ወይዛዝርትን ማየት እፈልጋለሁ። የሃገር ውስጥና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮቻችን የደዋሮ ሴቶች ሆነው ማየትን እመኛለሁ። የእርዳታ ማስተባበሪያ ተቋም ወይም ትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ ብዙ መነኖችን ለማየት እፈልጋለሁ። ኢትዮጵያን፤ ኤርትራን፤ ሱማሌን፤ ጅቡቲን፤ 2ቱን ሱዳኖች፤ ግብጽንና ኬኒያን አዋደው እና የተቃቃረውን አስማምተው፤ ለዓለማችን የሰላምን ዘር የሚዘሩ እሌኒዎችን ማየት ህልሜ ነው።

ለሃገራችን ጥቅምና አንድነት፤ ለዓለማችን ደህንነትና ሰላም፤ ለምድራችን ልምላሜና በረከት ሴቶች ከማጀታቸው እየወጡ አደባባዩን እንዲሞሉት ወንዶችም ሴቶችም ማገዝ፤ ማበረታታት፤ ጓዳቸው እንዳይጎድል ዘመድ ወዳጅ እንዳይሰላች መተጋገዝ ይገባናል። በተመሳሳዩም ወንዶች ለሃገራዊ ጉዳይ አደባባይ ስትውሉ ሴቶችም ሆንን ሌሎች ወንዶች ለቤተሰባችሁ ልንሳሳላችሁ ይገባል። ውጤት አለመስዋዕትነት እንደማይገኝ የታወቀ ነው፤ ነገርግን አንዳንዴ መስዋዕትነቱ የግል፡ ወይም የቤተሰብ፤ ከፍ ሲልም የማህበረሰቡ ሊሆን ይችላል። ዳንኤል ፖ የተባሉ ጸሃፊ ሚሼል ናር ኦቤድ ስለተባለችው የሃገሯ የአሜሪካን መንግስት በውጪ ሃገራት የሚያደርገውን ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት አምርራ ስለምትቃወመው ሴት ሲጽፉ፤ ሚሼል ማህበረሰባችን የእናትነትን ሚና ለእናት ብቻ የሚተወውን አስተሳሰብ፤ ለጋራ ጥቅም ሲባል ሃላፊነትን በመውሰድ ለጎጆዋ ብቻ ልታውለው የምትችለውን ልጇን በሰላምና በእንክብካቤ የማሳደግ እናታዊ ተግባር፡ ለፍጥረት ሁሉ አለኝታ ለመሆን፡ እየታሰረች እየተፈታች ስለ ዓለም ሰላም ስትታገል፤ በአንጻሩ ባሏና ማህበረሰቧ ሴት ልጇን ለማሳደግ እናታዊ ሚናን በጋራ በመወጣት ከዓላማዋ እንዳትደናቀፍ እንደተባበሯት ጽፈዋል (Danielle Poe “Woman, Mother, and Nonviolent Activism.” Positive Peace: Reflections on Peace Education, Nonviolence, and Social Change 2010 P. 119, 130-31).

ስለዚህ ጥያቄው ሴቶች ለምን ከትግል ጎራ ታጡ ሳይሆን፡ ወደ ትግሉ ጎራ ሲወጡ በቂ ድጋፍ እንዲኖራቸው ማህበረሰባችንን ለማንቃት፤ ለማስተማር ምን ስራ ተሰርቷል? የትግሉ ጎራ እንደ ኮርማ መጎሻሸሚያ መሆኑ፡ እንኳን ሴቶችን ወንዶችንም ስለሚያሸሽ፤ ለሃገር ጥቅም ሲባል ክብሬ ኩራቴ ተነካ በማለት መጎሻሸሙን ለማስቀረት በእናንተ ዘንድ ፈቃደኝነቱ አለ ወይ? ወደ ትግሉ ጎራ እንደምንም የመጡትንስ ሴቶች ከጓዳ ስራ ሌላ፤ ለማማከርና የመሪነት ድርሻ እንዲኖራቸው ለማብቃት ዝግጁ ናችሁ ወይ? ለሃገራችንስ ከህወሃት የተለየ ሴቶችን፤ ወጣቶችንና አነስተኛ የብሄር ቁጥር ያላቸውን የማህበረሰባችንን ክፍሎች የሚያሳትፍ ራዕይ ሰንቃችኋል ወይ? ራዕዩ ሲጠነሰስስ የሁሉም የህብረተሰብ አካላት ተሳትፎ አለበት ወይስ ለይስሙላና ብቻ ነው ተሳትፏችን የሚፈለገው?

ዶ/ር ታደሰ ወ/ጊዮርጊስ፤ “ኅብረተሰብ የሚፈጠረው፡ ኅብረተሰብ የሚደራጀው፤ የኅብረተሰቡ ግማሽ አካል የሆኑት ሴቶች በኅብረተሰቡ እንቅስቃሴ ውስጥ በእኩልነት ደረጃ ሲሳተፉ ነው” ብለው ጽፈዋል (የምዕራባውያን ሥልጣኔና ኢትዮጵያዊያን በአሜሪካ ማህበራዊ እና ስነ ልቡናዊ ትንተና 2006፤ ገጽ 235)። “ዘመናዊ” ትምህርት ተምረናል በምንልበት በዚህ ዘመን፤ ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት የነበሩ ቀደምቶቻችንን ያህል እንኳን አስተውለን፤ ሴቶች በተፈጥሮ የተቸራቸውን የማማከር፤ የማግባባት፤ አርቆ የማየት ጥበብ ጥቅም ላይ ስናውለው አላየሁም። ፕ/ር ሃይሌ ገሪማ እንዳሉት፡ “የኢትዮጵያ ጉዞ ሶስት ሺህ ዘመን ወደኋላ፤ ወደኋላ፤ ወደኋላ ሆኗል”። በሌላ በኩል ቴዲ አፍሮ “የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ” ቢለንም፤ ወደኋላ የምናየው ከበጎውም ከመጥፎውም ታሪካችን ለመማር እንጂ የነበረንና የገነባውን ሁሉ እያፈረስን የኋልዮሽ በመሄድ፤ አፍርሰን ለመስራት መሆን የለበትም። ስለዚህ፡ ምንም እንኳ ሴቶች ወደ ትግሉ ጎራ እንዳይገቡ ሌሎች ሴቶችም ሊያዳክሙ እንደሚችሉ ቢገለጽም፤ የዘመናችን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምህዳር የተጥለቀለቀው ግን በወንዶች ስለሆነ፤ የሴቶች ፖለቲካዊ ተሳትፎ እንዲጨምርና የኋልዮሽ ጉዞአችን እንዲቆም እናንተስ ምን አቅዳችኋል? ብዬ ጥያቄውን ወደ ወንዶቻችን መልሸዋለሁ።

ሕገ ወጥ የባንክ ሒሳብ ፈራሚ መድበው ኹለት ደመወዝ በመውሰድ የተጠየቁት: የመቐለ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ ከሓላፊነታቸው ተነሡ

$
0
0
  • የፈጸሟቸው አስተዳደራዊ በደሎች፣ የሀ/ስብከቱን ሰላማዊ እንቅስቃሴ አውኳል፤
  • በጠ/ጽ/ቤቱ አጣሪ ቢመደብም፣ በጉቦ ለመደለል ሞክረዋል፤ ሒደቱም ታጉሏል፤
  • የቀድሞው የጅግጅጋ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ፣ በጊዜአዊነት ተመድበዋል፤

ሐራ ዘተዋሕዶ

እናት ቤተ ክርስቲያናችን፣ በየጊዜው በከፍተኛ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ አካሏ ከምትስዳቸው አቋሞችና ከምታወጣቸው መግለጫዎች እንደምንረዳው፣ ወቅታዊ ትኩረትን የሚሹት ዐበይት ችግሮቻችን፦ የመልካም አስተዳደር ዕጦት፣ የሙስና መስፋፋት፣ የሚወሰኑ ውሳኔዎች አስፈጻሚ ማጣት፣ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት እና የእናድሳለን ባዮች ውስጣዊ ሤራ ናቸው፡፡

በተለይም፣ በመልካም አስተዳደር ዕጦትና በአማሳኝነት የሚፈጸሙ በደሎች፣ በአንድ ገጻቸው፣ ለምእመናን ኅሊና ዕንቅፋት እየኾኑና አገልጋዮችንም የሥራ ዋስትናና ከለላ እያሳጡ ሲያርቋቸው፤ በሌላ ገጻቸው ደግሞ፣ ለመናፍቃንና ለፀራውያን ሰርጎ ገብነት ክፍተት በመፍጠራቸው፣ ለቤተ ክርስቲያናችን የወደፊት ህልውና ከፍተኛ ስጋት እንደኾኑ ታምኖበታል፡፡

መልካም አስተዳደር ሰፍኖ፥ አድልዎ፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ፣ መለያየት በአጠቃላይ ከመንፈሳዊነት ጋራ የማይጣጣም አስተሳሰብና አሠራር ተወግዶ የተስተካከለ ሥርዓትን ማየትን እንሻለን፡፡ ለዚኽም፥ ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖታችን ክብርና ህልውና ከልብ የሚቆረቆሩ፣ መልካምሥነ ምግባርና የተስተካከለ ሰብእና ያላቸው፤ እንዲኹም፣ በኑሮአቸው ኹሉ ለሕዝበ ክርስቲያኑ እንደ አርኣያ የሚጠቀሱ የውሉደ ክህነት ሠራተኞች አመራር፣ በእጅጉ ወቅታዊ መኾኑን ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በየቃለ ምዕዳናቸው እያሳሰቡ ነው፡፡

የአስተዳደራችን ማእከልና ርእስ የኾነው ጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ ዋና ባለሥልጣን የኾኑት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁም፥ ሥራንና ሠራተኛን በማገናኘት ላይ ያተኮረ፤ በሚለኩና ሊገመገሙ በሚችሉ ወጪ ቆጣቢ ዕቅዶች ላይ በተመሠረተ፤ የቤተ ክርስቲያንን መብቶችና ጥቅሞች አስጠብቆ በማወያየትና በማሳመን መሥራትን ማእከል ባደረገ አኳኋን፥ ተጠያቂነትን ለማስፈንና ሕግን ለማስከበር፤ የሙስናና የመልካም አስተዳደር ችግሮችንም ለመቅረፍ ጥረት በማድረግ ላይ እንዳሉ ይገለጻል፡፡

መላው አህጉረ ስብከት፣ በተሳተፉበት የዘንድሮው 35ኛ ዓመታዊ አጠቃላይ ጉባኤ፥ በየደረጃው ያለውን የመልካም አስተዳደር መስተጓጎልና ያለመሟላት ክፍተት በሚገባ ፈትሾ በማስተካከል፣ ከቤተ ክርስቲያናችን የሚጠበቅ አስተዳደራዊ ሥርዓት ለማስፈን በአርኣያነት እንደሚሠሩ ባወጡት የጋራ መግለጫ ቃል ገብተዋል፤ ሲኖዶሳዊና ማዕከላዊ የኾነውን አሠራር በሚቃረን መልኩ የሚፈጸመውን አስተዳደር ነክ የሕግ ጥሰት ለመከላከል፣ ቅዱስ ሲኖዶስ ዝርዝር መመሪያ በማውጣት እንዲከታተለው በማሳሰብ፣ መዋቅርን በመጠበቅ በሕገ ቤተ ክርስቲያንና በቃለ ዐዋዲው ለመሥራት ቃል ገብተዋል፡፡

የፋይናንስ አያያዙን ለማጠናከርና ዘመናዊ ለማድረግ በተዘረጋው የኹለትዮሽ የሒሳብ አመዘጋገብ፣ በግልጽነትና በተጠያቂነት በመሥራት፣ ምእመኑ፥ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎትና ለሃይማኖት መጠበቂያ ብሎ በእምነት የሚለግሰው ገንዘብና ንብረት ከምዝበራ ተጠብቆ ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል ለመሥራት ቃል ገብተዋል፡፡ የኦዲትና ኢንስፔክሽን አሠራሩም በሠለጠኑ ባለሞያዎች ምደባ ተጠናክሮ እንዲፈጸም አሳስበዋል፡፡

የአህጉረ ስብከቱን አጠቃላይ ጉባኤው የጋራ መግለጫና የውሳኔ ሐሳብ በማዳበር የበጀት ዓመቱ የሥራ መመሪያ እንዲኾን ያጸደቀው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤም፥ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ቀልጣፋና ቅንነት የሰፈነበት አሠራር እንዲኖር፤ በየደረጃው የተዘረጉት የልማት አውታሮች የበለጠ ውጤት እንዲኖራቸው ለማስቻል ከመንበረ ፓትርያርክ ሥራ አስኪያጅ ጀምሮ ኹሎችም የየአህጉረ ስብከቱ ሊቃነ ጳጳሳት ሓላፊነት ያለባቸው ስለኾነ ተከታትለው እየሠሩ እንዲያሠሩ ከፍተኛ ውሳኔ ወስኗል፡፡

በሀገር ውስጥ ካሉን 50 ያኽል አህጉረ ስብከት አንዱ በኾነው፥ በክልል ትግራይ – የመቐለ ሀገረ ስብከት፣ ከ2005 ዓ.ም. ጀምሮ ሲፈጸሙ የቆዩ የአስተዳደር በደሎችና የጥቅመኝነት ተግባራት፣ በአህጉረ ስብከቱ የጋራ መግለጫና በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የተወሰነውን የሚፃረር ኢ-ሕገ ቤተ ክርስቲያናዊ በመኾኑ፣ ሰሞኑን፣ መዋቅርንና ሕግን የማስከበር ርምጃ በጠቅላይ ጽ/ቤቱ ተወስዷል፤ ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት የሚበቃ ማጣራት እንዲካሔድም ቀጣይ አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡ ሌሎችም አህጉረ ስብከት በተመሳሳይ መልኩ መዳሰስ የሚገባቸው ሲኾን፤ ከሓላፊነት በሚነሡትና በቦታቸው በሚተኩት ሹሞችም የተጠያቂነቱና የአርኣያነቱ ጉዳይ በጥብቅ ሊታሰብበት ያስፈልጋል፡፡


(ሰንደቅ፤ 12ኛ ዓመትቁጥር 600፤ ረቡዕ፣ የካቲት 29 ቀን 2009 ዓ.ም.)

ሥልጣናቸውን መከታ በማድረግ፣ ከሌሎች የክፍል ሓላፊዎች ጋራ፣ ከሕግና መመሪያ ውጭ ኹለት ወርኃዊ ደመወዝ የሚወስዱት፣ የመቐሌ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ፥ መልአከ ብርሃናት ገብረ ሥላሴ ሕሸ፣ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ውሳኔ ከሓላፊነታቸው ተነሡ፡፡

መልአከ ብርሃናት ገብረ ሥላሴ ሕሸ፥ ሕገ ቤተ ክርስቲያንንና ቃለ ዐዋዲውን በመጣስ ከበላይ አካል የተላለፉ ውሳኔዎችንና መመሪያዎችን ባለማስፈጸም እንቢታ ሲያሳዩ መቆየታቸውን በውሳኔው የጠቀሰው ጠቅላይ ጽ/ቤቱ፤ በሀገረ ስብከቱ የፈጠሩት አስተዳደራዊ ችግር ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ፣ ከየካቲት 20 ቀን ጀምሮ፣ በሥራ አስኪያጅነት የሥራ መደብ የሚያገኙትን ወርኃዊ ደመወዝ ብቻ እንደያዙ፣ ከሓላፊነታቸው ተነሥተውና ወደ ዋናው መ/ቤት ተዛውረው የመንፈሳዊ ፍርድ ቤት አባል ኾነው እንዲሠሩ መመደባቸውን አስታውቋል፡፡

የተጣለባቸውን የሥራ ሓላፊነት ወደ ጎን በመተውና ሥልጣናቸውን መከታ በማድረግ የፈጸሟቸውን መተላለፎችና በደሎችም ውሳኔው በስድስት ነጥቦች ለይቶ ዘርዝሯል፡፡ የመጀመሪያው፣ በሥራ አስኪያጅነት ሓላፊነታቸው ከሚያገኙት በተጨማሪ፣ ከሌሎች የሀገረ ስብከቱ ሠራተኞች ጋራ ኹለት ደመወዝ ሲወስዱ መቆየታቸው ነው፡፡

ለዚኽም፣ ሥራ አስኪያጁ፣ ከ6 ወራት በፊት በሞት በተለዩት ሒሳብ ሹም ምትክ፣ ከዋናው መ/ቤት ዕውቅና ውጭ በራሳቸው የባንክ ፈራሚ በመመደብ ለሕገ ወጥነታቸው አመቺ ኹኔታ መፍጠራቸው ተመልክቷል፡፡ የኹሉም አህጉረ ስብከት የባንክ ሒሳብ ፈራሚዎች የሚመደቡት በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ደብዳቤ እንደኾነ የጠቀሰው ውሳኔውም፤ ሥራ አስኪያጁ፣ ከሕግና መመሪያ ውጭ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ካልፈቀደለት ሠራተኛ ጋራ በጣምራ ፊርማ የባንክ ሒሳብ ሲያንቀሳቀሱ መቆየታቸውን አስረድቷል፡፡

የሀገረ ስብከቱ ምንጮች እንደገለጹት፣ ሥራ አስኪያጁ፣ ራሳቸውን በጽርሐ ኣርያም ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል አስተዳዳሪነት በመሠየም የእልቅናውን ደመወዝ ይወስዳሉ፤ በሕገ ወጥ መንገድ የተመደቡት የሀገረ ስብከቱ ሒሳብ ሹምና ዋና ጸሐፊም፣ በጽ/ቤቱና በአድባራት ደራርበው በያዟቸው ሓላፊነቶች፣ በአንድ ተቋም የተለያዩ የሥራ መደቦች ኹለትና ከዚያ በላይ ወርኃዊ ደመወዝ እንደሚያገኙ ተጠቁሟል፡፡

የጠቅላይ ጽ/ቤቱ ውሳኔ፥ በኹለተኛና በሦስተኛ ደረጃ ያስቀመጠው፣ ከወረዳ ቤተ ክህነት ሠራተኞችና ከአድባራት ለሚቀርቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች፣ በሥራ አስኪያጁ ወቅታዊ ምላሽ ባለመሰጠቱ ባለጉዳዮች ላልተገባ ወጪና እንግልት መዳረጋቸውን ነው፡፡

ለአብነት ያኽል፦ የዓይናለም ደብረ ኃይል ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ካህናትና ምእመናን የደረሰባቸውን በደል በመዘርዘር ላቀረቡት አቤቱታ፣ ሀገረ ስብከቱ በአስተዳደር ጉባኤ አይቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት፣ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ መመሪያ ቢሰጥም፣ በማንአለብኝነት ሳይፈጸም ቀርቷል፤ ባለጉዳዮቹም፣ በድጋሚ ለኹለተኛ ጊዜ አቤቱታ ለማቅረብ በመገደዳቸው ላልተገባ ወጭና እንግልት ተዳርገዋል፡፡

እንዲኹም፣ የሦስት ወረዳ አብያተ ክህነት ጽ/ቤቶች ሠራተኞች፣ የደረሰባቸውን አስተዳደራዊ በደል በመግለጽ በጻፉት ማመልከቻ ያቀረቡትን አቤቱታ፣ ሀገረ ስብከቱ ደረጃውን ጠበቆ በአስተዳደር ጉባኤ ውሳኔ እንዲሰጥበት ከዋናው መሥሪያ ቤት በተጻፈ ደብዳቤ መመሪያ ቢተላለፍም ሳይፈጸም ቀርቷል፡፡ ሌሎችም በርካታ መሰል ጉዳዮች እንዲኹም የቋሚ ሲኖዶስንና የፍርድ ቤት ውሳኔዎችን ጭምር ባለማስፈጸም፣ ሥራ አስኪያጁ፣ ለቤተ ክርስቲያናችን ሲኖዶሳዊና ማዕከላዊ አስተዳደር ባለመታዘዝና ተገዥ ባለመኾን እንቢታ ሲያሳዩ መቆየታቸው ታውቋል፡፡

በብልሹ አሠራርና በጥቅመኝነት የተፈጠረው ችግር፣ ከሀገረ ስብከቱ አልፎ ለክልላዊ መንግሥቱና ለመቐለ ከተማ አስተዳደር ጭምር የደረሰ ሲኾን፤ በአግባቡ አጣርቶ ኹነኛ የውሳኔ ሐሳብ የሚያቀርብ ሦስት አባላት ያሉት የጠቅላይ ጽ/ቤቱ ልኡክ፣ ባለፈው ጥር 29 ቀን 2009 ዓ.ም. ወደዚያው ተልኮ እንደነበር ውሳኔው አውስቷል፡፡

ልኡኩ በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት እንደደረሰ፣ የሚጣሩትን ጉዳዮች በመለየትና በአካሔዱም ላይ ከሥራ አስኪያጁ ጋራ በመነጋገር ተግባብቶ የነበረ ቢኾንም፣ ተግባሩን ለመጀመር በሚዘጋጅበት ዕለት ግን፣ ሥራ አስኪያጁ በፈጠሯቸው ማሰናከያዎች ምክንያት ተልእኮውን ሳያሳካ መመለሱ ተገልጿል፡፡

በመጀመሪያ፥ “ነገሩን አለሳልሱት፤ አስተኙት፤ የምትጠይቁትን እንከፍላለን፤ እንሰጣችኋለን፤” በሚል ልኡኩን በጉቦ ለመደለል ሞክረዋል፤ በገንዘብ የማጣራቱን ሒደት የማዳፈን መላ፣ ችግሩ ከተፈጠረበት ከ2005 ዓ.ም. ጀምሮ በሚላኩት የጠቅላይ ጽ/ቤቱ ልኡካን ላይ የለመዱት ቢኾንም፣ በአኹኑ ግን አልያዘላቸውም፡፡ ይህን ሲረዱም፣ ሊቀ ጳጳሱን በመገፋፋት እንዲኹም፣ በማጣራቱ እንዲሳተፉ ከጅምሩ ስምምነት የተደረሰባቸውን አቤቱታ አቅራቢዎችን ስም በማጥፋት አላስፈላጊ ቅስቀሳ በማካሔድ ሥራው በተያዘለት መርሐ ግብር እንዳይከናወን መሰናክል ፈጥረዋል፡፡

ልኡኩም፣ ያጋጠመውን መሰናክል በሪፖርት ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ በመረጃ ደረጃ ደግሞ ለከተማው ከንቲባ በማሳወቁ፣ በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ አንቀጽ 51 ንኡስ ቁጥር 6 ድንጋጌ መሠረት፣ የሀገረ ስብከቱ ዋና ጽ/ቤት ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጽ/ቤት እንደ መኾኑ መጠን፣ ሥራ አስኪያጁ ማጣራቱን ማስተጓጎል እንደማይችል የሚገልጽና ሒደቱ ከቆመበት እንዲቀጥል የሚያዝ ጥብቅ መመሪያ በደብዳቤ ቢያስተላልፍም፣ በማንአለብኝነት መመሪያው ሳይፈጸም መቅረቱን በውሳኔው አስፍሯል፡፡

ይህም ተደማምሮ፣ ከመልካም አስተዳደር ዕጦት በላይ የሀገረ ስብከቱን አጠቃላይ ሰላማዊ የሥራ እንቅስቃሴ የሚያኮላሽ በመኾኑ፣ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ፣ የካቲት 10 ቀን 2009 ዓ.ም.፣ በቁጥር 2956/19/2009 በጻፈው ደብዳቤ፣ሥራ አስኪያጁ፣ የሀገረ ስብከቱን ሒሳብ በስማቸው እንዳያንቀሳቅሱ ከማገዱም በላይ፣ ከሥራና ከደመወዝም አግዶ፣ እስከ የካቲት 17 ቀን 2009 ዓ.ም. ወደ ዐዲስ አበባ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ሔደው ሪፖርት እንዲያደርጉ አዟቸዋል፡፡

ሥራ አስኪያጁም፣ በትእዛዙ መሠረት፣ ወደ ዐዲስ አበባ ከመጡ በኋላ፣ የሀገረ ስብከቱ ኹለንተናዊ ችግሮች ቀድሞ በተመደበው አጣሪ ልኡክ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ፣ ለሀገረ ስብከቱ ወቅታዊ ሰላም ሲባል፣ ከየካቲት 20 ቀን ጀምሮ ከሥራ አስኪያጅነት አንሥቶ ወደ መንፈሳዊ ፍ/ቤት በማዛወር መመደቡን አስታውቋል፡፡

በተያያዘ ዜና፣ የጠቅላይ ጽ/ቤቱ አስተዳደር ጉባኤ፣ ትላንት ማክሰኞ፣ የካቲት 28 ቀን 2009 ዓ.ም. ባካሔደው ሳምንታዊ መደበኛ ስብሰባው፣ ከሓላፊነት በተነሡት መልአከ ብርሃናት ገብረ ሥላሴ ሕሸ ምትክ፣ በቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በጠቅላላ አገልግሎት ሓላፊነት የሚሠሩት፣ መልአከ መዊዕ ሰሎሞን ዓባይ፣ ሀገረ ስብከቱን በሥራ አስኪያጅነት እንዲመሩ በጊዜአዊነት መድቧል፤ የአሠራር ክፍተቶችንና አስተዳደራዊ በደሎችን የማጣራቱ ተግባርም፣ ቀደም ሲል በተመደበው ልኡክ፣ ከቀጣዩ ሳምንት ጀምሮ እንዲቀጥል ወስኗል፡፡

“ሁለት ስለት ባለው ቢላዋ ድርጅታችንን ለማረድ ሴራው ተጠናክሮ ቀጥሏል” – በ ፋኑኤል ክንፉ

$
0
0

በ ፋኑኤል ክንፉ / ሰንደቅ

ብአዴን-ኢሕአዴግ በዓመት ሁለት ጊዜ “አብዮታዊ ዴሞክራሲ” የሚል ስያሜ ያለው የድርጅቱ ልሳን መጽሔትን ያሳትማል። በዚህ ወር ለንባብ የበቃው የድርጅቱ ልሳን መጽሔት፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊና ድርጅታዊ ጉዳዮችን እና ተሞክሮዎችን በስፋት የዳሰሰ ነው። የዚህ የጥር ወር 2009 ዓ.ም. የታተመውን አብዮታዊ ዴሞክራሲ መጽሔት በወፍ በረር ለመቃኘት ተሞክሯል።

እንደሚታወቀው ኢሕአዴግ “ጥልቅ ተሃድሶ” የሚል ስያሜ የሰጠውን ተሃድሶ በፓርቲ እና በመንግስት መዋቅር ውስጥ አካሂዶ ጨርሷል። ብአዴን- ኢሕአዴግም ከተሃድሶ ንቅናቄው ጋር የተያያዘ ጥናታዊ ጽሁፍ አዘጋጅቶ ለአባላቱ እና ለባለድርሻ አካላት አትሞ አሰራጭቷል። የድርጅቱ ልሳን መጽሔት ተላላፊ እና ገዳይ የፖለቲካ በሽታዎች ሲል አምስት ፍሬ ነገሮች አስቀምጧል።

 

በዚህ ዓመት በአማራ ክልል የተፈጠረው የፖለቲካ የማሕበራዊ ቀውስ መሰረታዊ መነሻዎች ናቸው ያላቸውን በግምገማ የተገኙ ነጥቦች ከማስቀመጡ በላይ፣ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የተሃድሶ መሰረታዊ አስተሳሰቦች እና አካሄዶችን ያሳያሉ ያላቸውን የሀገሮች ተሞክሮ በዝርዝር ለማስቀመጥ ብዙ ርቀት ሄደዋል። ለአብነት ከቀረቡት መካከል፣ የፈረንሳይ ሶሻሊስት ፓርቲ፣ የጀርመን ሶሻል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የሲንጋፑር ፒፕልስ አክሽን ፓርቲ፣ የሕንድ ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲ እና የደቡብ አፍሪካ ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲ ናቸው። የተጠቀሱ ሀገሮች ከብአዴን-ኢሕአዴግ ርዕዮተዓለም ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ወይም ሙሉ ለሙሉ መመሳሰል ያላቸው ሳይሆኑ፣ ካስቀመጡት መስመር አንፃር የደረሰባቸውን የፖለቲካና የማሕበራዊ ቀውሶች እንዴት መወጣት እንደቻሉ ተሞክሮ ለመውሰድ ያለመ መሆኑ በግልፅ ሰፍሯል።

ድርጅቱ በተሃድሶ ነቅሶ ያወጣቸው ተላላፊና ገዳይ የፖለቲካ በሽታዎች ያላቸው ሲደመሩ የሚያሳዩት ውጤት፣ የድርጅቱ ማሕበራዊ መሰረቶች የሆኑትን የህብረተሰብ ክፍል አስቀይመዋል። ከዚህም በላይ ርቀው በመሄድ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን የማያከብሩ ፀረ-ዴሞክራሲያዊ አያያዞች መስተዋላቸውን ሰነዱ አስቀምጧል።

ድርጅቱ በተሃድሶ ነቅሶ ያወጣቸው ተላላፊና ገዳይ የፖለቲካ በሽታዎች ያላቸው በተለይ ከአማራ ክልላዊ መንግስት እና አስተዳደር አንፃር ስንመለከተው፤ የአማራ ሕዝብ ቢከፋው፣ ቢያምፅ፣ ተቃውሞውን ቢያሰማ ተገቢነቱ ከፍ ያለ ነው። የአማራ ሕዝብ ቅሬታዎች ቅቡል መሆናቸውን በተጨባጭ የሚያሳይ ነው። በአንፃሩ ይህንን የአማራ ሕዝብ ችግሮች መነሻ በማድረግ ማሕበራዊ መሰረት ሳይፈጥሩ፣ የሕዝቡን ችግሮች ለራሳቸው ፍላጎት መጠቀሚያ ለማዋል የተንቀሳቀሱ ኃይሎች ትዝብት ውስጥ ከመውደቅ ውጪ ያተረፉት አንዳች ነገር የለም። በተለይ በአማራ ሕዝብ እና በትግራይ ሕዝቦች መካከል ለዘመናት የነበረውን የማሕበራዊ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ትስስሮሽን ለመበጣጠስ እና በሕዝቦቹ መካከል የበቀለኝነት የደም መስመር ለማስመር ሲሯሯጡ ለነበሩ ኃይሎች የኢትዮጵያ አምላክ ይፋረዳቸው።

እንዲሁም ድርጅቱ የዘረዘራቸው ተላላፊና ገዳይ የፖለቲካ በሽታዎች ያላቸው በፍጥነት ሊያክማቸው ካልቻለ በአማራ ክልል የማሕበራዊ አብዮት እንቅስቃሴዎች መከሰታቸው አይቀሬ ነው። በርግጥ በሰነዱ ላይ እንደሰፈረው፣ “ተግባርን የመሰለ ፍትሃዊ ዳኛ የለምና፣ የመታደስ ጉዳይ የአንድ ሰሞን ሁከትና ግርግር ሳይሆን በቀጣይነት የጠራ መስመር የመጨበጥና በተግባር የመተርጎም ጉዳይ ነው” ይላል። ሁላችንም የምናየው ነው የሚሆነው።

 

በዚህ አምድ ብአዴን/ኢህአዴግ በጥልቅ ተሃድሶ አምስት ተላላፊና ገዳይ ፖለቲካዊ በሽታዎች ከነመንስኤዎቻቸው ደርሼባቸዋለሁ ያለውን አቅርበነዋል። አንባቢዎቻችን የራሳችሁን ግንዛቤ ውሰዱ።

 

የርዕዮተ ዓለማዊና ፖለቲካዊ አስተሳሰብ

መሸርሸርና ከመሰረታዊ መስመሮች መውጣት

የኪራይ ሰብሳቢነትን የፖለቲካ ኢኮኖሚ በመናድ የልማታዊ የፖለቲካ ኢኮኖሚን የመገንባት አስተሳሰብን ቀርፆ፣ በተግባር ለውጥ ለማምጣት የተሰማራው አመራር የድርጅቱን መስመር ከጥቀት መጠበቅ ተስኖት ታይቷል። አስተሳሰብ ግንባታን ማዕከል ያደረገ የመስመር ማጥለቅ ስራ በብዛት አልተሰራም፤ ይልቁንም በቴክኒካል ስራዎች አፈፃፀም ላይ መታጠር ታይቶበታል። አመራሩ እራሱን በንባብና በተግባር እያስተማረና እያበቃ በተቋሙ ውስጥ ልማታዊ ዴሞክራሲዊ መስመሩ ይበልጥ እንዲሰርጽ በማድረግ በኩል የትኩረት ማነስና ስንፍና እንደተስተዋለበት ታይቷል።

 

በግምገማ እንደተረጋገጠው፣ የመስመር ግልጽነት መጓደል፣ የያዘውን የመልቀቅና የህዝባዊ ውግንና መሸርሸር ታይቶበታል። “አውቃለሁ” እያለ መስመሩን ከላይ ከላይ ቢገልጽም፣ በጥልቀት ሳይጨብጠው እንደቆየ ግልጽ ሆኗል። “መስመሩን ይዣለሁ” የሚለውም በጥልቀት ጨብጦ መስዋዕትነት ሊከፍልበት መዘጋጀቱን የሚያረጋግጥ ተግባራት የማከናወን ድክመት ታይቶበታል። መስመሩ በቀጣይነት በማህበራዊ መሰረቱ ላይ እንዲሰርፅም አጥጋቢ ስራ ሳይሰራ ቆይቷል።

 

የአብዛኛው ህዝብ መድህን የሆነውንመስመር አንግቦ ከመፋለም ይልቅ፣ በኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰቦች መዋጥ ተስተውሎበታል። ጎራ ከመደበላለቅ አልፎ ቀላል ባሆነ ደረጃ የጠላት አስተሳሰቦችና አቋሞች ሲራመዱ ታይተዋል። ከልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መስመር የራቁ የትምህርት አስተሳሰቦችና ተግባራት በግላጭ ሲታዩ፣ በሁኔታው ተውጧል፣ ኋላቀር አስተሳሰብን መዋጋትም ብርቅ እንደነበር ግልጽ ሆኗል። አርሶ አደሩንና ሌሎች የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ ማህበራዊ መሰረቶቹን እየዘነጋ፣ ከማህበራዊ መሰረቶቹ ውጪ ለጥገኛ ባለሀብቶች የሚያጋድል አመራር የመሆን አዝማሚያ ታይቶበታል።

 

 

የአባላትን ምልመላና ግንባታ እንዲሁም የድርጅቱን ፕሮግራምና መተዳደሪያ ደንብ ማዕከል አድርጎ፣ በዚሁ ተዋረድ የተገነቡ መመሪያዎችንና አሰራሮችን በጥብቅ ዲስፕሊን ይዞ የግንባታ ሥራውን የማካሄድ ጉድለት ታይቶበታል። ድርጅት የሰዎች ስብስብ ነው። ጠንካራ ታጋዮች የተሰባሰቡበት ከሆነ ጥሩ ድርጅት ይሆናል። በአመራር ምልመላና ስምሪት ወቅት በቂ እውቀት ይዞ በተግባር የተፈተኑትን እየለዩ ግልጽነት ባለው አሰራር ወደ አመራር በማምጣት እንዲሁም በሂደት የሚስተዋሉ ዝንባሌዎችን እየለዩ በመገንባት በኩል በጥብቅ ክትትል የመምራት ጉድለት ነበር። ይህም በመሆኑ በየደረጃውና በየተቋማቱ የተሻለ አቅም ያላቸውና ህዝባዊ አመራር በመስጠት ሊያረጋግጡ የሚችሉ ሰዎች ወደ ድርጅቱ በሚፈለገው ደረጃ ተመልምለው አልገቡም።

 

አመራሩ ጠንካራ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት እየገነባና ሁኔታዎችን በጥልቀት እየገመገመ፣ የአመራር ሚናውን ማረጋገጥ ሲገባው፣ ከዚህ አካሄድ ያፈነገጡ ሁኔታዎችን በጥልቀት እየተጋለጠና ችግሮችን ወደ ውስጥ እየተመለከተ ከመሄድ አኳያ ችግሮች ታይተዋል። ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታውን በጥልቀት አለመረዳትና የሚያስከትሉትን አደጋ በብቃት አለመመዘንም ተገምግሞ ትምህርት ተወስዶበታል። እንዲሁም በተጨባጭ ግምገማና በዝንባሌ ትንተና ላይ ያልተመሰረተ፣ ጥብቅ የአመራርና የስራ ዲስፕሊን መጓደል፣ የትግልና የለውጥ አብነት አለመሆን እንዲሁም፣ የርዕዮተ አለማዊና ፖለቲካዊ አስተሳሰቡ ደካማ መሆኑ ተረጋግጧል።

 

የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብንና ተግባርን

በቀጣይነት ያለመታገል ሁኔታ

የክልላችንም ሆነ የአገራችን የፖለቲካ ኢኮኖሚ ልማታዊ ሳይሆን ኪራይ ሰብሳቢነት ወይንም ህገወጥ ተጠቃሚነት ሰፍኖበት የቆየ ነው። ይህንን የፖለቲካ ኢኮኖሚ በልማታዊ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ኢኮኖሚ መለወጥየግድ ይላል። አመራሩ የችግሩን ስፋትና ጥልቀት ግምት ያስገባ የለውጥ ንቅናቄ በማካሄድ በኩል የአስተሰብና የአፈፃፀም ችግሮች ታይተውበታል። የአስተሳሰብ ችግሮችን በሚመለከት በርካታ መገለጫዎች በአመራሩ ዘንድ በስፋት ተስተውለዋል። በተግባርም ኪራይ ሰብሳቢነትን የሚደፍቁ፣ ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ተግባራትን የሚያሳድጉ ተግባራትንም በማከናወን ረገድ መሰረታዊ ድክመቶች እንደተስተዋሉበት በግምገማ ተረጋግጧል።

 

የሙስናን ተግባራት በተመለከተ በየደረጃውና በሚመራው ተቋም፣ የባለሀብቶችንና የአመራሩን መርህ አልባ ጉድኝቶች አነፍንፎ፣ የስርዓቱን ጤንነት ለመጠበቅ የማይተጋ፣ ሰምቶ እንዳልሰማ የሚያልፍና የማይታገል አመራር ሆኖ መሰንበቱም ታይቷል። በኢንቨስትመንት ስም ሰፋፊ መሬቶችን አጥረው፣ አንድም ልማት የማያለሙ ብቻ ሳይሆን፣ ለሌሎች አልሚዎች እንቅፋት ሲሆኑ አይቶ እንዳላየ የሚያልፍ፣ የማይታገልና ርምጃም የማይወሰድ ነበር፣ ከዚህም የተነሳ ለተለያዩ ጥርጣሬዎች ተጋልጦ ቆይቷል።

 

ከመሬታቸው ለሚነሱ አርሶ አደሮች ካሳ አከፋፈል በወቅቱ በመክፈልና በተገቢ መንገድ በማቋቋም ረገድ ድክመቶች ታይተዋል። በግብር አሰባሰብ፣ በግንባታ ኮንትራት አስተዳደር፣ ፍትሃዊ የንግድ ስርዓት በአግባቡና በንጽህና እንዲፈፀም አመራር በመስጠት ረገድም ድክመቶች ታይተውበታል። በኮንስትራክሽን፣ በግዥ፣ በሰው ኃይል ስምሪት፣ ወዘተ የሚደርሱትን ጥቆማዎችና የሚሰማቸውን ብልሹ አሰራሮች በማስተካከል በኩል ጉድለቶች ነበሩበት። የያዘውን የህዝብ ኃላፊነት የህዝብ ኑሮ መለወጫ ማድረጉ ቀርቶ፣ የመንግስት ስልጣን አተያዩና አጠቃቀሙ የተዛባ እንደነበርም ታይቷል። ስልጣንን የኑሮና የሀብት መሰረት አድርጎ የመመልከት አዝማሚያ ታይቶበታል። ተጠያቂነት የሰፈነበት የስራ አፈፃፀምን ማሳደግም ላይ ችግሮች ነበሩ። ስለሆነም ውጤታማ ሳይሆኑ በመንግስት ስልጣን የመቆየት ዝንባሌ አንዱ መስተካከል ያለበት ጉዳይ እንደሆነ ተገምግሟል።

 

የህዝብን አንገብጋቢ ችግሮች ለይቶ በመፍታት ረገድ

የታዩ ድክመቶች

አመራሩ ዝንባሌዎችን እየተነተነ፣ ፖለቲካዊ አንድምታቸውን እየተገነዘበ፣ ችግሮች ከፍተኛ ደረጃ ላይ ሳይደርሱ ህዝብን እያሳተፈ የመፍታት መሰረታዊ ጉድለቶች ነበሩበት። በችግሮቹ አፈታት ዙሪያ ጥበብ የማነስም፣ የአተያይ ጉድለትም አጋጥሞታል። የአመራር ሂደቱም ዳተኛ እንደሆነ ተገምግሟል። ህዝብ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች፣ እንዲሁም በየተቋማቱ የሚነሱ ችግሮችንና አለመግባባቶችን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ፈትቶ ውጤታማ በመሆን በኩልም ችግሮች እንዳሉ ተለይቷል።

 

በግብርና ምርታማነት እድገት የመጣ ቢሆንም፣ ማደግ በሚገባው ደረጃ አላደገም። ይህም የገጠሩ ህዝብ በሚፈልገው ደረጃ እንዳይሻሻል እንቅፋት ሆኗል። በመሆኑም አመራሩ መሰረታዊ ለውጥ አላመጣም። በተለይም የግብርና ምርታማነት ስነምህዳርን ያማከሉ የምርምር ውጤቶችን በማውጣትና የአርሶ አደሩን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በሚፈለገው ደረጃ እንዲሻሻል በማድረግ በኩል የተሰራው ስራ ብዙ ችግሮች ያሉበት መሆኑ ተገምግሟል። በከተሞቻችንም የአምራች ኢንዱስትሪ መስኮችና የንግድ ስራ እንቅስቃሴ ምርታማነት እድገት በሚፈለገው ደረጃ እንዳላደገና ቀጣይ ርብርብ እንደሚጠይቅ ግልፅ ሆኗል።

 

የከተማውን ህብረተሰብና በገጠርም ቢሆን ቁጥሩ ጥቂት የማይባል ህብረተሰብ፣ መሰረታዊ የምግብ ፍጆታዎችን የሚሸምት በመሆኑ፣ ከምርታማነት አለማደግ፣ ከገቢ ምንጮች አለመስፋፋትና አለማደግ ጋር የተያያዘ የኑሮ ውድነት እያሰቃየው ይገኛል። እነዚህንና ተጓዳኝ ችግሮችን በብቃት በመፍታትና በለውጡ ላይ የተመሰረተ ተስፋ እያሳደጉ አመራርን በማረጋገጥ ረገድ ብዙ ችግሮች እንደነበሩ ግምገማው አረጋግጧል።

 

 

ስራ አጥነት በገጠርና በከተሞች እየተስፋፋ መሄዱ ግልጽ ነው። በጥቂቱ የሚገኘው የስራ እድልም በዘመድ፣ በአድሎና በትስስር የሚያዝ በመሆኑ፣ ወጣቱን ተስፋ እያስቆረጠ እንደሄደና ችግሩን የሚፈታ ጥረት መካሄድ እንዳለበት ታይቷል። የጥቃቅንና አነስተኛ አንቀሳቃሾች ተጨባጭ ሁኔታ፣ የወጣቱን ተስፋ የሚያለመልሙ መሆናቸው እየቀረና የወጣቶቹ መደራጀት እንደ መጨረሻ ግብ እየተቆረጠ መሄዱ፣ የወጣቱን ሰርቶ የመለወጥ ፍላጎት ተፈታትኖታል። አመራሩ በየሚመራው ተቋም ያለውን የስራ እድል ወጣቱን ተሳታፊ በማድረግ ትኩረት ሰጥቶ አለመስራት፣ ቅንጅታዊ አሰራር መጓደል፣ ግብአትን (ብድርን) በቀልጣፋ አሰራር አለማቅረብ፣ ይልቁንም በመመሪያ ማጠርና ባለው የመልማት እድል ልክ አቅዶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ረገድ፣ ከፍተኛ ችግሮች በመታየታቸው የተነሳ፣ እነዚህን ችግሮች የሚፈታ ርብርብ መካሄድ ይኖርበታል።

 

የወጣቶችና የሴቶች አደረጃጀቶች በጥቅሞቻቸው ዙሪያ ተሰልፈው እንዲታገሉ የሚያደርግ ችግር ፈቺ ድጋፍ አለማድረግ፣ ሴቶች ከሚደርስባቸው ተፅዕኖ እንዲሁም ኋላቀር አስተሳሰብና ተግባር እንዲላቀቁ በሚያደርግ አግባብ ስራውን አለመምራት፣ አደረጃጀቶችንም መሬት አስነክቶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በማድረግ በኩል መሰረታዊ ችግሮች ተገምግመዋል። የልማት ማዕከላትን (Growth Corridor) የተከተለ ልማትና ድጋፍ አለመስጠት፣ በዝናብ አጠርና በደጋማ አካባቢዎች ለሚኖረው ህዝብ በቂ ቴክኖሎጂዎችና የተሻሻሉ አሰራሮች ቀርበው ህይወቱን የሚለወጡ ተግባራት በአጥጋቢ ሁኔታ አልተካሄዱም፣ ስለሆነም እነዚህን የሚለውጥ ርብርብም ጠይቋል።

 

ከወሰንና ከማንነት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በህዝባዊነት መንፈስ ተመልክቶ፣ በወቅቱና በትክክለኛው አግባብ የመፍታቱ ሥራ ጊዜ ወስዷል። የችግሮችን ባህሪና ፖለቲካዊ አንድምታቸውን ተረድቶ እንዲሁም የችግሩን ምክንያቶች ወደ ውስጥ ተመልክቶ መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ የስሜት መጫጫንና፣ ውጫዊ ማድረግ የታየበት ወቅት ነበር። ህዝብን የሚያረጋጋ ስራ በመስራት በኩልም ችግሮች የተስተዋሉበት ነበር። ከዚህ በመነሳትም በህዝቦች ዘንድ ቅሬታና አለመግባባት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል።

 

 

የክልሉንና የየአካባቢዎችን እቅድ በማዘጋጀት፣ በእቅዱ መሰረትም ፈጻሚን በማብቃትና ውጤታማ የክትትልና ድጋፍ ስርዓት በመዘርጋት የአመራርነት ሚናን የማረጋገጥ መሰረታዊ ድክመቶችም ታይተዋል። በየአካባቢው ያለውን የልማት አቅም ተጠቅሞ፣ የህዝቡን ኑሮ ለመለወጥ ከመረባረብ ይልቅ “አልተጠቀምንም” በሚል አንጋጦ ማየት ተስተውሏል። በገጠርና በከተሞች ህዝብን የሚያስመርሩ የመልካም አስተዳደር በደሎች ላይ ስር ነቀል ለውጥ ያለማምጣት ችግሮች ተገምግመዋል። በተለይም የሴቶችን የመልካም አስተዳደር ችግሮች የመፍታት፣ ቅንጅታዊ አሰራሩን አዳብሮ የመንቀሳቀስና እልባት እንዲያገኙ የማድረግ ድክመቶች ሲታዩ ቆይተዋል።

 

በፌዴራልም ሆነ በክልል የሚሰሩ የመሰረተ ልማት አውታሮች ግንባታ በጥራትና በወቅቱ እንዲከናወኑ መርህ ላይ ቆሞ በመታገልና በማስተካከል ረገድ ድክመቶች ነበሩ። በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የተጀመሩ የመንገድ፣ የውሃ፣ የመስኖና የቤቶች ልማት ግንባታዎች ተጓትተዋል፣ ጥራት የጎደላቸው መሆናቸውም ተገምግሟል። ችግሮቹንም በወቅቱ ክትትል አድርጎ መፍትሄ በመስጠት በኩል የቁርጠኝነት ችግሮች ነበሩበት። የሲቪል ሰርቪስ፣ የፍትህ፣ የፋይናንስ፣ የአመራርና ሌሎች የማሻሻያ ፕሮግራሞች በውጥን ታቅደውና ተጀምረው የቀሩበት ሁኔታም እንደነበር ተገምግሟል። ተግባራቱን በጥብቅ ይዞ ውጤት በሚያመጣ አግባብ የመምራት ጉድለት ነበር። የተበላሹ አለሰራሮችንና የስራ ድክመቶችን ፈልፍሎ አውጥቶ ተጠያቂ የሚያደርግ፣ የተበላሹትን የሚያርምና የጠነከሩትን የሚያበረታታ ጥበቅ አሰራር ተነድፎ የህዝቡን ችግሮች በሚፈታ መልኩ ስራ ላይ እንዲውል የአመራርነት ሚናውን አላረጋገጠም።

 

አድርባይነትና ፀረ-ዴሞክራሲ በድርጅቱ ውስጥ ገንግኗል

ድርጅቱ ዴሞክራሲዊ ባህሪው እያደገ፣ የታጋዮችና የተራማጆች ድርጅት መሆን ሲገባው፣ በሂደቱ ከዚህ በተቃራኒው ፀረ-ዴሞክራሲና አድርባይነት እየተስፋፋ እንደመጡ ተረጋግጧል። በውስጠ ድርጅት ዴሞክራሲው፣ ለየት ያለ ሃሳብ በሚቀርብበት ሁኔታ በብቃት ለመደማመጥ የዝግጁነት ችግር ታይቷል። በየደረጃው የሚነገረውን መስማት እንጂ ያለ ማዳመጥ ሁኔታም ነበር። “አዳምጫለሁ” ቢልም በተግባር ያለመተርጎም ሁኔታ ነበር። አዳምጦ ይተወዋል፣ የተስማማ መስሎ አለመስማማቱን በተግባር የመግለፅ አዝማሚያዎችም ነበሩ። የማዳመጥ ችግሩ በአመራሩ መካከል ብቻ ተወስኖ የቀረ ሳይሆን፤ ወደ ሁሉም አቅጣጫዎች ተስፋፍቶ ዘልቋል። በዚህም የተነሳ፣ ከድርጅቱ አመራሮችና አባላት አልፎ እስከ ህዝቡ ድረስ ዘልቆ “ትሰማላችሁ እንጂ አታዳምጡም፤ ብታዳምጡም ወደ ተግባር አትቀይሩም!” እስከማለት ደርሷል።

 

በየደረጃው ማለትም በከፍተኛ፣ በመካከለኛ፣ በጀማሪና በታችኛው አመራር መካከል ዴሞክራሲያዊ ግንኙነቱ መሆን በሚገባው ደረጃ ላይ ያልደረሰ፣ አልፎ ተርፎም አድርባይነትና ፀረ-ዴሞክራሲ፣ መጠቃቃትና አድሮ መኖር የተጣባው እንደነበር በግምገማው ግልጽ ሆኗል። መርህ ላይ ቆሞ ሁሉም ለዴሞክራሲና መርህ ላለው ግንኙነት መታገል ሲገባው፣ መርህ አልባነት ተስተውሏል። ወጥነት ባለው መስመር ላይ የተገነባ የአመራርነት ሚናውን የማረጋገጥ ጉደለቶች ነበሩ። በአመራሩና በህዝቡ መካከል መገንባት የነበረበት መርህ ያለው ግንኙነትም፣ መርህ የጎደለውና ለቀጣይ እድገትና ለውጥ አቅም የማይፈጥር አቅጣጫን ይዞ ሰንብቷል። የምንሰራውን እንደምንሰራ፣ የማንሰራውን ጊዜ እንደምንፈልግ በግልጽ ተናግሮ ከመታገል ይልቅ፣ የማይፈፀም ቃል መግባት ተስተውሏል። አልፎ አልፎም ከመደበኛው አሰራር ውጭ ከአመራሩ ይልቅ በሽማግሌዎችና በጉዳይ አስፈፃሚዎች አቤቱታ ላይ ተመስርቶ ውሳኔ መስጠት ትክክለኛ ያልሆነ የችግር አፈታት ስርዓት እንዲስፋፋ የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቷል።

 

የብዙሃንና የሙያ ማኅበራት፣ ልዩ ልዩ የህዝብ አደረጃጀቶች ነፃነታቸውን ጠብቀው የህዝብ መታገያ ተቋማት በሚሆኑበት ደረጃ ድጋፍ እንዳልተካሄደ ተረጋግጧል። ማኅበራዊ መሰረቶቻችንን ከሚያስቀይሙና በበጎ ተጽዕኖ ከሚፈፀሙ ተግባራት በላይ፣ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን የማያከብሩ ፀረ-ዴሞክራሲ አያያዞችም ተስተውለዋል። ይህንንም በአግባቡ የሚያርም ስራ ሳይሰራ ቆይቷል። የመንግስት አሰራር ተጥሶ በሕገ-ወጥነት ስራዎች ሲሰሩ አልታገለም፤ አይቶ እንዳላየ ያልፋል፤ ለምሳሌ ሕገ-ወጥ የቤቶች ግንባታዎች፣ እንዲሁም ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር በአካባቢው ሲታዩ ታግሎ የማስተካከል ችግሮች ታይተዋል። በየወቅቱ የሚታዩትን ችግሮች በመተራረምና በመገንባት መንፈስ ከማየት ይልቅ፣ የመጠቃቃትና ፀረ-ዴሞክራሲ የሆነ እንቅስቃሴ መካሄድም አልፎ አልፎ መታየት ጀምሯል።

 

ትክክለኛና ወቅታዊ ሁኔታዎችን በትክክለኛ ሃሳብ ከመግለፅ ይልቅ፣ ያልተገባ ድጋፍ መፈለግ እንደነበር ተገምግሟል። ለማኅበራዊ ህይወቱ የማድላት ሁኔታም የታየ ጉዳይ ነው። አልፎ አልፎ በሂስና በሂስ መልሶች በፀረ-ዴሞክራሲና በሚያሸማቅቅ ሁኔታ ገልብጦ የመገምገም ዝንባሌዎች የፀረ-ዴሞክራሲ መገለጫዎች ነበሩ።

 

በዘረኝነት የማገለፅ ፀረ-ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብና ተግባርም ሌላው መገለጫ ነው። ብዝሃነት በሰፈነባት ክልላችንና አገራችን በማንነት ላይ ተመስርቶ ማቅረብና ማራቅ ፍፁም ፀረ-ዴሞክራሲ ከመሆኑም በላይ፣ ለህዝቦች አንድነት እንቅፋት ነው። በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና አባላት ቀላል ባልሆነ ደረጃ ለዚህ ዓይነት መጥፎ በሽታ ተጋልጠው መገኘታቸው ምን ያህል አደገኛ እንደሆነ ታይቷል።

 

የትምክህት አስተሳሰብና ተግባር

ከመቼውም ጊዜ በላይ ገኖ የተስተዋለበት ወቅት

በተከታታይ በተካሄዱ የትግል መድረኮች፣ አንድ ወቅት ወደ ዳር ተገፍቶ የነበረው ትምክህት፣ ትግሉ መቀዛቀዝ ባሳየበት ወቅት ህዝብን ከህዝብ የሚያፋጅ የመድረኩ ቀንደኛ ጠላት ሆኖና ገኖ የታየበት ሁኔታ ነው የነበረው። አመራሩ በየወቅቱ በውስጡም ሆነ በኅብረተሰቡ መካከል የሚታዩ ችግሮችን እየታገለ ባለመሄዱ፤ የትምክህት አስተሳሰቡ እየሰረፀው ሂዶ የተዛባ አስተሳሰብና ተግባር ውስጥ ወድቆ ሰንብቷል።

 

በአማራ ጠገዴና በትግራይ ፀገዴ ወረዳዎች መካከል የተነሳውን የወሰን ማካለል ጥያቄ፣ በአግባቡና በወቅቱ ለመፍታት ከመንቀሳቀስ ባሻገር የትምክህት አስተሳሰብ የተጠናወተው አስተሳሰብና ተግባር ጐልቶ ወጥቷል። ጉዳዩ በሁለት ወረዳዎች መካከል በጥቂት አዋሳኝ ስፍራዎች ላይ ያለ ሆኖ ሳለ፣ ከደረጃውና ከጉዳዩ ልክ በላይ ተጋኖ እንዲታይ አድርጓል።

 

የቅማንት ብሔረሰብ የማንነትና የራስ አስተዳደር ጥያቄን በወቅቱ አይቶ በዴሞክራሲያዊ አግባብ መፍታት ሲገባው፣ የትምክህት አስተሳሰብና ተግባር በመበራከቱ ምክንያት በወቅቱ ሳይፈታ ከመቅረቱም በላይ ብዙ ጉዳት ደርሷል። ከወልቃይት ህዝብ ማንነት ጋር ተያይዞ በተነሳው ውዝግብም አመራሮችና አባላት ቀጥታ በማያገባቸው ጉዳይ ገብተው ህዝብን ለጉዳት የዳረጉበት እንደሆነ በግምገማ ተረጋግጧል። በወልቃይት ማንነት ዙሪያ ባለቤቶቹ ከቦታው እያሉና ጥያቄ ካላቸው በራሳቸው ታግለው መብታቸውን ሊያስከብሩ እየቻሉ፣ የሌሎች አጀንዳ በሆነ ጉዳይ ተስቦ በመውጣት ወይንም ቀጥተኛ አግባብ በሌለው ጉዳይ ውስጥ ገብቶ አካባቢን የሚያተራምስ መጥፎ ውድቀት ውስጥ እንደገባ በግምገማችን ተረጋግጧል።

 

አመራሮችም ሆኑ አባላት በተዛባ መረጃ ላይ ተመስርተው እህት ድርጅቱን ተጠራጥረዋል። የአፈፃፀም ችግሮችን በማንሳት ዴሞክራሲያዊና ፀረ-ዴሞክራሲያዊ ኃይሎችን ቀላቅለው ተመልክተዋቸዋል። የትምክህት ኃይሉ አመራሩን ለመከፋፈል ሲንቀሳቀስ የጠላትን አስተሳሰብ ተሸክሞ አራግቧል። ተደራጅቶ መመከትና መታገል ሲገባው፣ አይቶ እንዳላየ በተደራዳሪነት ተመልክቷል። ከሁሉም ብሔሮች የተነሱ ጥገኞችን በኩል መዋጋት ሲገባው “የእኛና የእኛ ያልሆነ” በሚል ሸፍኖ የመሄድ አስተሳሰብ፣ የአመራሩ ትምክህተኛ አመለካከትና ተግባር አንድ ማሳያ ሆኖ ታይቷል። የራሱን ብሔር ጥገኞች የቅድሚያ ትኩረት ሰጥቶ በሚፈለገው ደረጃ አልታገለም። በህዝባችን መካከል ዴሞክራሲያዊ አንድነት እንዲጠናከር የሰራው ስራ ደካማ ነው። ብዝሃነትን የማይቀበሉና የዴሞክራሲያዊ አንድነት እንቅፋት የሆኑ አስተሳሰቦችንና ተግባራትን በብቃት አልታገላቸውም። የአክራሪነትና የጠባብነት አመለካከቶችና ተግባራት፣ ከባቢያዊነትና ጎጠኝነት በተለያዩ ደረጃዎች የሚስተዋሉ ሲሆን፣ እነዚህን ችግሮች የታገለበት አግባብም ወጥነት አልነበረውም።

 

በየተቋሞቹ የትምክህት አስተሳሰቡ በስፋት ገኖ ሲወጣ፣ ከፍተኛ አመራሩ በራሱ የሚታየው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ የመታገልና የማስተካከል ሁኔታው ከአመራር በሚጠበቅ ቁመና አልነበረም። አክራሪነትን አጥብቆ በመታገልና ከመሰረቱ አስተሳሰቡንና ተግባሩን ለማጥፋት ወጥና ጠንካራ እንቅስቃሴዎችን አላካሄደም። ትምክህት በአስተሳሰብም፣ በተግባርም ጣራ ነክቶ ችግር እየፈጠረ በነበረበት ወቅት አዲስ ነገር እንዳልተፈጠረ አድርጐ አቅልሎ የማየት ችግር ታይቶበታል። እነዚህ ችግሮች ተዳምረው ክልላዊና አገራዊ ህዝባዊ አንድነታችንን የጎዱ አደገኛ አዝማሚያዎች በመሆናቸው ለቀጣይ ትምህርት በሚሆን አግባብ መታረም አለባቸው።

 

የነዚህ ሁሉ ችግሮች መነሻ ምንጮችና መንስኤዎች

አመራሩ የያዘውን ህዝባዊ ኃላፊነት የህዝብ ኑሮ መለወጫ ማድረጉ ቀርቶ የስልጣን አተያዩና አጠቃቀሙ የተዛባ ሆኖ እንደሰነበተ በግምገማ ተለይቷል። አመራሩ ኃላፊነቱን የኑሮና አልፎ አልፎ የሀብት ምንጭ መሰረት አድርጎ የመጠቀም በአስተሳሰብና በተግባር የመውሰድ ዝንባሌ ተስተውሎበታል። ይህ ደግሞ ከህዝባዊ ወገንተኝነት መራቅና ከዓላማ ጽናት መጓደል ጋር የተያያዘ ችግር ሆኖ ተገኝቷል፤ በመሆኑም በተሀድሶ ንቅናቄ የተለዩትን ችግሮችና የችግሮቹን መንስኤዎች በብቃትና በኃላፊነት መንፈስ ተረድቶ ለውጥ ለማምጣት ቀጣይ ርብርብ ማድረግን ይጠይቃል።¾

አዲስ አበባና ኦሮሚያ አዲስ የድንበር ዉዝግብ ዉስጥ ገብተዋል ተባለ – ዋዜማ ራዲዮ

$
0
0

ዋና ከተማዋን የሚያዋስኑ ልዩ የኦሮሚያ ዞኖች ከአዲስ አበባ አጎራባች ክፍለ ከተሞች ጋር አዳዲስ የመሬት ይገባኛል ዉዝግብ ዉስጥ መግባታቸውን ከዋዜማ ምንጮች ባለፉት ተከታታይ ሳምንታት የተሰበሰቡ መረጃዎች አመለከቱ፡፡

 

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ የሰበታ ከተማ አስተዳደር ጀሞ ወረዳ አንድ ድንበር ላይ ይገኙ የነበሩና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የተመዘገቡ አርባ አምስት ነባር የመሬት ባለይዞታዎችን ከመሬቴ ተነሱልኝ አላውቃችሁም ብሏቸዋል፡፡

 

ነገሩ ያስደነገጣቸው ባለሐብቶች ይዞታቸው ለሚገኝበት የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለአቶ ፍጹም ካህሳይ አቤቱታቸውን ያቀረቡ ሲኾን ከአቤቱታ አቅራቢዎች ዉስጥ በኦሮሚያ ግብረኃይል መጋዘኖቻቸው የፈረሱባቸው ዜጎች እንደሚገኙበት ተመልክቷል፡፡

 

የክፍለ ከተማው ሥራ አስፈጻሚና አመራሮቻቸው በዚህ እንግዳ ክስተት ዙርያ አስቸኳይ ዝግ ስብሰባ ማካሄዳቸው የተሰማ ሲኾን በነገታው ባለይዞታዎቹን በመሰብሰብ ለአጭር ሰዓት አወያይተዋቸዋል፡፡ ችግሩ ፖለቲካዊ መልክ ስላለው በአጭር ጊዜ ሊቀረፍ የሚችል እንዳልሆነ ጠቆም የተደረጉት ባለጉዳዮቹ ችግሩን ለመፍታት ከሰበታ አስተዳደር ጋር በተከታታይ መነጋገርን እንደሚጠይቅ ተብራርቶላቸዋል፡፡

 

ሥራ አስፈጻሚው አቶ ፍጹም ካህሳይ በበኩላቸው ጉዳዩን በግላቸው ይዘው ጊዜ ሳይሰጡ ከከንቲባው ጋር እንደሚነጋገሩበትና ባለይዞታዎቹ ለጊዜው በትዕግስት እንዲጠብቋቸው ተማጽነዋል ተብሏል፡፡ ነገሮች ካልተስተካከሉ ግን ሁሉም ባለይዞታዎች ተመጣጣኝ ቦታ በምትክነት እንደሚያገኙም ቃል ገብተውላቸዋል፡፡

 

ይዞታቸውን በይገባኛል ምክንያት በሰበታ ከተማ አስተዳደር የተቀሙ ባለይዞታዎች ዉስጥ ድርጅቶችና የሃይማኖት ተቋማት ይገኙበታል ፡፡ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለከፍተኛ ትምህርት ማዕከል ማሰሪያ በሚል የወሰደችው 15ሺ ካሬ ቦታም በሰበታ ከተማ አስተዳደር ከተወረሱት መሬቶች አንዱ ነው፡፡ ከድርጅቶቹና የሃይማኖት ተቋማት በተጨማሪ የአዲስ አበባ ሊዝ ጨረታን በማሸነፍ ቦታ የተረከቡ፣ ለግንባታ ጠጠርና አሸዋ በመድፋት ዝግጀት ሲያደርጉ የነበሩ፣ ለቁሳቁስ ማስቀመጫ መጋዘን የገነቡ፣ ለንግድና ኢንደስትሪ ቦታ የወሰዱ ባለሐብቶችና ቤት ገንቢ ነዋሪዎች ይገኙበታል፡፡

 

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባልተለመደ ሁኔታ በአዲስ አበባ ዙርያ የሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ዞኖች በተለይም ባለፉት ሳምንታት በአዲስ አበባ የድንበር መሬት ላይ ተከታታይ የይገባኛል ጥያቄ በማንሳት ላይ ይገኛሉ፡፡ ጥያቄው ለምን በዚህ ጊዜ በተመሳሳይ ሁኔታ ተከሰተ ለሚለው አጥጋቢ ምላሽ ማግኘት ባይቻልም ከምሥራቃዊ አዲስ አበባ ዉጭ በሚገኙ በሁሉም የአዲስ አበባ አጎራባች የኦሮሚያ ልዩ ዞኖች ባለፉት ሦስት ሳምንታት ብቻ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ከሚያጎራብቷቸው ክፍለ ከተሞች ጋር በቁራሽ መሬት ዙርያ መለስተኛ እሰጥ አገባ ዉስጥ ገብተዋል፡፡

 

ዋዜማ ከአቃቂ ቃሊቲ፣ ከንፋስ ስልክና ከኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተሞች በሳምንታት ልዩነት የሰበሰበቻቸው መረጃዎች እንደሚያሳዩት ቡራዩ፣ ሱሉልታ፣ ገላን፣ ሰበታና ዓለም ገና በአጎራብቷቸው የከተማ ማዋቅሮች ላይ ጥያቄን አንስተዋል፡፡ ይህ የይገባኛል ጥያቄ እንዴት በተመሳሳይ ጊዜ ሊከሰት ቻለ? ነገሩ አጋጣሚ ነው ወይስ አይደለም? ለሚለው መላምት እርግጡን ምላሽ ማግኘት አዳጋች ኾኗል፡፡

 

ምናልባት ጉዳዩ በኦህዴድ ከፍተኛ አመራሮች ዘንድ ዉስጥ ዉስጡን ሲብሰለሰል የቆየና የኦሮሞ ብሔርተኝነትን ፈራ ተባ እያለም ቢኾን ማቀንቀን በጀመረው የአቶ ለማ መገርሳ ካቢኔ የተቀነባበረ ሴራ ሊሆን እንደሚችል የሚገምቱ አልጠፉም፡፡ ይኸውም በቅርቡ ኦሮሚያ ከአዲስ አበባ ማግኘት በሚኖርባት ልዩ መብትና ጥቅም ላይ ይደረጋል ተብሎ በሚጠበቀው ድርድር ላይ ተጨማሪ ጫና ለመፍጠር ታስቦ ሊሆን እንደሚችል የጠረጠሩም ጥቂት አይደሉም፡፡

 

የአዲስ አበባ ደቡባዊው ክፍል በተለይም አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ እንዲሁም ደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ የሚገኘው የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ከሰበታና ከገላን የኦሮሚያ ልዩ ዞኖች ጋር የሚለየው ትክክለኛ ድንበር የት እንደሆነ አይታወቅም፡፡ በሰሜን አዲስ አበባም ተመሳሳይ ችግር ይስተዋላል፡፡ ከተማዋ የተሻለ ተፈጥሯዊ ድንበር አላት የሚባለው በምሥራቅ አቅጣጫ በጣፎ በኩል ከቦሌና ከየካ ክፍለ ከተሞች ጋር ያለው ሸለቆ ነው፡፡ በምዕራብ አቅጣጫ ኮልፌ ቀራንዮን የሚያዋስነው የኦሮሚያ ልዩ ዞንም ቢኾን የድንበር ጥያቄ ይነሳበታል፡፡ ቡራዩን ኮልፌ ቀራንዮ ዉዝግብ ተለይቷቸው አያውቅም፡፡

 

ከሰባት ዓመታት በፊት በምዕራብ አዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ አንፎሜዳ በሚባል ሰፈር ተመሳሳይ የይገባኛል ጥያቄ በቡራዩና በኮልፌ ቀራንዮ መሐል መነሳቱ ይታወሳል፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎችም በየትኛው ክልል ዉስጥ እንደምንገኝ በግልጽ ይነገረን የሚል ጥያቄ ገፍተው ማንሳታቸውን ተከትሎ በአቶ ኩማ ደመቅሳና በአቶ አባዱላ ገመዳ የሚመራ ልዩ ኮሚቴ በወርሃ ታኅሳስ 2002 ዓ. ም በአካባቢው በመገኘት ጉብኝት ማድረጉ ይታወሳል፡፡

 

ኾኖም በወቅቱ ይህ ነው የሚባል መፍትሄ ሳይሰጥ ቆይቷል፡፡

 

ከአካባቢው ነዋሪዎች መሐል ከፊሎቹ ፋይላቸው በኦሮሚያ ልዩ ዞን ሲገኝ ሌሎች ደግሞ ተጠሪነታቸው ለኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ነው፡፡ በርካታ የቤት ማኅበራት በከንቲባ ብርሃነ ደሬሳ ዘመን አንፎሜዳ አካባቢ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤቶችን ለመገንባት ቦታ ወስደው የነበረ ሲኾን ግንባታ ለመጀመር በዝግጅት ላይ ሳሉ ግን የቡራዩ ከተማ አስተዳደር በኦሮሚያ መሬት ላይ መገንባት አትችሉም በሚል ግንባታው እንዲቆም አድርጎ ነበር፡፡

 

በተመሳሳይ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ የሚተዳደረውና ሰፊ የቆዳ ስፋት እንዳለው የሚነገረው ኤርቶሞጆ የሚባለው ሰፈር የኦሮሚያ እንደኾነ ቢታመንም የአዲስ አበባ መስተዳደር ትልቁን የ20/80 የጋራ መኖርያ ቤት እውን ሊያደርግበት እየተዘጋጀ ያለ ቦታ ኾኖ ቆይቷል፡፡ ኾኖም ከሰሞኑ እንደተሰማው ከኾነ የኦሮሚያ ክልል የኤርቶሞጆ የቤቶች ፕሮጀክት ጉዳይ የአዲስ አበባ መስተዳደር በይደር እንዲያቆየው ጥያቄ ማቅረቡ ተሰምቷል፡፡

 

ሪፖርተር ጋዜጣ ከአንድ ወር በፊት በሠራው ዘገባ ከአዲስ አበባ መስተዳደር መሬት የወሰዱ 38 ባለሐብቶች የተረኩቡት ቦታ በሰበታና ገላን ከተሞች የይገባናል ጥያቄ ስለተነሳበት ለዓመታት ሲጉላሉ መቆየታቸውን ጠቅሶ የድንበር ጉዳይ እልባት እስኪያገኝ ድረስ የሁሉም ባለሐብቶች ፋይል ወደ ኦሮሚያ እንዲዛወር መወሰኑን አስነብቦ ነበር፡፡

 

በአዲስ አበባ መስተዳደር መዋቅር ዉስጥ በመካከለኛ የኃላፊነት ደረጃ ላይ በማገልገል ላይ የሚገኙ አንድ የመሬት ልማት ባለሞያ ለዋዜማ እንደተናገሩት የማስተርፕላኑ እስከዛሬ ያለመጽደቅ ዋንኛው ምክንያት ተመሳሳይ የድንበር ጉዳዮች አልባት ባለማግኘታቸው እንደሆነ ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡ እንደርሳቸው ገለጻማስተርፕላኑ የኦሮሚያ ያደረጋቸውና በአዲስ አበባ የሚተዳደሩ፣ ማስተርፕላኑ የአዲስ አበባ አካል ያደረጋቸውን በኦሮሚያ የሚተዳደሩ ወረዳዎች በርካታ ናቸው፡፡ “ይህ እልባት ሳያገኝ ማስተርፕላኑ የሚፀድቅ አይመስለኝም” ብለዋል፡፡

 

አዲስ አበባ ቀድሞ ከነበራት 54ሺ ሄክታር የቆዳ ስፋት ይጸድቃል ተብሎ በሚጠበቀው 10ኛው ማስተርፕላን 2ሺህ ሄክታር ያህል ቀንሳ መገኘቷን መዘገባችን ይታወሳል፡፡


አብዮተኞቹ በታሪክ ውስጥ – በጥበቡ በለጠ

$
0
0

በጥበቡ በለጠ / ሰንደቅ
የካቲት ወር በኢትዮጵያ ውስጥ ባለታሪክ ነው። የየካቲት አብዮት እየተባለ በታሪክ ውስጥ ይነገራል። ያ አብዮት 43 አመት ሆነው። ያ አብዮትን የሚያስታውሱ መጻሕፍትም ከ43 በላይ ሆነዋል። የካቲት ወር ማለቂያው ላይ ሆነን ወደ ኋላ ሄደን የኢትጵያን አብዮት በጥቂቱ እናስታውሰው። የኛ ታሪክ ነው። ያለቅንበት፣ የደማንበት፣ ብዙ ሰው የተሰደደበት፣ ምስቅልቅል የተጀመረበት ወር ነው። እናም ትንሽ ብንጫወትስ?

በኢትዮጵያ ውስጥ 1966 ዓ.ም “አብዮት ፈነዳ” ተባለ። የፈነዳው አብዮት አዲስ ስርዓት እንዲመሠረት የሚጠይቅ ነው። ሦስት ሺ ዓመታት ያህል በስልጣን ላይ ቆይቷል የተባለው ሰለሞናዊው የንግስና ዘመን ተገረሠሠ ተባለ። የመጨረሻው የሰለሞናዊ አገዛዝ መሪ የነበሩት ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ከመንበረ ስልጣናቸው ወረዱ። ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር (ደርግ) የሀገሪቱን አመራር ያዘው። ወጣቱ ደግሞ መሬት ለአራሹ ብሎ ዘምሮ ያመጣው ለውጥ በደርግ ወታደሮች ተቀማሁ ብሎ በኢሕአፓ ሥር ተደራጅቶ ከከተማ እስከ ጫካ ድረስ የትጥቅ ትግል ውስጥ ገባ። ሌሎችም ፓርቲዎች ደርግን ለመዋጋት ተፈጠሩ። በዘር፣ በሃይማኖት እና ኅብረ ብሔራዊ ሆነው የተደራጁ ፓርቲዎች መጡ። 17 ዓመታት አንዱ በአንዱ ላይ የበላይ ለመሆን የማያቋርጥ ጦርነት ተከፈተ። ኢትዮጵያዊያኖች በአያሌው ደማቸው ፈሰሰ። ህይወት ጠፋ። ለውጥ በመምጣቱ ምክንያት ትውልድ ረገፈ። የመጣው ለውጥ በተደራጀ መልኩ ባለመያዙ የትውልድ ሰቆቃ ታይቶበት እንዳለፈ ፀሐፍት ያስረዳሉ።

 

ለመሆኑ አብዮት የት እና መቼ መቀጣጠል ጀመረ ተብሎ መጠየቁ አይቀርም። የኢትዮጵያ አብዮት መቀጣጠል የጀመረው በስነ-ጽሁፍ ውስጥ እንደሆነ የሚያስረዱ አያሌ መዛግብት አሉ። እነዚህ አብዮታዊ ሥነ-ጽሁፎች መውጣት የጀመሩት ደግሞ 1950ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ እንደሆነም ይጠቀሳል።

 

አብዮት አቀጣጣዩ ትውልድ ብቅ ያለው ከኢጣሊያ ወረራ በኋላ ት/ቤት ገብቶ የተማረው ነው። በ1930ዎቹ አጋማሽ ውስጥ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ለትምህርት ከፍተኛ ትኩረት የሰጡበት ወቅት ነበር። በዚህ ጊዜም ወደ ተማሪ ቤት የገቡት ልጆች አያሌ ድጋፍ እያገኙ መማር ጀመሩ። እነዚህ ትውልዶች በ1950ዎቹ ውስጥ ትምህርታቸውን እያጠናቀቁ በልዩ ልዩ የሙያ መስክ ውስጥ መሰማራት ጀመሩ። እጅግ የካበተ የሥነ-ጽሁፍ ችሎታ ያላቸው ደራሲያን የተፈጠሩበት ዘመን ሆነ። በስዕል፣ በሙዚቃ፣ በጋዜጠኝነት እና በሁሉም የሙያ መስኰች ጥሩ እውቀት ያላቸው ወጣቶች ብቅ አሉ።

 

በሥነ-ጽሑፍ ውስጥ የአብዮት አቀጣጣይ ሆነው ብቅ ካሉት ፀሐፍት መካከል አንዱ ፀጋዬ ገ/መድህን ነው። ፀጋዬ አንድ የቆየን ታሪክ በከፍተኛ ሁኔታ ቀየረው። ይህም የአፄ ቴዎድሮስን የህይወት ታሪክ ነው። ከፀጋዬ በፊት የነበሩት አያሌ ፀሐፍት አፄ ቴዎድሮስን የሳሏቸው ጨካኝ፣ ብዙ ሰው የገደሉ፣ ትዕግስት የሌላቸው እና ብዙ ጥፋት ሰርተው ያለፉ ንጉስ መሆናቸውን ይገልፁ ነበር። በ1940ዎቹ መጨረሻ ግን ደጃዝማች ግርማቸው ተክለሃዋርያት “ቴዎድሮስ ታሪካዊ ድራማ” የተሰኘ ቴአትር ፃፉ። ይሄ ቴአትር ቴዎድሮስ ራዕይ የነበራቸው ጠንካራ ንጉስ መሆናቸውን አሳየ። ከዚህ በኋላ ደግሞ ፀጋዬ ገ/መድህን ቴዎድሮስ ፍፁም ኢትዮጵያን የሚወዱ፣ ኢትዮጵያን በአንድነትና በስልጣኔ ሊያራምዱ ቆርጠው የተነሱ፣ የለውጥ ሐዋርያ የሆኑ የጀግንነት ተምሳሌት ናቸው በሚል ቴዎድሮስን ሰማየ ሰማያት አድርጐ አቀረባቸው።

 

በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን የቴዎድሮስ ታሪክ እምብዛም አይነገርም ነበር። ምክንያቱም ቴዎድሮስ ከሰለሞናዊያን ነገስታት የዘር ሐረግ የላቸውም። ከሽፍትነት ተነስተው አሸንፈው ንጉስ የሆኑ ናቸው። ስለዚህ በዘር ሐረግ ስልጣን በሚተላለፍበት ዓለም ቴዎድሮስ ጥሩ ምሳሌ አይደሉም። ሽፍታ ሀገር መምራት ይችላል የሚል ትርጓሜ ያሰጣል። አንድ ሰው ጫካ ገብቶ (ሸፍቶ) ከተዋጋ እንደ ቴዎድሮስ መንግስት መሆን ይችላል። ስለዚህ በዘመነ አፄ ኃይለሥላሴ ቴዎድሮስን ማቆለጳጰስ ስርዓቱን እንደመቃወም ሁሉ የሚቆጠርበት ሁኔታም ይታያል። በዚህ ሁኔታ ውስጥ ነው ፀጋዬ የአፄ ቴዎድሮስ ታሪክ ለትውልድ ሁሉ አርአያ እንደሚሆን አድርጐ የፃፈው።

 

ፀጋዬ በአፄ ቴዎድሮስ በኩል ትግልን፣ ፅናትን፣ ሀገርን መውደድ፣ ለሀገርም መስዋዕት መሆንን ሁሉ አስተማረበት። በወቅቱ አዲስ አስተሳሰብ በትውልድ ውስጥ የሚዘራ አፃፃፍ ነው። ቴዎድሮስን ብሔራዊ አርማ የማድረግ አቀራረብ ተጀመረ። አፄ ቴዎድሮስ የትግል መማሪያ ሆኑ።

 

ልክ እንደ ፀጋዬ ገ/መድህን ሁሉ ብርሃኑ ዘሪሁንም ቴዎድሮስን ብሔራዊ አርማ አድርጐ ፃፋቸው። የብርሃኑ ቴአትር “የቴዎድሮስ ዕንባ” ይሰኛል። ብርሃኑም በራሱ ውብ የአፃፃፍ ቴክኒኩ ታላቁን አፄ ቴዎድሮስ የጀግኖች ሁሉ ቁንጮ አድርጐ አቀረበው። ቴዎድሮስ ሰዎችን ይቀጡ የነበሩት ጨካኝ ስለሆኑ ሳይሆን ሀገራቸውን በጣም ስለሚወዱ ነው። በሀገር ላይ ጥፋት የሰራን ሰው አማላጅ የላቸውም፤ ይቀጣሉ፤ ይገድላሉ። እነዚህ ላይ አትኩሮ ታላቁ ደራሲ ብርሃኑ ዘሪሁን ፃፈ።

 

ከነ ፀጋዬ በፊት በነበሩት ፀሐፍት እንደ ሽፍታ እና ጨካኝ መሪ ይታዩ የነበሩት ቴዎድሮስ፣ አሁን ርህራሄያቸው እና አዛኝነታቸው እንዲሁም አርቆ አሳቢነታቸው እየተገለጠ መታየት ጀመረ። ለምሳሌ ቴዎድሮስ ወደ ሸዋ መጥተው፣ የሸዋን መንግስት ከጣሉ በኋላ የ12 ዓመት ልጅ የነበሩትን የንጉስ ልጅ (ምኒልክን) ማርከው አልገደሏቸውም። የጠላቶቼ ልጅ ነው ብለው አላሰቃዪዋቸውም። ከቴዎድሮስ በፊት የነበሩት ነገሰታት ልጆቻቸው ስልጣናቸውን እንዳይወርሷቸው ሁሉ ይጠነቀቁ ነበር። ቴዎድሮስ ግን የጠላቶቼ ልጅ ነው ብሎ ሳያስብ ምኒልክን ወደ ጐንደር ወስዶት እንደ ራሱ ልጅ በስርዓት አሳደገው። “ወደፊት ኢትዮጵያን የምትመራ አንተ ነህ” ብሎ አስተማረው። ስለዚህ ቴዎድሮስ ጨካኝ መሪ ሳይሆን ልበ ቀና ሆኖ ኢትዮጵያን የሚወድ ነው እያሉ እነ ፀጋዬ ገ/መድህን ፃፉ።

 

ይሄን የአፃፃፍ መንገዳቸውን የበለጠ ተወዳጅ ያደረገ ደራሲ ደግሞ ብቅ አለ። አቤ ጉበኛ ነው። ስለ አፄ ቴዎድሮስ ማንነት የምርጦች ምርጥ የሚሰኝ መጽሐፍ በ1950ዎቹ ውስጥ አሳተመ። የመጽሐፉ ርዕስ አንድ ለእናቱ ይሰኛል። ታሪካዊ ልቦለድ ነው። የቴዎድሮስን ማንነት ከውልደት እስከ ፍፃሜ ፍንትው አድርጐ የሚያሳይ ነው። የአቤ ጉበኛ አፃፃፍ ቀላል እና ማራኪ በመሆኑ በአብዛኛው ኢትዮጵያዊ ልብ ውስጥ ቴዎድሮስ እንዲሸሸግ አደረገ። ‘ቴዎድሮሳዊነት’ እንደ ፍልስፍና ብቅ አለ። ታግሎ ማሸነፍ፣ ተደራጅቶ መነሳት፣ አለመፍራት፣ ወዘተን ማስተማሪያ ሆነ። ቴዎድሮሳዊነት የለውጥ ማቀንቀኛ ሆኖ ወጣ!

ይህን የእነ ፀጋዬ ገ/መድህንን፣ የእነ ብርሃኑ ዘሪሁንን፣ የእነ አቤ ጉበኛን እንዲሁም የደጃዝማች ግርማቸው ተ/ሐዋርያት አፃፃፍን መሠረት አድርጐ ታላቁ ደራሲ በዓሉ ግርማ በዚያን ዘመን አንድ ሰፊ መጣጥፍ (ሂስ) ፃፈ። ጽሁፉ የሚያተኩረው ቴዎድሮስ ከ100 ዓመት በኋላ በእነ ፀጋዬ ገ/መድህን አማካይነት እንደገና መወለዱን ነው። እነዚህ ደራሲያን ያልታየውን ቴዎድሮስ ፈጠሩት እያለ አቆለጳጰሳቸው።

የለውጥ ማቀጣጠያ ጀግና ተፈጠረ። ቴዎድሮስ ፍልስፍና ሆኖ መታገያ ማታገያ እየሆነ መጣ። በዚሁ ዘመን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ብዕሮች ስለ የለውጥ ማቀጣጠያ ቀለም መትፋት ጀመሩ። ዮሐንስ አድማሱ፣ ዳኛቸው ወርቁ፣ ኃይሉ ገ/ዮሐንስ (ገሞራው)፣ ኢብሳ ጉተማ፣ ታምሩ ፈይሣ፣ አበበ ወርቄ፣ ይልማ ከበደ እና ሌሎችም በርካታ ገጣሚያን በዩኒቨርሲቲ ውስጥ አብዮት አቀጣጣይ ግጥሞችን መፃፍ ጀመሩ። ዘመኑም ከ1953 ዓ.ም በኋላ ነው።

“የዩኒቨርሲቲ ቀን” ተብሎ በተሰየመው ዕለት የግጥም “ናዳዎች” መቅረብ ጀመሩ። ግጥሞቹ በዘመኑ በማኅበረሰቡ ውስጥ የሚነሱትን ልዩ ልዩ ችግሮች እያነሱ የሚያቀጣጥሉ ናቸው። ግጥሞቹ ሲነበቡ በተማሪው ዘንድ ከፍተኛ የጭብጨባ እና የድጋፍ ድምፅ ይሰነዘር ነበር። ለምሳሌ በ1953 ዓ.ም ታመሩ ፈይሳ የተባለ የዩኒቨርሲቲ ገጣሚ ለተማሪዎች ያቀረበው ግጥም ከዳር እስከ ዳር እንዳነቃነቀ እማኞች ያስረዳሉ። የታምሩ ግጥም “ደሃው ይናገራል” የሚል ርዕስ ነበራት። እንዲህም ትላለች፤

ግማሽ ጋሬ እንጀራ እጐሰጉስና

አንድ አቦሬ ውሃ አደሽ አደርግና

ሣር እመደቤ ላይ እጐዘጉዝና

ድሪቶ ደርቤ እፈነደስና

ተመስገን እላለሁ ኑሮ ተገኘና

ጮማና ፍሪዳ የት ነው የማውቀው

እንዲሁ አሸር ባሸር ሆዴን አመሰው

የእግዜር ፍጡር ነው ትላላችሁ ወይ

ምስጥ የበላው ዝግባ መስዬ ስታይ

ይህችም ኑሮ ሆና በጉንፋን አሳቦ

ከዚሁ ገላዬ፣ ከዚሁ አካላቴ፣ ከዝችው አቅም

ልክ እንቧይ ያህላሉ ቁንጫና፣ ትኋን፣ ቅማል በእኔ ደም!

እያለ ታምሩ ገጠመ። የለውጥ ቋፍ ላይ የነበረው ተማሪ ደስታውን አስተጋባ። ኢብሳ ጉተማ የተባለ ገጣሚም በይዘቷ ለየት ያለች ግጥም አቀረበ። ርዕሷ “ኢትዮጵያዊ ማን ነው?” የሚል ነበር። አንዳንድ ሰዎች ግጥማ ዘመን አይሽሬ ናት። ኢብሳ ጉተማ ግን ዘመን ሽሮት የአንድ ፓርቲ አባል ሆነ እያሉ ይገልፃሉ። የግጥሟ ከፊል ገፅታ እንዲህ ይላል።

ያገር ፍቅር መንፈስ ያደረበት ሁሉ

ማንነቱን ሳያውቅ በመንቀዋለሉ

ማነኝ ብሏችኋል መልሱን ቶሎ በሉ፣

እናንተ ወጣቶች ኢትዮጵያዊ ማን ነው?

ከሆዱ ያበጠ ቦርጫም መኰንን ነው?

ወይስ ኰሰስ ያለው መናጢ ድሃ ነው?

ላቡን አንጠፍጥፎ ከመሬት ተታግሎ

ካገኘውም ሰብል ለጌቶች አካፍሎ

ለራሱ ከእጅ ወደ አፍ የሚያስቀረው ነው?

በሉ እስቲ ንገሩኝ ኢትዮጵያዊ ማን ነው?

የመንግስቱ ደም ስር የህዝቡ አከርካሪ

በመከራ ጊዜያት አደጋ ከማሪ

በሰላም ወራት ሌሎችን አኩሪ

ገበሬው ነው ወይ የመታው ሐሩር?

ኢትዮጵያ ለእናንተ የማናት ሀገር?

ወሎዬ ነው አማራው ትግሬ ነው ጉራጌ?

ወላይታ ነው ኰንታው አኙዋኩ ነው ጉጂው?

ጭንቅ ብሎኛል ኢትዮጵያዊ ማን ነው?

ወጣት ሽማግሌው አገር ሲጠየቅ

አንዱ ጐጃም ነኝ ሲል ሌላው በጌምድር

አንዱ ኤርትራ ሲል ሌላው ተጉለት

አንዱ መንዝ ነኝ ሲል ሌላው ጋሙ ጐፋ

ኢትዮጵያዊ ነኝ ባይ ብፈልገው ጠፋ።

እስቲ አዋቂዎች እናንተ ንገሩኝ

እኔን ያስጨነቀው ኢትዮጵያዊ ማን ነው?

ኢብሳ ጉተማ እንዲህ ያለ ኢትዮጵያዊ ገጣሚ ነበር። ይህ ኢትዮጵያዊነቱ በ1950ዎቹ መግቢያ ላይ እየተንተገተገ ፈልቶ ነበር። ዛሬ ያለችው ኢትዮጵያም በዚህ ግጥም ውስጥ ትታያለች። ግን በዘመኗ አብዮት አቀጣጣይ ግጥም ነበረች። ሀሳቧ ዘላለማዊ ነው።

በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ከተነሱት አብዮት አቀጣጣይ ትውልዶች አንዱ ኃይሉ ገ/ዮሐንስ (ገሞራው) ነው። ዛሬም ድረስ በስደት የሚንከራተተው ይህ ገጣሚ በ1954 ዓ.ም ትንታግ እና የሚቀጣጠል ግጥም ፅፎ በትውልድ ልብ ውስጥ ዘላለማዊ ሆኖ እየኖረ ነው። ኃይሉ “በረከተ መርግም” የተሰኘ ረጅም ግጥም ፅፏል። በዚህ ግጥም ውስጥ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን የፈለሰፉ ጠቢባንን የርግማን ናዳ ያወርድባቸዋል። እርግማኑ የሚያተኩረው ለሰው ልጅ ጥቅም የማይሰጥ ፍልስፍና ድራሹ ይጥፋ እያለ ነው። ግጥሙ ረጅም ነው። በጣም ጠቂቱ ይህን ይመስላል፤

ሆኖም ምስጢሩ፣ ባይገባንም ለአያሌ ዘመናት

በአንክሮ ምጥቀት፤ ስናየው የኖርነው

ሲነድ ሲቃጠል፣ የሚስቅ እሣት ነው

ርግጥ ነው ክብሯን እውነት ነው ክብሯት

እኔ በበኩሌ አልወድም ነበረ ሰውን ያህል ፍጡር

ዳዊትና ዳርዊን ያፀደቁለትን ያንን ትልቁን ትል

መወረፍ መጣቆስ

ከምን ልጀምር፣ ከየትስ ልነሳ

በየግንባሩ ላይ ለጥፎ ለመኖር የትዝብት ወቀሳ

አዎን የተዛባን መንፈስ ያጐበጠ ኑሮ

የገለማን ህይወት፣ ምክንያቱ ሆነው ካስገኙ በዓለም

ተራው ምን አደረገ ሊቆቹን ነው መርገም።

እያለ የእርግማን አይነት ያወርዳል። የቀረው ሳይንቲሰት፣ የቀረው ፈላስፋ የለም። ኃይሉ ትልቅ ባለቅኔ ነበር። ደርግ ሲመጣ የተሰደደ እስከ ዛሬ አልተመለሰም። ወጥቶ የቀረው ባለቅኔያችን ነው። መቼ ይሆን የሚመጣው?

ሌላኛው አብዮት አቀጣጣይ ገጣሚ ዳኛቸው ወርቁ ነው። ዛሬ በህይወት የሌለው ዳኛቸው ከፍተኛ የሥነ-ጽሑፍ ችሎታ ያለው ምሁር ነው። የበርካታ መፃህፍት ደራሲ የሆነው ይህ ከያኒ በ1954 ዓ.ም “እምቧ በሉ ሰዎች” የሚሰኝ ረጅም ግጥም ጽፏል። 33 ገፅ የሆነው ይህ ግጥም ህዝብን የመቀስቀስ እና የማነሳሳት ባህሪ በስፋት አለው። “የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ካልተማርክ፣ ካላወክ፣ ካልተመራመርክ…. እንደ ከብቶቹ እምቧ በል” እያለ በሁለት በኩል በተሳለ የግጥም ቢለዋ ያስፈራራል። እናም ለእውቀት ተነስ! ወደ ኋላ አትበል ይላል፤

በድሎት ላሽቀን

መስራትም ማሰራት

ሁሉንም ካቃተን፣

ምነው ምናለበት

የፍጥፍጥ ሄደን

ያሮጌ ዓለም ህዝቦች

ብሎ ሰው ቢያውቀን

ሰው ሁሉ ሰልጥኖ ስልጣኔ ሲረክስ

ሌላ ዓለም ፈልጐ ባየር ላይ ሲፈስ

ደስታ አይደለም ወይ ለታሪክ መቅረት

እንደኛ ደንቆሮ ሆኖ መገኘት

እነዚህ ገጣሚያን በወጣትነት ያፍላ ዘመናቸው ለውጥ እያቀጣጠሉ የመጡ ናቸው። ዛሬ ወደ አሜሪካን ሀገር የሸሹት የሕግ ባለሙያው አበበ ወርቄም በ1958 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሳሉ ምላሴን ተውልኝ የሚልየዴሞክራሲ ጥያቄ ያነገበች ግጥም ፅፈዋል።

ከ1953 ነበልባል ከሆነው ትውልድ ውስጥ ጐልቶ የሚጠቀሰው ባለቅኔው ዮሐንስ አድማሱ ነው። የእርሱም ግጥሞች ኢትዮጵያን ለመቀየር ቆስቋሽ የሆኑ ጠንካራ ርዕሰ ጉዳዮችን የሚያነሱ ናቸው። እንዲህ እያለ ጉዞው ቀጠለ። መሬት ለአራሹ መጣ። የተማሪ አመፅ መጣ። የሰራተኛው፣ የጦር ኃይሉ አመፅ… እያለ ቀጠለ።

“አትነሳም ወይ አትነሳም ወይ

ይህች ባንዲራ ያንተ አይደለችም ወይ”

ተባለ።

ፋኖ ተሰማራ

ፋኖ ተሰማራ

እንደ ሆቺ ሜኒ

እንደቼኩ ቬራ

አብዮት ተቀጣጥሎ ምርጥ የኢትዮጵያን ወጣት ልጆች ፈጅቶ ሄደ። የካቲት እንዲህ አይነት ታሪክ አላት። ብዙዎች ስለ የካቲት ጽፈዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ኤርትራን አርበኞች ግንቦት ሰባትን ኢሳትንና ኦ ኤም ኤንን የተመለከተ አዲስ ዕቅድ እያዘጋጀ ነው

$
0
0

ዋዜማ ራዲዮ- የኢትዮጵያ መንግስት “የደህንነት አደጋ ደቅነውብኛል በሀገሪቱ ስላምና መረጋጋትን አናግተዋል” ያላቸውን ሀይሎች ለመፋለም እየተዘጋጀ መሆኑን በገዥው ፓርቲ ዙሪያ ላሉ ቁልፍ ሹማምንትና ለደህንነት አካላት ሹክ ብሏል።

ኢህአዴግ በተለይ በአማራና ኦሮምያ ክልሎች ተከስቶ የነበረው ህዝባዊ አመፅ እንዳይደገም ይረዱኛል ያላቸውን እርምጃዎች በሁለት ዘርፍ ከፍሎ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰናዳ መሆኑንም ለዋዜማ የደረሰ መረጃ ያመለክታል። ከእርምጃዎቹ አንዱ በኤርትራ ላይ የሚከተለውን ፖሊሲ መለወጥና በአስመራ ላይ ስልታዊ እርምጃ መውሰድ እንዲሁም በውጪ ሀገር ያሉ ተቃዋሚዎችና ሚዲያዎችን በህግ ፊት ማቅረብና ማዘጋትን ያካትታል። አርበኞች ግንቦት ሰባትና ኦነግ እንዲሁም ኢሳትና ኦ ኤም ኤን የአዲሱ የመንግስት ጥቃት ኢላማ መሆናቸውን የመንግስት የቅርብ ምንጮች አረጋግጠዋል። በኤርትራ ላይ የተዘጋጀው አዲስ ዕቅድ በቅርቡ ለህዝብ ይፋ የሚደረግ ሲሆን በሌሎቹ ጉዳዮች ላይ አለማቀፍ አማካሪ ለመቅጠርና የምዕራባዉያንን ትብብር ለመጠየቅ ዕቅድ ተይዟል። [ይህን ጉዳይ በተመለከተ  ዘርዘር ያለ ማብራሪያ ከታች በድምፅ ያገኛሉ]

ዋዜማ  ከተለያዩ ምንጮች እንዳረጋገጠችው በኤርትራ ላይ የተያዘው ዕቅድ በተወሰኑ የፓርቲ ሹማምንት ሰፊ ክርክር የተደረገበት ሲሆን በዕቅዱ ዙሪያ የሀሳብ ልዩነት አለን ያሉ ባለስልጣናት ዕቅዱ በድጋሚ ይከለስ የሚል ሀሳብ አቅርበዋል። ከአንድ ወር በፊት ጀምሮ በተደረገውና በቅርቡም በቅንጭብ ለካቢኔ አባላት እንደተነገራቸው፣ ዕቅዱ ተግባራዊ ሲሆን ከኤርትራ ጋር ወደ ለየለት ጦርነት ሊያስገባ ይችላል የሚል ስጋት አለ።
የአረብ ሀገራት የድርድር ጥያቄ በተደጋጋሚ አቅርበው የአስመራ መንግስት እንዳልተቀበለው የሚገልፁ አንድ ሹም ኤርትራን አስገድዶ ወደ ድርድር ማምጣት የዕቅዱ አንድ አካል ነው ይላሉ።
ይህ ካልሆነ በኤርትራ የሰርዓት ለውጥ እንዲመጣ በተለየ መልኩ ለመስራት መታሰቡንም ሹሙ ነግረውናል።
የአሜሪካ የኮንግረስ አባላትና ወታደራዊ አታሼዎች በቅርቡ ወደ አዲስ አበባ ተጉዘው ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር በሶማሊያ ጉዳይ ውይይት ባደረጉበት ወቅት ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚገኙና “አሸባሪ” ያለቻቸው ግለሰቦች ላይ ክስ ለመመስረት እንዲሁም በኢሳትና በኦ ኤም ኤን የሚዲያ ተቋማት ላይ ክስ መስርቶ እንዲዘጉ ማድረግ የሚቻልበትን መንገድ ለማግባባት እንደተሞከረ ተሰምቷል።
“ይህን ጉዳይ በይፋ ስብሰባ ላይ አልተነሳም ይሁንና ይፋዊ ባልሆነ መንገድ ለልዑካን አባላቱ እንደተነገራቸው አውቃለሁ” በስብሰባው ላይ የተሳተፉ አንድ የአሜሪካ መንግስት ምንጭ እንደተናገሩት።
“ኢትዮጵያ በሶማሊያ የሚኖራትን ትብብር ተቃዋሚዎችን ከመቅጣት ጋር ለማያያዝ ሞክረዋል፣ ይህ በጣም አስቸጋሪ ጉዳይ ነው። ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ጥያቄ ቀርቦ ነበር፣ አልተቀበልነውም። የፕሬዝዳንት ትራምፕ አዲሱ አስተዳደር በጉዳዩ ላይ ያለውን አቋም እስካሁን አልተናገረም፣ አዲስ ነገር ይኖራል ብዬ አልጠብቅም” ይላሉ ምንጩ።
ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ወታደሮቿን ወደ ድንበር በመሳብ በሶማሊያ ያላትን ተሳትፎ የቀነሰች ሲሆን አዲሱ የትራምፕ አስተዳደር ደግሞ በሶማሊያ በአልሸባብ ላይ የተጠናከረ ወታደራዊ ዘመቻ ለመክፈት የኢትዮጵያን ተሳትፎ ይፈልጋል። ለኢትዮጵያና ለሌሎቹ በዘመቻው ለሚሳተፉ ሀገሮች ዳጎስ ያለ በጀት ከአሜሪካ በኩል መያዙም ተሰምቷል።

ሰበር ዜና….. የመምህራን አድማ በጎጃም፣ በወሎና በጎንደር ብዙ ቦታወች ተጠናክሮ ቀጥሏል! – አስናቀው አበበ

$
0
0

በአሁኑ ሰአት የምስራቅ እስቴ ወረዳ መካነየሱስ ሁለተኛ እና መሰናዶ ትምህርት ቤት መምህራንና ተማሪወች አመፅ ላይ ናቸው። መምህራኖች ከዚያው ተከበው ይገኛሉ የሚያናግራቸው አካል መጥቶ ካላናገራቸው አድመውን እንደሚቀጥሉ በቁጣ ተናግረዋል። የወያኔ አፋኝ ወታደሮችን በማሰማራት ከበዋቸውም ይገኛል። መምህራኑ ጥያቄያቸውን ህዝብ እንደደገፈው በመግለፅ ሁሉም አድማውን እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ አብዮት የመምህራንና የተማሪው ድርሻ አብይ እንደሆነ አይዘንጋም።
ህዝብ ያሸንፋል©!
Asnakew Abebe
******
የሚከተለውን ዘገባ ደግሞ ከ Tiss AbayGenji የገኘነው ነው…
ሰበር ዜና #የመምህራን አመጽ
በጎጃም ስናን ወረዳ የት/ቤቱ ር/መምህር መምህራንን ለወታደሮች እየጠቆመ በማስጠቃቱ በመምህራን ተደብድቦ ሲገደል ሌላ መምህር ደግሞ ከወታደሮች በተተኮሰ ጥይት ተገሏል። የመምህራን የስራ ማቆም አመፅ በመላው #አማራ ተቀጣጥሎ ቀጥሏል።በምስራቅ ጎጃም፣ ምዕ/ጎጃም፣ አዊ፣ ደ/ጎንደር፣ ደ/ወሎ የሚገኙ ትም/ቤቶች ተዘግተዋል። ኮማንድ ፖስቱ መምህራንን ማዋከብና ማሰር ስራ ላይ ተጠምዷል።
የጮቄው ነኝ

ደባርቅ በወያኔ ልዩ ሃይል ተወራለች!
ትናንት ያወጣነው መረጃ ትክክል ነው!

ደባርቅ፣ ዳባትና አምባ ጊዮርጊስን ለቆ በወጣው የወያኔ ሃይል ምትክ አዲስ ሃይል እንደሚመጣ በትናንትናው ዘገባ ማስጠንቀቃችን ይታወሳል። በዛሬው እለት ደባርቅ በወያኔ ልዩ ሃይል ግርግር ውስጥ ናት። የወታደር ካምፑንም ተረክበውታል።
ወደ ዳባት አካባቢ ለመስፈር የሚመጣ ሃይልም እንደተንቀሳቀሰ መረጃ ደርሶናልና ሁለገብ ጥንቃቄ ይደረግ።
ህዝብ ያሸንፋል©!
Asnakew Abebe

Image may contain: one or more people and outdoor

121ኛው የአድዋ ድል በዓል በዳላስ በደብልትሪ ሆቴል ይከበራል

$
0
0

121ኛው የአድዋ ድል በዓል March 18, 2017 በዳላስ ሰዓት አቆጣጠር 3 PM ጀምሮ 1981 N Central Expy, Richardson Tx, 75080 በሚገኘው በደብልትሪ ሆቴል ይከበራል። በእለቱ በዳላስ ቴክሳስና አካባቢዋ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንድትገኙ ተጋብዛችኋል።

የእለቱ የክብር እንግዶች፦
1. ፕ/ር ኃይሌ ላሬቦ
2. ዶ/ር መስፋን ገናናው

ቀን፦ March 18, 2017
ሰዓት፦ 3 PM
ቦታ፦ ደብልትሪ ሆቴል (1981 N Central Expy, Richardson Tx, 75080)

አዘጋጅ፦ በዳላስና ፎርትወርዝ የኢትዮጵያውያን ጉዳዮች የውይይት መድረክ ፎረም

በቅዱስ ፍሬምናጦስ እና በቅድስት ሥላሴ ኮሌጆች: በኑፋቄና የምግባር ብልሽት አምስት ደቀ መዛሙርት ተባረሩ

$
0
0
  • በክህነት ባወቁትና ሊጠብቁት በሚገባው ምስጢረ ቤተ ክርስቲያን ተሣልቀዋል፤
  • ለዲቁና የማይገባ ማታለልና ኃይል አሳይተዋል፤ ከመናፍቃንም ጋራ ጸልየዋል፤
  • የኑፋቄን ስውር ተልእኮ፣ ከቴዎሎጂ ኮሌጆቻችን የማጥራት ቀጣይ አካል ነው፤

ሐራ ዘተዋሕዶ

በሚያፈሩት የተማረ የሰው ኃይል፣ በቤተ ክርስቲያናችን የዛሬና የወደፊት የአገልግሎት አቅጣጫ ላይ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው የሚታመንባቸውን መንፈሳውያን ኮሌጆቻችንን፣ ከመናፍቃን ተጽዕኖ የመከላከልና ከኅቡእ ምንደኞቻቸው የማጽዳቱ እንቅስቃሴ በተጠናከረ ኹኔታ ቀጥሏል፡፡

በመቐለ፥ የቅዱስ ፍሬምናጦስ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጅ እና በዐዲስ አበባ፥ አንጋፋው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ ሰሞኑን በወሰዱት አስተዳደራዊ ርምጃ፣ በእምነት አቋማቸውና በሥነ ምግባራቸው ከባድ ኑፋቄና መተላለፍ የተገኘባቸውን አምስት ተማሪዎች፣ ሙሉ በሙሉ ከደቀ መዝሙርነት አሰናብተዋል፡፡

አምነው በተቀበሉት ኑፋቄ የተነሣ፣ በማዕርገ ክህነታቸው ያወቁትንና ሊጠብቁት የሚገባውን ምስጢረ ቤተ ክርስቲያን ማቃለላቸው በማስረጃ የተረጋገጠባቸው ሦስት ተማሪዎች፣ ባለፈው ሳምንት ዓርብ፣ የካቲት 24 ቀን 2009 ዓ.ም.፣ ከቅዱስ ፍሬምናጦስ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጅ ተባረዋል፡፡

በመንፈሳዊ ኮሌጁ፣ የተማሪዎች መማክርት እና የዲስፕሊን ኮሚቴ በየደረጃው ተረጋግጦ፣ ለአስተዳደር ጉባኤው ውሳኔ የቀረበው ማስረጃ እንደሚገልጸው፦ ሦስቱ ተማሪዎች፣ ኾነ ብለውና መክረው በደቀ መዛሙርት ፊት በድራማ መልክ ባሳዩት ትዕይንት፣ በሥጋ ወደሙ ታላቅነት ላይ ተሣልቀዋል፤ የክርስቶስን አማናዊ ቅዱስ ሥጋ አማናዊ ክቡር ደም የምንቀበልበት ምስጢረ ቊርባን፥ “የማይመረመር ምስጢር” የመኾኑን ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ እየነቀፉና እያቃለሉ፣ የፕሮቴስታንታዊውን “ተራ ኅብስት” አስተሳሰብ የመዝራት ተልእኳቸውን ለመፈጸም ተንቀሳቅሰዋል፡፡

ስመ ደቀ መዛሙርቱ፣ በተማሪዎች መማክርቱ ሲጠየቁ፣ ጥፋታቸውን በግልጽ ያመኑ ሲኾን፤ ጉዳዩ በዲስፕሊን ኮሚቴው ዘንድ በታየበት ወቅት ግን ለመካድ ሞክረው እንደነበር ተመልክቷል፡፡ ይኹንና ተደግፎ የቀረበው ማስረጃና የዓይን እማኞች ምስክርነት በአስተዳደር ጉባኤው ተመርምሮ ጥፋተኝነታቸው በማያሻማ ኹኔታ በመረጋገጡ፣ ሙሉ በሙሉ ከኮሌጁ እንዲሰናበቱ መወሰኑ ታውቋል፡፡ የስም ዝርዝራቸውና የተላኩበት አህጉረ ስብከትም፡-

  1. ታደለ ለገሰ፤ ከደቡብ ምዕራብ ሸዋ – ወሊሶ ሀገረ ስብከት የተላከና በመጀመሪያ ዲግሪ የሦስተኛ ዓመት ተማሪ የነበረ፤
  2. ሃይማኖት ገረመው፤ ከቤንች ማጂ ዞን ሀገረ ስብከት የተላከና በመጀመሪያ ዲግሪ የአራተኛ ዓመት ተማሪ የነበረ፤
  3. ሰሎሞን ገብረ ሕይወት፤ ከሲዳሞ ሀገረ ስብከት የተላከና በመጀመሪያ ዲግሪ የአምስተኛ ዓመት ተማሪ የነበረ ናቸው፡፡

በሌላ በኩል፣ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ ትላንት ረቡዕ፣ የካቲት 29 ቀን 2009 ዓ.ም.፣ ከፍተኛ የሥነ ምግባር ግድፈት የታየባቸውን ኹለት የቀን መደበኛ ደቀ መዛሙርት ከኮሌጁ አሰናብቷል፡፡ ለክህነታቸው በማይገባና የደቀ መዝሙርነት ዲስፕሊንን በሚፃረር መልኩ፥ ኃይልና ጉልበት በማሳየት መምህራንን ሲጣሉና ሲሳደቡ እንደነበር የተገለጸ ሲኾን፣ በፈተና ወቅትም በመኮራረጅ እጅ ከፍንጅ መያዛቸው ተነግሯል፡፡

ኹለቱም በመጀመሪያ ዲግሪ የሦስተኛ ዓመት የቀን ተማሪዎች የነበሩ ሲኾን፦ ብርሃኑ ተስፋዬከወሊሶ ሀገረ ስብከት እና ኃይሉ አየለከጅማ ሀገረ ስብከት የተላኩ መኾናቸው ታውቋል፡፡ መጽሐፍ በጻፈበት ስሙ “ናዝራዊ” ብሎ ራሱን የሚጠራው ኃይሉ አየለ፥ በቅርቡ በኑፋቄ ከተባረሩት ስምንት ተማሪዎች መካከል፣ ስሜነህ መኰንን ከተባለው ጋራ ጥብቅ ግንኙነት እንዳለውና በተለይም በአንደኛ ዓመት ደቀ መዛሙርት ላይ በማተኮር፥ “ኮርስ እናሠለጥናችኋለን” በሚል በኅቡእ እየመለመለ በየመንደሩ የሚወስድ የኑፋቄው አስፈጻሚ እንደነበር በመረጃው ተጠቅሷል፡፡

ከኹለቱም ኮሌጆች የተሰናበቱት የስም ደቀ መዛሙርት፣ ክህነታቸውም እንደ አንድ መስፈርት ታይቶ የገቡ እንደመኾናቸው፣ በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃም መታየት የሚገባቸው ቀኖናዊ ጉዳዮች በመኖራቸው፣ ሥልጣነ ክህነታቸውን በተመለከተ ቀጣይ ውሳኔዎችም ይጠበቃሉ፡፡

ከሦስቱ ከፍተኛ መዓርጋተ ክህነት የመጀመሪያ የኾነው ዲቁና፣ ለጳጳሱና ለቄሱ የመላላክ፣ ምእመናንን የማንቃት ተልእኮ የሚፈጸምበት ነውና በመዓልትም በሌሊትም በሥነ ምግባር ላቅ ብሎ መገኘትን ይጠይቃል፡፡ ከኃጢአት ንጹሕ ኾኖ መልካም አገልግሎት የሚያገለግል ዲያቆን፥ ይረባል፤ ይጠቅማል፤ በጎ ዕድል ፈንታ ያገኛል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ሲያስረዳ፦ “እንዲኹም ዲያቆናት ጭምቶች፣ በኸለት ቃል የማይናገሩ፣ ለብዙ የወይን ጠጅ የማይጎመጁ፣ ነውርና ረብ የማይወዱ፣ በንጹሕ ኅሊና የሃይማኖትን ምሥጢር የሚይዙ ሊኾኑ ይገባቸዋል፤” ብሏል፡፡ (1ጢሞ. 3፥ 8-13)

ዲያቆናት፥ ትሑት ኾኖ የማገልገልን ክርስቶሳዊ አርኣያነት ወደ ጎን በመተው በሰው ላይ መታበይ፣ ኃይልን ማሳየት፣ ሰውን መማታት፣ በሐሰት መመስከር በመሳሰሉት ተመክረው የማይመለሱ ኾነው ሲገኙ ከክህነታቸው ይሻራሉ፡፡

ከምንም በላይ ደግሞ፣ ለሕገ ቤተ ክርስቲያን ተገዥና ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አክብረው የሚያስከብሩ መኾን አለባቸው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለሚገኙ፣ ከንዋያተ ቅድሳቱ ጀምረው እስከ አንድ ቆቆር ዕጣን ድረስ ዋጋ የሚሰጡ መኾን አለባቸው፡፡ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እየነቀፉና እያቃለሉ ጥርጣሬ እየዘሩ በአገልግሎታቸው እንዲቀጥሉ አይፈቀድላቸውም፡፡

በመኾኑም አንድ ዲያቆን፥ ቤተ ክርስቲያንን ትቶ ከሔደ በኋላ የተመለሰ፣ ከመናፍቃን የተጠመቀ፣ ቊርባናቸውን የተቀበለ፣ ከመናፍቃን ጋራ የጸለየ፣ ቤተ ክርስቲያንን ትቶ ወደ ሌላ ቤተ እምነት ከሔደ ከዲቁናው ይሻራል፡፡ በእምነቱ ኑፋቄ ከተገኘበት፣ ንስሐ ቢገባም፣ በምእመንነቱ ይቀጥላል እንጂ፣ በሥልጣነ ክህነቱ ማገልገል አይችልም፡፡ /ፍትሐ መንፈሳዊ አንቀጽ 7 ክፍል 5/

Viewing all 2265 articles
Browse latest View live