Quantcast
Channel: Amharic News – Medrek
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2265

የኢትዮጵያ አገራዊ ንቅናቄ ህዝባዊ ጉባዬና ገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ በስኬት ተጠናቀቀ

$
0
0

በአሰግድ ታመነ

በዛሬው ህዝባዊ ጉባዬ የአገራዊው ንቅናቄ ተቀዳሚ ሊቀመንበር አቶ ሌንጮ ለታና ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በእንግድነት የተገኙ ሲሆን የጉባዬው አዘጋጅ የዴሞክራሲ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሊቀመንበር አቶ ይበልጣል የመግቢያ ንግር አድርገዋል።
በማስከተልም አቶ ሌንጮ ለታ ስለ አገራዊው ንቅናቄ ምስረታ ገለፃ አድርገዋል ።
አቶ ሌንጮ በተለይ ከጠቀሷቸው ውስጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ጨዋ ስለሆነ ነው እንጂ እንዲህ ተርቦ ተቸግሮና በድህነት ተሰቃይቶ ዝም ብሎ አይቀመጥም ነበር ብለዋል ። ሲቀጥሉም ወያኔን ማስወገድ የምንችለው እኛ ተቀራርበን ስንመካከር ነው ። ስለዚህ የተስማማንባቸው ጉዳዮች እንዳሉ ሆነው ልዮነታችንን ለመፍታትና ወደቀጣይ ስራ ለመጋዝ በቀርጠኝነት መነጋገር ይገባናል ብለዋል።
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በበኩላቸው ወደ አገራዊ ንቅናቄውን የመሰረቱበትን ምክንያት ሲያስረዱ ሁለት በሆኑ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ መጀመርያ ተስማማን እነሱም
፩ኛ አንድነታ የተጠበቀ ነፃነትና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን በመቀበል።
፪ኛ ልዮነታችንን በግልፅነት በመነጋገር ለመፍታት የሚሉት ናቸው ብለዋል።
ህነዚህ ለህብረታችን መሰረት ናቸው ያል ሲሆን ሌሎች ልዩነታችንን ሁሉ በመነጋገር እንፈታዋለን ብለዋል በተጨማሪም ወደፊት ከኦብነግ፣ከትፕዴም፣ከየአማራ አይል ንቅናቄ ጋር ተነጋግረር ወደ አንድነት እንመጣለን ብለዋል በዚህም ወያኔ ህወሀት ሊያፈርሳት ያሰባትን ሀገራችንን እንደማትፈርስ እናረጋግጥለታለን ብለዋል።
በመጨረሻም የገቢ ማሰባሰብ ስነስርሀት ተካይዶ አንድ መቶ አምሳ ሺ የኖርዌይ ገንዘብ ከተሰበሰበ በኃላ ከህዝብ ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስ በመስጠት የለቱ ጉባዬ ተጠናቋል።

The post የኢትዮጵያ አገራዊ ንቅናቄ ህዝባዊ ጉባዬና ገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ በስኬት ተጠናቀቀ appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2265

Trending Articles