Quantcast
Channel: Amharic News – Medrek
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2265

ሁለቱ ጋዜጠኞች ክስ ሳይመሰረትባቸው ከሦስት ወር በላይ መታሰራቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለጹ

$
0
0

የአናኒያ ሶሪ ባለቤትና የኤልያስ ገብሩ እህት ጋዜጠኞቹ በጹሑፍ ሐሳባቸውን ከመግለጽ ውጭ የሠሩት ወንጀል የለም ብለዋል። መንግሥት በበኩሉ የታሰሩ ካሉ ወይ ሞያው የሚጠይቀውን የጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ባለማክበራቸው ነው ወይም ጋዜጠኞች ባለመሆናቸው ነው ብሏል።

አናንያ ሶሪና ኤልያስ ገብሩ የተባሉ ሁለት ጋዜጠኞችና የኢንተርኔት አምደኞች ክስ ሳይመሰረትባቸውና የታሰሩበትን ምክንያት በይፋ ሳይነገራቸው ከሦስት ወር በላይ በእስር ቤት እንደሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ለአሜሪካ ድምጽ ገለጹ። ወጣቶቹ በጹሑፍ ሐሳባቸውን ከመግለጽ ውጭ የሠሩት ወንጀል የለም ብለዋል – ቤተሰቦቻቸው።መንግሥት በበኩሉ የታሰሩ ካሉ ወይ ሞያው የሚጠይቀውን የጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ባለማክበራቸው ነው ወይም ጋዜጠኞች ባለመሆናቸው ነው ብሏል።

የጋዜጠኞች ደህንነት ተሟጋቹ ሲፒጄ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያ የታሰሩት ስለፃፉ ብቻ ነው በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል ማለቱ ይታወሳል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ።

if(typeof(jQuery)==”function”){(function($){$.fn.fitVids=function(){}})(jQuery)};jwplayer(‘jwplayer-1’).setup({“image”:”http://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2017/02/VOA.jpg”,”file”:”http://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2017/03/2fe47afe-fc9c-47c9-b977-c8f3026fdc5c_hq.mp3″});


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2265

Trending Articles