Quantcast
Channel: Amharic News – Medrek
Viewing all 2265 articles
Browse latest View live

የድርድር ቅድመ ጸብ በ”ተቃዋሚዎች” መካከል እና የጠብ-መንጃ “ሰላም” እስከመቼ?

$
0
0

ቅድሚያ “የታሰሩ ይፈቱና አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ይነሳ” የሚለው ኢህአዴግን ሳይሆን “ተቃዋሚዎችን” አላስማምም፤ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች “ቅድሚያ ይፈቱ” የማያስማማቸው ተቃዋሚዎችን አንድ የማድረግ ሃሳብም አለ። ይህንን ሃሳብ የሚያራምደው ደግሞ ኢዴፓ ነው። የህብረቱን ጥያቄ በፕሮግራም ደረጃ አርቅቆ በይፋ ጥሪ ያቀረበውን ኢዴፓ ተቃዋሚዎች የሚያቀርቡትን ቅድመ ሁኔታ አይደግፍም። ይህንኑ ተከትሎ ኢዴፓ በኢህአዴግ ይደገፋሉ ተብለው ከሚታሙትና የቤተሰብ ጥርቅም የሆኑትን ካልሆነ በዚህ አቋሙ ያሰበውን ሊያሳካ እንደማይችል አስተያየት እየተሰጠ ነው።

ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የፖለቲካ አካሄድ እንደተቀየረና ከቀድሞው ይልቅ እየከረረ መሄዱን ሁሉም ወገኖች ይስማሙበታል። በደጋፊና ተከታይ ብዛት ተጽዕኖ ፈጣሪ ወይም ተሰሚነት አላቸው የሚባሉት የብሄር ፓርቲዎች ይህንን የከረረውን ፖለቲካ የማርገብ ከፍተኛ ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉ ራሱ ኢህአዴግ ያመነበት፣ የውጭ ድጋፍ ሰጪ አጋር አገሮችም ሃሳብና ማሳሰቢያ የሰጡበት፣ ፓርቲዎቹም “እውነት ኢህአዴግ ከልቡ ከሆነ” እያሉ ማረጋገጫ የሚጠይቁበት ጉዳይ ነው።

ድርድር የሚባለው ጉዳይ የመጣውም ከዚሁ መንፈስ እንደሆነ እሙን ነው። ጉዳዩን ተአማኒ የሚያደርገው ደግሞ “ሕገመንግስት እስከመቀየር ወይም እስከማሻሻል የሚደርስ ስምምነት ለማድረግ ዝግጁ ነኝ” ሲል ኢህአዴግ የድርድር ቡፌ ማዘጋጀቱ ይሆናል። በተጓዳኝ የእርቅ ጉዳይ መነሳቱም ጉዳዩ የታሰበበትና የታቀደበት ስለመሆኑ አመላካች ነው። ጥርጣሬ ቢኖርም ድርድርም ሆነ እርቅ የሚለው ሃሳብ ብዙዎችን አስማምቷል። ተስማምተዋል የሚባሉት ወገኖችና ፓርቲዎች “እስኪ እናየዋለን” ሲሉ ኢህአዴግ የመጨረሻ ፈተና ለራሱ እንደሰጠ እየተናገሩ ነው።

ከውጭ ብቻ ሳይሆን ኢህአዴግ አስቸኳይ ጊዜ ያወጀበት የውስጥ ችግሩ ውስጥ ውስጡን ሲብላላና እየተቀጣጠለ ሄዶ የቀበሌ መዋቅሩን ሳይቀር አስልሎ ስለበላው እንደሆነ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ እየመሰከሩ ነው። የቀበሌና የወረዳ መዋቅሮች ስለመንኮታኮታቸው ዋናው ማስረጃ ደግሞ በመላው አገሪቱ እስኪባል ድረስ የተዛመተው ተቃውሞ ዋና ማስረጃ ሲሆን፣ ተቃውሞውን ተከትሎ በሺህ የሚቆጠሩ ከፍተኛና ዝቅተኛ አመራሮች እንዲወገዱ፣ ከሃላፊነት እንዲነሱ ወይም ዝቅ እንዲሉ፣ አለያም ተራ ዜጋ ሆነው ሲፈለጉ “አለሁ” እንዲሉ ፋይል ተክፍቶባቸው እንዲቀመጡ መደረጋቸው ነው።

ራሱ ኢህአዴግ ከመነሻው “ትክክል ነው” ያለው ሕዝባዊ ቁጣና አመጽ፣ ለጊዜው በአስቸኳይ አዋጅ ጋብ እንዲል ሲደረግ፣ ከዛው ጎን ለጎን የጠፋው የሰው ህይውት፣ በስር ላይ የደረሱ በደሎች የብዛታቸውን ያህል ቂም አምርተዋል። ይህ የተጠራቀመ ቂም በየትኛው ጊዜና ሰዓት የበቀል ክንዱን ከፍ እንደሚያደርግ ባይታበለም፣ ሁሉንም ጉዳይ “በይቅርታ እናትመው” መባሉ አሁንም የጉዳዩን አሳሳቢነትና ነገሮች በዚህ ሊቀጥሉ እንደማይችሉ አመላካች ነው። ለዚህም ይመስላል አሜሪካ “ነግረናል ወሳኔውና ምክሩን ስራ ላይ ማዋል የኢህአዴግ ፈንታ ነው” በማለት ማስጠንቀቋን ያስታወቀችው።

ከዚህ አንጻር ቀደም ባሉ ጊዜያት እንደሚካሄደው አይነት ተራና ለውጪው ፖለቲካ ግብአት እንዲመች የሚደረጉ ውይይቶችና ድርድሮች ጊዜ ያለፈባቸው ይመስላሉ። ከዚህ ቀደም ኢህአዴግ ስለ ድርድርና ሽምግልና ሲጠየቅ “ለድርድር የሚያበቃ ምንም ጉዳይ የለም” ሲል እንዳልነበር የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጫና / እዚህ ላይ ተቃዋሚ ሲባል በቤተሰብ የተሰባሰቡትንና እንድ ቅንጅት፣ ኦብኮና ሌሎች ከምዝገባ ፈቃድ የዘለለ ልዕልና የሌላቸውን አያካትትም/ ምን ያህል እንደሆነ ባይታወቅም ህዝብ አስገዳጅ ሁኔታን ፈጥሯል። ስለዚህም ድርድሩ በሙሉ መስጠትና መቀበል መርህ እንዳይሆን የሚያግደው ጉዳይ እንደማይኖር ከግምት በላይ ይታመናል። እንደራደር ያለው ኢህአዴግም አሁን አፈ ቀላጤ ድርጅቶች ምንም ሊረዱት እንደማይችሉ ያመነ ይመስላል።

የድርድሩ ጉዳይ እንዲህ በስሎና ነፍሮ የመታ ሆኖ ሳለ አንቱ የተባሉ የፖለቲካ መሪዎችን አስሮ፣ ደጋፊውችን አጉሮና አባላትን እያሳደዱ የሚደረግ የሰላም ድርድር ለተቃዋሚዎች ክህደት፣ ለራሱ ለኢህአዴግ ደግሞ ድንቁርና ከመሆን አይዘልምና ጥያቄው “ቅድመ ሁኔታም” ድረስ ሊያደርስ ባልቻለ ነበር። ሲሆን ሲሆን “ብረት አንስተናል” የሚሉትን ቢያካትት ፋይዳው የጎላ፣ ውጤቱም ተስፋው የበዛ በሆነ ነበር። ይህ ለጊዜውም እንኳን ባይቻልም በአገር ቤት ጽንፈኞችን ሲታገሉና ሲያሽመደምዱ የነበሩትን ጨምሮ የታሰሩ የፖለቲካ መሪዎችን እየወነጀሉ “እንታረቅ” ማለት ሲጀመር ድርድሩን የከሸፈ እንዳያደርገው ስጋት አለን የሚሉትን ወገኖች በቀናነት መቀበልና ማድመጥ ይጠበቃል፤ ግድም ነው።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ነው ባለፈው ቀዳሜ አቶ ልደቱ አያሌውንና የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹን የቪኦኤዋ አዳነች ፍስሃዬ ባነጋገረችበት ወቅት አስገራሚ የተባለው አለመግባባት የተደመጠው።

በጥያቄና መልሱ ከተነሱት ነጥቦች መካከል “ቅድም ድርድር” የሚለው ዋናና ቁልፍ ጉዳይ አንዱ ነበር። አቶ ልደቱ “በቅድመ ሁኔታ አናምንም” ሲሉ አቶ ሙላቱ “ያልተነካ ግልግል አያውቅም” ሲሉ በንፅፅር መልስ ሰጡ። እሳቸው ይህን ሲሉ የታሰሩባቸውን የድርጅታቸው አመራሮች፣ ደጋፊዎችና አባላት ከግምት ውስጥ አስገብተው ነበር።

አንድ በስውዲን የግጭት አፈታትና አወጋገድ ሳይንስ ትምህርት እየተከታተለ ያለ ተማሪ ተማሪ እንዳለው “ኦፌኮ በቀለ ገርባን፣ መረራ ጉዲናን፣ የማይዘመርለትን ኦልባና ለሊሳን.. ሌሎች አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች አሳስሮ ከኢህአዴግ ጋር ምን ብሎ ይደራደራል? ተደራድሮስ ለሕዝቡ ምን ይዞ ይመጣል? ከዛስ የድርጅቱ ህልውና ምን ይሆናል?” ሲል ይጠይቃል።

አያድርገውና ኢዴፓ ልክ እንደ ኦፌኮ መሪዎቹ፣ አባላቱና፣ ደጋፊዎቹ ቢታሰሩ “በቅድመ ድርድር አላምንም፤ አባሎቼን፣ አመራሮቼን፣ ደጋፊዎቼን ለምን ታሰሩ ብዬ አልጠየቅም ይል ነበር?” ሲል አስተያየት ሰጪው ይጠይቃል። አያይዞም አቶ ልደቱ በግልጽ ኢህአዴግ ሆነው ቢገላገሉ እንደሚሻል ይጠቁማል።

አቶ ልደቱን የሚደገፍ ሌላ አስተያየት ሰጪ “አቶ ልደቱ እንዳሉት ቅድመ ሁኔታ በማስቀመጥ ድርድር ከሚጨናገፍ ጉዳዩን ቀዳሚ አጀንዳ ማድረግና መመልከቱ የተሻለ ነው” ይላል። አያይዞም አቶ ልደቱ እንዲህ ያለውን ጉዳይ በዝምታ ቢያልፉና ለወደፊት ፓርቲያቸው አቋም እንደሚይዝበት ቢያስታውቁ የተሻለ እንደሚሆን ጠቁሟል።

አዳነች “የታሰሩት አመራሮች ካልተፈቱና፣ አስቸኳይ አዋጁ ካልተነሳ ድርድሩን አትቀበሉም ማለት ነው?” ስትል ደግማና ደጋግማ እየጠየቀች፣ በአቶ ልደቱ በኩል ማስተባበያ እያሰጠች ባስኬደችው ቃለ ምልልስ አቶ ሙላቱ “የሚደራደሩለትን አስሮ ማን ይደራደራል” ሲሉ መልሰውላታል። አቶ ልደቱንም “ያልተነካ ግልግል አያውቅም” ሲሉ ኢዴፓ እሳቸው እንደሚመሩት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ፓርቲ መከራና ስቃይ እንዳልደረሰበት ለማሳየት ሞክረዋል።

ቀደም ሲል “የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ አንፈልግም” ብለው የነበሩት አቶ ልደቱ ፣ በዚህኛው ቃለ ምልልስ አዋጁ እንዲነሳ ፣ የታሰሩ የፖለቲካ መሪዎች እንዲፈቱ ምኞቱ እንዳላቸው ተናግረዋል። ኢዴፓ አመራሮቹ ባይሆኑም የታሰሩ አባላት እንዳሉትም አመልክተዋል። ሁሉም ሆኖ ግን ኢዴፓ በመርህ ደረጃ ለድርድር ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጥ የድርድር አካሄድን ያደናቅፋል የሚል የቆየ እምነት እንዳለው ነው አቶ ልደቱ ያመለከቱት።

“በሰው አገር የከበረና በጨለማ የጨፈረ አንድ ነው’ የሚለውን የትግራይ ተረት ያስታወሰው የግጭት አወጋገድ ትምህርት ተማሪ” አቶ ልደቱ አሁን እየተከተሉ ያሉት አካሄድ ስልታዊ ነው። ተቃዋሚዎችን ሳይሆን ገዢውን መንግስት በስልት ማስደሰትና እሱን ሆኖ መናገር፤ ይህ ማለት በሌሎች ቁስል እንጨት ስደድበት እንደማለት ይቆጠራል። እርገጠኛ ነኝ ስለዚህ ጉዳይ ዋናው የኢህአዴግ ሰው ቢጠየቁ ከአቶ ልደቱ የተለየ መልስ የላቸውም” ሲል አቶ ልደቱ ቢያንስ ተቆርቋሪነታቸውን ሊያሳዩ በተገባ ነበር ሲል ትዘብቱን ያስቀምጣል። አያይዞም “ኢዴፓ በዚህ አቋሙ ከማን ጋር ተዋህዶ ለመስራት ነው የውህደት ጥሪ ያቀረበው? ኢህአዴግ የፈጠራቸውን አሰባስቦ የተሻሻለው ሌላ ኦህዴደ ወይም ብአዴን ወይም ደህዴን ከመሆን አይዘልም። እንዲህ ያለው አካሄድ ላለፉት 25 ዓመታት ተሰርቶባቸው ውጤታቸው በገሃድ ታይቷል” ሲል አስተያየቱን ያጠቃልላል።

አቶ ልደቱና የእሳቸው ፓርቲ አካሄድ የተመረጠ እንደሆነ የሚናገረው አስተያየት ሰጪ በበኩሉ “ኢህአዴግ ለለውጥ በሩን የሚዘጋው ጽንፈኛ አካሄድ ስለሚያስፈራው ነው። ስለዚህም እንደ አቶ ልደቱ አይነት አካሄድ ካልሆነ በስተቀር እስኪሞት ይንገዳገዳል እንጂ ውንበሩን ለማንም አይሰጥም። አንድ እውነት አለ። ብአዴንና ኦህዴድ እንደ ድርጅት አሉ አይባልም። ለዚህም ነው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያስፈለገው። ስለዚህ አሁን ስጋት ውስጥ ያለን መንግስት ምቾት የሚነሳ የትግል ስልት የትም አያደርስምና በፖለቲካዊ መለሳልስ ነገሮችን በዝግ በር መያዙ ያዋጣል” ባይ ነው።ይህ አስተያየት ሰጪ ሚዲያዎችና አስተያየት ሰጪዎች ድርድሩን አስመልከቶ ጥንቃቄ ቢወስዱ፣ የማበረታት ስራ ላይ ቢያተኩሩና፣ አገሪቱ የገባችበት አደገኛ ሁኔታ እንዲገፈፍ ቢሰሩ የተሻለ እንደሆነ ይመክራል። ገና በጅምር ላይ ባለ ጉዳይ ብዙ ማለቱ ማንኛውንም ወገን እንደማይጠቅምም ያሰምርበታል።

ድርድሩ አጀንዳ መቅረጽን ጨምሮ በአራት ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ የተደረሰበት መሆኑ አይዘነጋም። በድርድሩ ድምጽ ብልጫ አንዱ የመወሰኛ አማራጭ መሆኑና ኢህአዴግ ፈለፈላቸው የሚባሉት ሁሉ የሚካተቱበት መሆኑ ብዥታን የፈጠረ መሆኑም አይዘነጋም። ከድርድሩ በፊት ተደራዳሪዎች እርስ በእርሳቸው አለመግባባታቸው ገኖ መውጣቱ አሳዛኝ እየተባለ ነው። አይኑን በጨው ያጠበው የኢትዮጵያ ፖለቲካ የተቅውሞ ኮሪድር ይህን ይመስላል። ቀኑ ሲደርስ ኢህአዴግ ምን ይል ይሆን? (ምንጭ: ዛጎል ዜና)


“አንተስ…?”

$
0
0

ዓይኔን በዓይኔ ያየሁበት፣
በስተእርጅና ያገኘሁት፣
የትናንቱ ማሙዬ፣

ያሳደኩት አዝዬ
የንግሊዞችንወረራ

ሰምቶ፣

በቴዎድሮስ ሞት

ተቆጥቶ፣
ለምን? ለምን ሞተ?
ብሎ ሲያለቅስ፣

የዓይኑን ዕንባ ላደርቅ-

የልቡን መሰበር ላድስ፣

ጀግኖቻችንን ቆጥሬ-
ታሪካችንን ባወድስ፣
ዕንባውን ዋጥ አድርጎ-
በአትኩሮት ዓይኔን እያየኝ፣
«አንተስ…?» አንተስ!-
ምን ሰርተሀል? በማለት ጠየቀኝ።
እድሜ ቢደራረብ ተግባር ሳይላበስ፣
እንደዚህ እንደኔ ያስጠይቃል ለካስ!
(ወለላዬ)

የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች የህግ ሂደት ከተጀመረ 1020 ቀናት በኋላም ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

$
0
0

ሚያዚያ 17፣ 2006 የታሰሩት አራት የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች አቤል ዋበላ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ በፍቃዱ ኃይሉና አጥናፉ ብርሃኔ እንዲሁም በሌለችበት ክስ የቀረበባት ሶልያና ሽመልስ ለመጨረሻ ውሳኔ ዛሬ ጥር 30፣ 2009 ለሃምሳ አንደኛ ጊዜ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የወንጀል ችሎት ይቀርባሉ::

ጥቅምት 05፣ 2008 የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ችሎት አራቱን ጦማርያን ከቀረበባቸው ክስ በነፃ ያሰናበተ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን፤ ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ ላይ የቀረበበት ክስም ወደ መደበኛው የወንጀል ሕግ ተቀይሮ በዋስትና ከእስር ተፈትቷል:: ነገር ግን ከሳሽ የፌደራል ዓቃቤ ሕግ “በከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሳኔ ቅር ተሰኝቻለሁ” በማለት በታሕሳስ 04፣ 2008 ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ አቅርቧል::

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱም የቀረበውን ይግባኝ ተቀብሎ የሁለቱንም ወገን ክርክር ከሰማ በኋላ “የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት” በሚል የተለያዩ ምክንያቶችን በመስጠት ከዓመት በላይ የወሰደ ሲሆን ፤ ጥር 19፣ 2009 በዋለው ችሎትም አስፈላጊው ሰነዶች ሁሉ ተሟልተው መቅረባቸውን አረጋግጦ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ለዛሬ ጥር 30፣ 2009 ቀጠሮ ይዟል::

በሌላ በኩል ጦማሪ አቤል ዋበላ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የነበረበትን ክስ የቦሌ ክፍለ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ችሎት “ከስራው የታገደበት አግባብ ተገቢ ነው” በሚል ምክንያት ወደ መደበኛ ስራው እንዳይመለስ ውሳኔ የሰጠ ሲሆን ፤ ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ እና ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉም በድጋሚ በተለያዩ ምክንያቶች በቅርቡ ታስረው የተፈቱ መሆናቸው የሚታወስ ነው::

Zone9

አረና ትግራይና ድብቅ ማንነቱ! – ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

$
0
0

አረና ትግራይ ትላንትና 28,5,2009ዓ.ም. መቀሌ በሚገኘው ቢሮው (መሥሪያ ቤቱ) ባደረገው የፓርቲው (የቡድኑ) 4ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ካሳለፋቸው ውሳኔዎች ሁለት ዋና ዋና ነጥቦች ትኩረቴን ሳቡትና ነው ይህችን ጽሑፍ ለመጻፍ የተነሣሁት፡፡

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

እነኝህ ነጥቦች 1ኛው አረና ትግራይ ከጎሳ ተኮርነት ወጥቶ ወይም ጎሳተኮርነቱን (ዘውገኝነቱን) ትቶ ተመሳሳይ የአንድነት አቋም ካላቸው ጋር በመሆን ሀገር አቀፍ የአንድነት ፓርቲ ለመመሥረት እንደሚንቀሳቀስ የተነገረው ሲሆን 2ኛውና ከላይ ከተናገሩት ነጥብ ጋር በቀጥታ የሚጣረሰው ነጥብ ደግሞ “ፓርቲው ወደፊት ተመርጦ ሥልጣን ቢይዝ የሕወሓት ባለሥልጣናት መጠቀሚያ የሆነውን የትእምትን (EFFORT) ሀብት በትክክል የትግራይ ሕዝብ ሀብት አደርጋለሁ!” ማለቱ ነው፡፡

ከዚህ ቀደም በተለያየ ጊዜ አረና ትግራይንና በትጥቅ ትግል ላይ ያለው ዴምሒትን ወይም ትሕዴንን በምሳሌነት በማንሣት “ተደራጀን!” የሚሉለትን ምክንያትና ዓላማ በመጥቀስ ከትግራይ ማሕፀን ኢትዮጵያን ማሰብ የሚችል ወይም ኢትዮጵያን የሚያስቀድም ፍትሐዊና ዲሞክራሲያዊ (መስፍነ ሕዝባዊ) መሠረት ያለው ፓርቲ (ቡድን) ፈጽሞ ሊወጣ ሊፈጠር እንደማይችል መናገሬ ይታወሳል፡፡ ለዚህ ድምዳሜየ ማስረጃየ እነኝሁ ፓርቲዎች ወያኔን አኩርፈው ከወያኔ እየተለዩ አረናንና ትሕዴንን የመሠረቱበት ምክንያት ነው፡፡ እነሱ በተደጋጋሚ እንደተናገሩት ከወያኔ ተለይተው የተጀራጁበት ምክንያት “ሕወሓት በረሃ እያለ ለትግራይ ሕዝብ የገባውን ቃል ሊፈጽም አልቻለም! የትግራይ ሕዝብ በሕወሓት ተክዷል!” በሚል ቅሬታ በመነሣሣትና ያንን ቃል ተፈጻሚ ለማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የፓርቲዎቻቸውን ሥያሜ ትግራይን ማዕከል እንዲያደርግ ያደረጉበትም ምክንያት ይሄው ነው፡፡

እነኝህ ቡድኖች “ሕወሓት ተፈጻሚ አላደረገውም!” ከሚሉት ቃል የተገቡ ጥቅሞች አንዱ “ትግራይን በጎንደር በኩል ሌላው ቢቀር እስከ ደባርቅ ድረስ፣ በወሎ በኩል እስከ አለውኃና ከነባ ድረስ ማስፋት የሚለው አንዱ ሲሆን ሌላው ደግሞ የተለየ የኢኮኖሚ (የጥሪት) ተጠቃሚነት ነው፡፡

ለእነኝህ ፓርቲዎች (ቡድኖች) ወያኔ ከጎንደርና ወሎ ቆርሶ የወሰዳቸው ለምና ሰፋፊ መሬቶችና ከመጀመሪያው ጀምሮ ከኢትዮጵያ ሕዝብ እየተዘረፈ በሕገወጡ ኤፈርትና በሌላም አማካኝነት ትግራይ ላይ የሚፈሰው የግፍ የሀገሪቱ ሀብት እንዲሁም በመላ ሀገሪቱ ትግሬን ብቻ ተጠቃሚ ያደረገው የንግድ እንቅስቃሴና የሥራ ዕድል በጭራሽ በቂ አይደለም፡፡ በቂ ባለመሆኑም ከዚህ በላይ በሚፈልጉት መጠን ተጠቃሚ ለማድረግ በማሰብ እየታገሉ ይገኛሉ፡፡ በሌላ አገላለጽ ሰዎቹ የሚፈልጉት እያንዳንዳችንን በቁማችን ሥጋችንን ግጠው መብላት ነው የሚፈልጉት፡፡ የለየላቸው ጭራቆች ናቸው ሰዎች አይደሉም፡፡ እየታገሉ ያሉት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ከወያኔ እጅግ የከፋ ወያኔ ሆኖ ለመምጣት ነው፡፡ የወያኔን ኢሰብአዊ መራር ግፍ ምን ያህል መሸከም እንዳቃተንና በፍጹም እንዳልቻልን፣ በአፍጢማችን እንደደፋን አስቡና ከወያኔ የከፋን ሌላ ወያኔን አስቡ! መቋቋም እንችላለን? ታዲያ እነኝህ ሰዎች ናቸው?

እንግዲህ እንዲህ ዓይነት የነቀዘ የገማ ኢፍትሐዊ አስተሳሰብ ያለው አረና ነው እንግዲህ በትናንትናው ጉባኤው ላይ ከጎሳ ተኮር ወይም ዘውገኛ አስተሳሰብ ወጥቶ ሀገር አቀፍ አስተሳሰብ ካላቸው ወገኖች ጋር በመሆን ሀገር አቀፍ የአንድነት ፓርቲ የመመሥረት ዓላማ እንዳለው ያስታወቀው፡፡

ይህ አባባሉ አዲስ የማወናበጃ መንገድ ለመፍጠር የታሰበ አባባልና አረና መቸም ቢሆን ከጎሰኝነት ደዌው ሊፈወስ የሚችል አለመሆኑን የሚያረጋግጠው “ወደፊት ሥልጣን ብይዝ የኤፈርትን ሀብትና ንብረት በሙሉ የትግራይ ሕዝብ ሀብት እንዲሆን አደርጋለሁ!” ካለበት የምኞት ቃሉ ላይ ታገኙታላቹህ፡፡

አረናዎች ሕገወጡ ኤፈርት ሀብቱን በምን በምን ዓይነት ሕገወጥ መንገድ የኢትዮጵያን ሕዝብና የሀገርን ሀብት ዘርፎ እንዳከማቸና እያከማቸ እንዳለ ከማንኛችንም በላይ ያውቃሉ፡፡ ወያኔ በረሀ በትግል ላይ እያለ ትግራይና ሰሜን ጎንደር የመንግሥት (የሕዝብ) ባንኮችን እየዘረፈ፣ ሥልጣን ከያዘ በኋላም ከብሔራዊ ባንክ በቢሊዮኖች ልብ በሉ በቢሊዮኖች (በብልፎች) ነው ያልኩት የሚቆጠር የሕዝብና የሀገር ገንዘብ በማናለብኝነት ወስዶ ነው የኤፈርትን አቅም የገነባው፡፡ ከዚህም ባሻገር ኤፈርት በሕገወጥ መንገድ ተቋቁሞ ቀረጥና ግብር ሳይከፍል፣ የመንግሥትን ንብረቶች በሕገወጥ መንገድ እየተገለገለና እየተጠቀመ የሚንቀሳቀስ ሕገ ወጥ ድርጅት እንደመሆኑ ከፍተኛ የሀገርና የሕዝብ ዕዳ አለበት፡፡

ዛሬ ላይ ኤፈርት በአቦይ ስብሐት አገላለጽ “በሀገሪቱ ተወዳዳሪ በሌለው ካፒታል (አቅመ ንዋይ)” እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ ኤፈርት እንደ ፋብሪካዎች (መምረቶች) እና ኢንዱስትሪዎች (ምግንባቦች) ያሉ ቋሚ ንብረቶቹን መቀመጫቸውን ትግራይ ላይ ሲያደርግ ሌሎች ገቢ የሚያገኝባቸውን እንደ ባንክ (ቤተ ንዋይ) ፣ ኢንሹራንስ (ዋስትና) ፣ ትራንስፖርት (መጓጓዣ) ፣ የብዙኃን መገናኛ (ማስ ሚዲያ) ፣ ገቢና ወጪ (ኢንፖርት ኤክስፖርት) ንግድ፣ ግብርናና ማዕድን፣ ኮንስትራክሽን (ግንባታ) ወዘተረፈ እንቅስቃሴውን ደግሞ በመላ ሀገሪቱ አንሰራፍቶ ፍርፋሪውን ብቻ በመተው በሕገወጥ መንገድ በብቸኝነት ተቆጣጥሮ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡

አረናዎች የኤፈርት ሀብት በእንዲህ ዓይነት ዝርፊያ፣ ውንብድናና ሕገወጥ መንገድ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ዘርፎ ሀብቱን እንዳካበተ እያወቁ ነው እንግዲህ “የትእምትን ወይም የኤፈርትን ሀብትና ንብረት ሁሉ በትክክልም የትግራይ ሕዝብ ሀብት እንዲሆን እናደርጋለን!” እያሉን ያሉት፡፡ ምክንያቱም መቸም ቢሆን ሊለወጡ፣ ከጎሰኝነት ደዌያቸው ሊፈወሱ አይችሉምና፡፡
አረና “የኤፈርትን ሀብት የኢትዮጵያ ሕዝብ ሀብት እንዲሆን አደርጋለሁ፣ ኤፈርት ፋብሪካዎቹን (መምረቶቹን) እና ኢንዱስትሪዎቹን (ምግንባቦቹን) ኢፍትሐዊ በሆነ መንገድ ትግራይ ላይ አከማችቷቸዋልና ሁሉም የሀገሪቱ ክፍል በእኩልነት ተጠቃሚ ሊሆኑ በሚችሉበት ሁኔታ ተነቅለው በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች መተከል አለባቸው!” ብሎ ቢሆን ኖሮ “ጎሰኝነት እንደማይጠቅምና ሀገርንና ሕዝብንም በእጅጉ እንደሚጎዳ ተገንዝቤያለሁ!” ማለቱን አምነን በመቀበል አረና ትግራይ ከጎሰኝነት ደዌው ተፈውሷል፣ የበሰለ የፖለቲካ (የእምነተ አሥተዳደር) ግንዛቤ ላይ ደርሷል፣ ኢትዮጵያን አስቀድሟል፣ ኢትዮጵያዊነት ተሰምቶታል ባልን ነበር፡፡

ነገር ግን ጠባብ ጎሰኝነት ከትግራይ ማሕፀን ለሚወለዱ ድርጅቶች ካንሰራቸው (ነቀርሳቸው) በመሆኑ ከዚህ ደዌያቸው ሊፈወሱ አይችሉምና “አስተሳሰባችን ወደ ሀገር አቀፍ የአንድነት ደረጃ አድጓል፣ ጎሰኝነትን እንደማይጠቅም አውቀን ትተናል!” እያሉ ባሉበትም ጊዜ “ወደፊት ተመርጨ ሥልጣን ብይዝ የኤፈርትን ሀብት የትግራይ ሕዝብ ሀብት እንዲሆን አደርጋለሁ!” ሊሉ ቻሉ፡፡

ወያኔ ኤፈርትን ሲመሠርት ምክንያት ያደረገው “በ17 ዓመቱ የደርግ ዘመን ትግራይ የጦርነት ቀጠና ሆና በመቆየቷና በመጎዳቷ ትግራይን መልሶ ለማቋቋም ነው!” የሚል ሐሰተኛ ምክንያት በመስጠት ነበር፡፡

የነበረው እውነታ የሚያሳየው ግን ነገሩ ተገላቢጦሽ መሆኑን ነው፡፡ በ17 ዓመቱ የደርግ ዘመን ትግራይም ሆነች ኤርትራ የጦርነት ቀጠና በመሆናቸው ከተቀረው የሀገሪቱ ክፍል በተሻለ ተጠቃሚ የነበሩ መሆናቸውን ነው እንጅ ተጎጂ መሆናቸውን አይደለም፡፡ በሁለት ምክንያቶች፡፡ አንደኛው ደርግ በዘመኑ የሀገርን ከፍተኛ በጀት ለሀገር መከላከያ በጅቶ (መድቦ) ይንቀሳቀስ የነበረ በመሆኑ ያንን ያህል የሀገር ሀብት ይንቀሳቀስ የነበረው ትግራይና ኤርትራ ላይ ነበር፡፡ ደርግ ይሄንን ያህል ግዙፍ ባጀት (የገንዘብ መደብ) በእነኝህ ሁለት ክፍላተ ሀገራት በሠፈረው ሠራዊቱ ላይ ሲያንቀሳቅስ ሁለቱ ክፍላተ ሀገራት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ መሆናቸውን ለመረዳት የሚከብድ አይመስለኝም፡፡ ሌላኛው ምክንያት ደግሞ ደርግ ያባበለ እየመሰለው እህልን እንኳን ሳይቀር ከተቀረው የሀገሪቱ ክፍል እያራቆተ ዕድሜ ልኩን ኤርትራና ትግራይ ላይ ያፈስ የነበረ በመሆኑ ነው፡፡
በተጨማሪም ሀገሪቱ ከነበሯት ፋብሪካዎች (መምረቶች) እና ኢንዱስትሪዎች (ምግንባቦች) የሚበዛው በዚሁ ቀጠና የነበረና ከዚህም አንፃር ከሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ (ጥሪታዊ) እንቅስቃሴ የአንበሳውን ድርሻ የያዘው ይሄው ተጎዳ የተባለው ቀጠና ነበር፡፡

ወያኔ “ትግራይ የጦርነት ቀጠና በመሆኑ ከተቀረው የሀገሪቱ ክፍል በትምህርትና የጤና ሽፋን፣ በመሠረተ ልማት ዝርጋታ ወዘተረፈ. ከሌሎቹ የሀገሪቱ ክፍላተ ሀገራት በዚህን ያህል ደረጃ ወደኋላ ቀርታለች ወይም ተጎድታለች! ብለህ አኃዛዊ መረጃ አቅርብ?” ተብሎ ቢጠየቅ ውጤቱ የሚያሳየው ቅጥፈቱን በመሆኑ ፈጽሞ ሊያደርገው አይችልም፡፡ በመሆኑም ነው እንዲያው በደፈናው ምክንያት በመመክነት ብቻ አሳቦ ዝርፊያ ሲፈጽምብን የኖረውና ያለው፡፡

እርግጥ ነው ጦርነት መገዳደያ መጠፋፊያ እንጅ መሸላለሚያ አይደለምና በዚህ ቀጠና በርካታ ወገናችንን አጥተንበታል፣ ጉዳት ደርሶብናል፡፡ ልብ ሊባል የሚገባው ነገር ግን በዚህ የጦርነት ቀጠና ያለቀው ዜጋ የትግራይና የኤርትራ ተወላጅ ብቻ ሳይሆን ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍል በብሔራዊ ውትድርና በግዳጅ ተመልምሎ ይወሰድ የነበረውና ምንም የማያውቀው ለጋ ወይም ገና ታዳጊ ወጣት ወገን ጭምርም ነው ያለቀውና የአካል ጉዳተኛም ሆኖ የቀረው፡፡

እናውራው ከተባለስ እንዲያውም ከሕወሓት መሥራች ታጋዮች አንደበትና ከሌሎች ምንጮችም እንደሰማነው በደርግ ከተገደሉ የትግራይና የኤርትራ ተወላጆች ይልቅ ራሳቸው ወያኔና ሸአብያ የትግራይና የኤርትራ ተወላጆች በእነሱ አስተሳሰብ ብቻ አምኖ የሚንቀሳቀስ ለማድረግ፣ ከእነሱ የተለየ አስተሳሰብ እንዳይይዝ እንዳያንጸባርቅ ለማድረግ የገደሉት እንደሚበዛ መረጋገጡን እዚህ ላይ ማንሣቱ ተገቢ ነው፡፡ በወያኔና ሸአቢያ በትግራይና ኤርትራ ተወላጆች ላይ ለተፈጸመው ጭፍጨፋና ወያኔና ሸአቢያ በአካባቢው ሆን ብለው ያደርሱት ለነበረው የመሠረተ ልማት፣ የትምህርት ቤት፣ የጤና ጣቢያ የመሳሰሉት ውድመቶች የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕዳ ከፋይ ወይም ባለዕዳ ሊሆን የሚችልበት አንድም ዓይነት አግባብ የለምና ወያኔ ትግራይን ለመጥቀም የፈጠረው ሰበብ አሳማኝ፣ ትክክልና ፍትሐዊ ሊሆን አይችልም፡፡

ደርግ ስላደረሰው ጥፋት ስናወራ ቀይ ሽብር አንዱና ዋናው ነው፡፡ በዚህ የቀይ ሽብር እርምጃ ከሀገሪቱ አካባቢዎች እጅግ በከፋ መልኩ እንደቅጠል የረገፈውና የተጎዳው የጎንደርና የጉራጌ የሀገሪቱ ክፍል ነው፡፡ ታዲያ እንግዲህ እውነታው ይሄ ከሆነ “ትግራይና ኤርትራ የጦርነት ቀጠና ስለነበሩና ከተቀሩት ክፍላተ ሀገራት በተለየ መልኩ የደርግ አገዛዝ ባደረሰው ጥቃት ተጎድተዋልና የመልሶ ማቋቋም ሥራ ሊሠራላቸው ይገባል!” ተብሎ ተጨባጩ ሀቅ ግን የተቀረው የሀገሪቱ ክፍል ከሁለቱ በከፋ መልኩ በደርግ ጥቃትና ከላይ እንዳነሣነው ሁለቱ ክፍላተ ሀገራት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ የሆኑበትን “ለጦሩ!” በሚል ሁለንተናውን ተበዝብዞ በከፋ መልኩ የተጎዳ መሆኑን እያሳየ እያለ የተሰጠው ምክንያት የቱ ላይ ነው እውነትነቱ፣ ትክክለኛነቱና ፍትሐዊነቱ?

በመሆኑም ሐሰተኛ ወይም የማስመሰያ ምክንያት ተፈጥሮ የለየለት ፋሺስታዊ (አረመኔያዊ) ዝርፊያና ውንብድና ነው ሲፈጸምብን የኖረውና እየተፈጸመብንም ያለው፡፡ አረና ትግራይም ይሄንን ግፍ ማስቀጠል ነው የሚፈልገው፡፡ “ሥልጣን ብንይዝ!” ብለው የተናገሩት ነገር ፓርቲው በአንድነት ፓርቲ ጭምብል ተከልሎም ጠባብ ኢፍትሐዊ የጎሳ ጥቅሙን ለማስጠበቅ እንዳሰበ ማረጋገጫ ነው፡፡

አረና በዚሁ ጉባኤው ላይ ወልቃይትን በተመለከተ ያለውን አቋም ሲገልጽ የወልቃይት ጉዳይ በሕዝበ ውሳኔ እንዲፈታ እንደሚፈልግ አቋሙን አስታውቋል፡፡ ኃላፊዎቹ ግን በግል የሚያንፀባርቁት ከዚህ የተለየ ነው፡፡ ለምሳሌ በዚህ ጉባኤ የፓርቲው ሊቀመንበር ሆኖ የተመረጠው አብርሃ ደስታ የወልቃይት ሕዝብ “ጥያቄያችን የማንነት ጥያቄ ነው!” እያለ ባለበት ሁኔታ ይሄንን የሕዝብ ጥያቄና ጩኸት ኢዲሞክራሲያዊና ኢፍትሐዊ በሆነ አተያይ በማየትና ጥያቄያቸውን ለመቀበል ባለመፈለግ “የወልቃይት ሕዝብ ጉዳይ የአስተዳደር ችግር እንጅ የማንነት አይደለም!” በማለት “ወልቃይት የኛ ነው!” የሚል አንባገነናዊ አቋሙን ግልጽ ያደረገ ግለሰብ ነው፡፡

አሁን ፓርቲው “የወልቃይት ጉዳይ በሕዝበ ውሳኔ እንዲፈታ ይፈልጋል!” ብሎ ሲል ኃላፊዎቹ በግል ከያዙት አቋም የተለየ ወይም የተሻለ አቋም ማንጸባረቁ ሳይሆን የወያኔ ሕገመንግሥት “መኖሪያውን በቦታው ካደረገ 5 ዓመታትና ከዛ በላይ የሆነ ሰው ሁሉ በሕዝበ ውሳኔ የመሳተፍ መብት አለው!” ስለሚልና ወያኔ ከትግራይ እያጋዘ ያሠፈረው ሕዝብ እያፈናቀለ፣ እያሳደደ፣ እየገደለ በእጅጉ ካመናመነው ከነባሩ የወልቃይት ሕዝብ ቁጥር በእጅጉ የሚበዛ መሆኑን ስለሚያውቁ ሕዝበ ውሳኔው እነሱኑ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ በመተማመን የያዙት አቋም ነው፡፡ በመሆኑም የፓርቲው አቋም እነ አብርሃ ደስታ በግል ከያዙት አንባገነናዊና ፋሺስታዊ (አረመኔያዊ) አቋም የተለየ አይደለም፡፡
በወልቃይት ጉዳይ ላይ ታች አምና በቅሊንጦ እስር ቤት እያለሁ ከአብርሃ ደስታ ጋር በተነጋገርንበት ጊዜ አንድ ያነሣልኝ ነጥብ ነበረ፡፡ ምን አለ መሰላቹህ “የጎሳ ፌዴራሊዝም (ራስ ገዝ) ወይም ይሄ የአማራ ክልል ነው፣ ይሄ የትግሬ ክልል ነው፣ ይሄ የኦሮሞ ክልል ነው… የሚባለው ነገር የሚቀር ከሆነና ዜጎች በፈለጉት የሀገሪቱ ክፍል የመኖር ሙሉ መብት ካላቸው ወልቃይት የአማራ ነው! የሚለውን ነገር ምን አመጣው?” ብሎኝ ነበር፡፡

እኔም ስመልስለት “የትግሬ ነው የሚለውንስ ምን አመጣው? ነገር ግን እኔ እያልኩ ያለሁት የጎሳ ፌዴራሊዝም (የራስ ገዝ ሥርዓት) እንዳይኖር እንዲጠፋ እንፈልጋለንና የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የትግሬ… የሚባል ነገርም አይኖርምና ወልቃይት የአማራ ነው ወደአማራ መመለስ አለበት ሳይሆን እያልኩ ያለሁት ወልቃይት የጎንደር ነውና ወደ ጎንደር መመለስ አለበት! ነው እያልኩ ያለሁለት! በግፍ ተፈናቅለው፣ ተነጥቀው እንዲሰደዱ እንዲጠፉ ተደርገው መሬታቸው፣ ቤት ንብረታቸው ለሠፋሪ ትግሮች የተሰጠባቸው ወገኖች ንብረታቸው ከካሳ ጋር ሊመለስላቸው ይገባል! ይሄንን የፍትሕ ጥያቄ ሳንመልስ መቸም ቢሆን ፍትሐዊና ዲሞክራሲያዊ (መስፍነ ሕዝባዊ) ሥርዓትን መሠረትን ልንል አንችልም!” ብየ ነበር የመለስኩለት፡፡ በወቅቱም አብርሃ ባልኩት ነገር ተስማምቶ ነበር አሁን ላይ ቢያፈርሰውም፡፡

እናም በእነኝህ ምክንያቶች አረና ትግራይ ኢትዮጵያንና ሕዝቧን የሚያስቀድም የማንነትና የብስለት ደረጃ ላይ ሊደርስ የማይችል ድውይ ጠባብ ጎሰኛ ፓርቲ በመሆኑ ሌሎች ወገኖች ተታላቹህ “ከሱ ጋር አብረን ሀገር አቀፍ የአንድነት ፓርቲ እንመሠርታለን!” ብላቹህ እንዳትጃጃሉና መጠቀሚያ እንዳትሆኑ ከወዲሁ አጥብቄ ማሳሰብና ማስጠንቀቅ እወዳለሁ!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!! ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
amsalugkidan@gmail.com

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመነሳቱ በፊት ሕገወጥ ቤቶችን ለማፍረስ ታስቧል

$
0
0

ዋዜማ ራዲዮ- በአዲስ አበባ የአስሩ ክፍለ ከተማ ሥራ አስፈጻሚዎች ከተሸኘው ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ ሕገ ወጥ ግንባታዎችን ማፍረስ በሚቻልበት ሁኔታ ዙርያ እየመከሩ ነው፡፡ ከንቲባ ድሪባ በሚመሩት በዚህ ዝግ ስብሰባ ላይ ከቀረቡ አከራካሪ ነጥቦች አንዱ በአዲስ አበባ አራት ክፍለ ከተሞች በሚገኙ ሰፋፊ ሕገ ወጥ ግንባታዎች የማፍረስ ዘመቻ መቼ ማካሄድ አለብን የሚለው ነው፡፡

በዚህ ዝግ ስብሰባ ከአስሩ የሥራ አስፈጻሚዎች በተጨማሪ የየክፍለ ከተሞቹ የመሬት ልማትና ከተማ ማደስ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች ከሁለተኛው ቀን ጀምሮ እንዲገኙ ተደርጓል፡፡

ከወራት በፊት በተደረጉ ተመሳሳይ የመስተዳደሩ ከፍተኛ ኃላፊዎች የተገኙባቸው ስብሰባዎች በ2009 አዲስ የማፍረስ መርሐ ግብር እንደማይኖርና ከዚያ ይልቅ የፈረሱ ቦታዎችን ለባለሐብቶች የማስተላለፍና የማልማት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በስፋት ሲነገር ቆይቷል፡፡ ይህ አቋም ተይዞ የነበረው አገሪቱ አጋጥሟት ከነበሩ ሕዝባዊ አመጾች ጋር በተያያዘ ነዋሪዎችን ለማረጋጋት እንደነበር ይገመታል፡፡

አሁን የአዲስ አበባ መስተዳደር የአቅጣጫ ለውጥ ለማድረግ እየመከረ እንደሚገኝ በጉለሌ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማት ማኔጅመንት ቢሮ የሚሰሩ አንድ ኃላፊ ለዋዜማ ተናግረዋል፡፡ ይኸውም የማፍረስ ዘመቻን ላልተወሰነ ጊዜ ከማዘግየት ይልቅ  የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመነሳቱ ቀደም ብሎ ቢካሄድ ለቁጥጥር አመቺ መኾኑ በአንዳንድ ሹማምንት ዘንድ በመታመኑ ነው፡፡

ኾኖም በርሳቸው የግል አመለካከት የማፍረስ ተግባሩን መስተዳደሩ ልጀመር ቢል እንኳ የደኅንነት መዋቅሩ ይህ እንዲሆን ይፈቅዳል የሚል ግምት የላቸውም፡፡ “በኔ እምነት በመጪዎቹ ጥቂት ዓመታት ዉስጥ አዲስ አበባ ላይ ቤት ማፍረስ የሚታሰብ አይሆንም፡፡” 

የካ፣ ኮልፌ ቀራንዮ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶና አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተሞች ዉስጥ በድምሩ ከ40ሺ የሚልቁ ሕገወጥ ግንባታዎች እንደሚገኙ ይነገራል፡፡ ባለፈው ዓመት መጨረሻ በግብረ ኃይል እንዲፈርሱ ቀን ተቆርጦላቸው የነበሩ በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ጀሞ ሁለት አካባቢ በተለምዶ ሱቄ ሰፈር፣ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የቀርሳና ኩንተማ ሰፈሮችን የሚጎራበቱ ወረዳዎች፣ እንዲሁም በኮልፌ ቀራንዮ በተለምዶ ስልጤ ሰፈር አካባቢ ይጠቀሳሉ፡፡ ኾኖም የማፍረስ ሂደቱ በድንገት ላልተወሰነ ጊዜ እንዲዘገይ ከመስተዳደሩ መመሪያ ተላልፎ ነበር፡፡

ከዚያ በኋላም አቧሬ ሚስፎርድ ሰፈር፣ ቦሌ አድዋ ፓርክ ዉስጥ የሚኖሩ በርካታ ነዋሪዎች፣ አምባሳደር ፖስታ ቤት ጀርባ ጥቂት የንግድ ቤቶችና መኖርያዎች በአጭር ጊዜ ዉስጥ እንደሚፈርሱ እቅድ ተይዞ ነበር፡፡ ይህም እቅድ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ተፈጻሚ ሳይሆን ቀርቷል፡፡

ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የክፍለ ከተማ የመሬት ማደስ ባለሞያዎች እንደሚገምቱት የማፍረስ ዘመቻው እንዲዘገይ የተደረገው በአገሪቱ አብዛኛዎቹ የኦሮሚያና የአማራ ክልሎች አለመረጋጋት መከሰቱን ተከትሎ ቤት የማፍረሱ ተግባር ቢቀጥል በዋና ከተማዋ ትኩስ እምቢተኝነት ሊቀሰቀስ ይችላል ከሚል ስጋት ጋር ተያይዞ ነው፡፡

ምናልባት አሁን እየተደረገ ባለው ምክክር የ10 ክፍለ ከተማ ሥራ አስፈጻሚዎች ከ2003 ወዲህ የተገነቡ ሕገ ወጥ ግንባታዎችን የማፍረስ ተግባር እንዲቀጥል ከወሰኑ በመጀመርያው ዙር ወደ ተግባር የሚገባባቸው በእነዚሁ አራት ክፍለ ከተሞች የተዘረዘሩ ወረዳዎች እንደሚሆኑ ይገመታል፡፡

ከአንድ ወር በፊት ከአዲስ አበባ መስተዳደር የደንብ ማስከበር ጽሕፈት ቤት የቀረበ አንድ ሪፖርት እንደሚያትተው በ2008 ዓ. ም ብቻ  በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ የሚገኙና ሕገ ወጥ ናቸው የተባሉ 11ሺ 691 ቤቶች እንዲፈርሱ ተደርገዋል፡፡ በሃና ማርያም ሰፈር ደግሞ ተጨማሪ 1ሺ 860 ቤቶች እንዲፈርሱ ሆነዋል፡፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ በአንድ ዓመት ዉስጥ 4ሺ ቤቶች ፈርሰዋል፡፡ በዚህ ሂደት በአንድ ዓመት ዉስጥ በከተማዋ የተፈናቀለው ቤተሰብ ቁጥር ከ30ሺ እንደሚልቅ ይገመታል፡፡

የመስተዳደሩ የደንብ ማስከበር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኮማንደር አሳዬ አምባዬ ከሦስት ወራት በፊት ለመንግሥት ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ሕገ ወጥ ግንባታንና የመሬት ወረራን የመከላከል ሥራው በተያዘው በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለው ነበር፡፡

መስተዳደሩ የመሬት ወረራ የሚፈጽሙ አብዛኛዎቹ ነዋሪዎች ከክፍለ አገር የሚመጡ ዜጎችና በአጭር ጊዜ መክበር የሚፈልጉ የመሬት ደላሎች ናቸው ብሎ ያምናል፡፡ አብዛኛዎቹ ሕገ ወጥ መሬት ወራሪዎች ቁራሽ መሬት ከአርሷደር በካሬ ሜትር እየገዙ አጥረው የሚይዙ ባለሀብቶች እንጂ ቤት አልባ ነዋሪዎች ዋነኛ መሬት ወራሪ እንዳልሆኑ የመስተዳደሩ ኃላፊዎች በተደጋጋሚ ይከራከራሉ፡፡

ባለፈው ዓመት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ልዩ ስማቸው ማንጎ፣ ቀርሳና ኩንተማ በተባሉ ሠፈሮች ሕገ ወጥ የተባሉ ነዋሪዎችን ለማጽዳት በተደረገ ሙከራ የወረዳውን ሥራ አስፈጻሚ ጨምሮ የአምስት ሰዎች ሕይወት ስለመጥፋቱ መዘገቡ አይዘነጋም፡፡ ከዚያ ቀደም ብሎም እንዲሁ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ወረገኑ በተባለ ሰፈር ሕገወጥ የተባሉ ቤቶችን በግብረኃይል ለማፍረስ የተወሰደው እርምጃ ደም አፋሳሽ እንደነበር ይታወሳል፡፡

በደንብ ማስከበር ግብረኃይል በተለያዩ የከተማዋ ሰፈሮች በአስቸኳይ እንዲፈርሱ የሚደረጉ ቦታዎች ለዓመታት እንደታጠሩ ይቀመጣሉ፡፡ በቅርቡ ለመስተዳደሩ ኃላፊዎች የቀረበ አንድ ጥናት በከተማዋ 750 ቦታዎች ታጥረው ለዓመታት ተቀምጠዋል፡፡ እንደምሳሌ ከቀሩቡት ዉስጥ በሜድሮክ ታጥረው የተያዙ ቦታዎች በአማካይ ለ15 ዓመታት ታጥረው ያለምንም ግንባታ ተይዘዋል፡፡

በተመሳሳይ ባለፈው ዓመት መጨረሻ በኃይል እንዲፈርሱ ከተደረጉ ሰፈሮች ዉስጥ አንዳቸውም ከመታጠር ዉጭ ወደ ልማት አልገቡም፡፡

ገንዘቤ ዲባባ በ2000 ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር የዓለም ሪከርድ ሰበረች

$
0
0

ጀግናዋ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በ2000 ሜትር የቤት ውስጥ ሩጫ የዓለም ክብረ ወሰንን ሰበረች:: ከሰዓታት በፊት በስፔን ሳባደል ከተማ በተደረገው የሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊቷ ጀግና በ5:23.75 በመግባት ታሪክ ሰርታለች::

በቤት ውስጥ ውድድር ዛሬ ያስመዘገበችው ሰዓት በተመሳሳይ የውጭ ውድድር ካላት ሰዓት የተሻለ ፍጥነት እንዳለው የስፖርት ባለሙያዎች ተንትነዋል::

ይህ ሪከርድ በገብርኤላ ዛቦ ከ1998 ጀምሮ ተይዞ ነበረ::
በኦሎምፒክ መድረክ ብራዚል ላይ የብር ሜዳሊያ በ1500 ሜትር ያሸነፈችው ገንዘቤ ባለፈው ዓመት በዓለም ሻምፒዮና ወርቅ ማግኝጧ አዘነጋም::

ገንዘቤ በ2015 የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የዓለማችን ምርጥ አትሌት ብሎ እንደሰማት ይታወሳል::

የተስተካከለ ጠባብነትና ትምክህት ለአንድነታችን ጠንቅነው !! – ከአስገደ ገብረሰላሴ መቀለ

$
0
0

አስገደ ገብረስላሴ

ይድረስ የማህበራዊ ሚዲያ ወዳጆቼ ፣ በተለይ ደግሞ በትግርኛ ቋንቋ ባለመጻፌ የምት ወቅሱኝ ይሁን የምትደግፉኝ ሁሉ ፣የሁላችሁን በበጎ ይሁን በመጥፎ የምትተቹኝ አስታያየታችሁ አከብርላችሁ አለሁ ።

የተከበራችሁ ወገኖቼ እኔ ላስታላልፈው የምፈልገው መልእክት በአማርኛ በመጻፌ ጸረ ትግርኛ ቋንቋ ፥እንደሆንኩ በመጥፎ መንፈስ ትፈርጁኝ አላችሁ ።

የተከበራችሁ ወዳጆቼ እኔ ጸረ ትግርኛ ቋንቋ አይደለሁሞ 17 አመት ሙሉ የታገልኩት የኢትዮጱያ ህዝቦች ቋንቋቸው፣ ታሪካቸው፣ ባህላቸው ፣ ሀይማናኖታቸው አስተሳሰቸው ፣ ሰብአዊ ክብራቸውና መብታቸው ፣ እኩልነትና ነጻነታቸው እንዲከበር ታሳቢ በማድረግ ነው ። በተለይ ደግሞ የናቴ ቋንቋ የሆነው ትግርኛ የምወደውና የማፈቅረው የአፌን መክፈቻ ቋንቋ ነው ።

አንድ አንድ ወገኖች ግን ካላቹ የተባላሸ ጠባብ አስተሳሰብ መአዝን እየተንደረደራችሁ ለትምክህተኞች አማራና ጠባቦች ለማስደሰትና ተወዳጅነት ለማግኜት ስትል ነው እያላቹህ ስሜን ታጠፉኝ አላችሁ ። እኔ ከማንም ርካሽ ተወዳጅነት ለማግኜት አስቤም ተመኝቼም አላውቅም ። ለጥቅምና ለርካሽ ተወዳጅነት ብፈልግ ንሮ በህወሐት ኢህአደግ ጉያ በታቀፍኩ ነበር ። ምክንያቱ ከሱጋር መጠጋት ቡዙ ሀብት ለመሰብሰብ ይቻላል ። ግን ሂሊናዬን አይፈቅደውም ።

ግን ማነው ጠባብና ትምክህተኛ ? በእኔ እምነት ቀደም ሲል ገዥዏች የአገዛዝ እድሜያቸው ለመራዘም ለመላው የኢትዮጱያ ሀዝቦች በቋንቋ ፣ በሀይማኖት ፣በአካባቢ ፣በጎጥ ፣በቀለም ፣ እየለያዩ ዜጎች አንዱ ለአንዱ እየተናናቁ እርስ በእርሳቸው እያጣረሱ የህዝቦች ግጭት ተጠቅመው በማኸሉ ተንደላቅቀው ይኖሩ ነበር።

በአሁኑ ጊዜም የናንተ ጌታ የሆነው የኢህአደግ አንባ ገነንና ከፋፋይ ስርአትም ያለፉት ስርአቶች ሌጋሲ በመከተል ዜጎች በአንድነት ተፋቅረውና ተቃቅፈው ከኖሩ ለስልጣን እድሜው ማራዘም ጠንቅና አስጊ በመሆናቸው ፣ መላው የአገራችን ቢሄር ቢሄረሰቦች በቃንቋ በቀለም በወንዝ በመከፋፈል በሁሉም ክልሎች ጥላቻ መቃቃር ፣ የዘረኝነት ጦርነት እንዲነሳ በመቀስቀስ በዝህች ሀገራችን አደጋ እንዲደቀን አድርጓል ።

በመሆኑ በእኔ እምነት በአሁኑ ጊዜ የትምክህትና ጠባብነት ፣የዘረኝነት ግጭት መሀንዲስና ፈለስፋ የኢህአደግ አባል ፓርቲዏች ፣አጋሮቹ እነሱ የሚመሩት ስርአት ናቸው ። ስለዚህ ትምክህተኞችና ጠባቦች እናንተው ናችሁ ።

አንድ አንድ ወገኖች ህዝብ እንደህዝብ በጠባብነትና በትምክህት ፣በዘረኝነት እየፈረጁ ትምክህተኛ አማራ እንደሆነ ። ጠባቦች ለህወሐት ኢህአደግ የሚቃወሙ ክልላዊና የቢሄር ህዝቦች ደግሞ ጠባቦች በማለት ይኮኑኑዋቸዋል ።

እነዚህ ደግሞ በአጋርነት የሚሰለፉ በዛ ሀገራዊ ቋንቋችን የሆነው አመርኛ ለአብዛኛው የኢትዮጱያ ህዝቦች ማግባቢያ ሆኖ ለረጅም ዘመናት የሰራ አማርኛ ቋንቋ ተጠቅመን ሀሳባችን ለኢትየጱያ ህዝቦች መጻፋችን ወይ መልእክት ማስተላለፋችን የአማራ ቅጥሮኞች እያሉ ቁሻሻ አስተሳሰባቸው የሚያሰራጩ ያሉ ተላላኪ ካድሬዎች ናቸው ።እነዚህ ፍጡራን በሙሉ በብቃት የወረዱ በአስተሳሰብ የራሳቸው ነጻ አስተሳሰብ የሌላቸው ጥገኞች ናቸው ።

የተከበራችሁ የድህረገጽ ሚዲያ ተጠቃሚዏች መላው ህዝቦች እኔ በኢትዮጱያ ያሉት ቋንቋዏች ባውቅ ንሮ በሁሉም ቋንቋዏች ሀሳቤ በሳራጭ ደስታው አልችለውም ነበር ። ምክንያቱም ማንም በዚህ አገር ያለው ህዝብ ስለአገሩ ሙሉ መረጃ ማግኜት እንዳለበት እምነቴ ነው ።

አሁን በትግራይ ያለው ሁኔታ በአማርኛ የምትጽፉ ትግሬዏች የትግርኛ ጥላቻ ስላላቹሁና የትምክህተኞች ተላላኪ የምትሉን ያላችሁ ተሳስታችኃል ። በእኔ እምነት በትግራይ ህዝብ ያለው ችግር ፣ ኦሮሞው ፣ሱማሉ ፣ አማራው ፣ ደብብ ህዝቦች ወዘተ ለማወቅ ከተፈለገ አገር አቀፉ ቋንቋችን አማርኛ ስለሆነ በአማርኛ መጻፍ የግድ ይላል ። በሌሎች ክልሎችም እንደዚሁ መሆን አለበት ። እናንተ የምትፈልጉት ግን በየክልልሉ ያሉ ችግሮች እንዳይ ጋለጡ ተደብቀው እንዲኖሩ ወይ እንዲያልፉ ነው ።
በእኔ እምነት በዚህ አገር ገዥዏች ከድንቁርናቸው የመነጨ አልሰሩትም እንጅ ፣ በሀገራችን ቡዙ ቋንቋዏች በካሪከለም ተቀርጸው ሁሉ ህዝብ ተሙሮዋቸው ቢሆን ንሮ አሁን የፋሽሽቶች ማፈንጫ አንሆንም ነበር ። ጠባቦችም አይሸውዱንም ነበር ።በመሆኑ የፈለጋችሁን በሉ እንጅ በፈለግነው በቻልነው ቋንቋ መጻፋችን ልናቁም አይታሰብም ። እነተ ግን የህወሐት የጠባብነትና ትምክሕት ጠበል እየተነከራችሁ ኑሩበት ።
ከአስገደ ገብረሰላሴ መቀለ ፣
30 / 5 / 2009 ዓ ም

በሚሰማው ጉድ ኢትዮጵያውያን እግዚኦ እንበል! – ነፃነት ዘለቀ

$
0
0

 

በስንቱ አፍረን እንደምንዘልቀው አሁንስ እጅጉን ግራ ገባኝ፡፡ ይሄኮ ከነፍስ ግድያ አይተናነስም፡፡

ዐረቦች እንዲህ ይቀልዱብናል አሉ – ከተጨባጩ እውነት ስንነሳም በጣም ልክ ናቸው፡፡ እየጎመዘዘንና እየመረረንም ቢሆን ልንቀበለው ይገባል፡፡ የብዙዎቻችን ወቅታዊ ምግባር ገሃድ እያወጣብን የሚገኝን መጥፎ አድራጎት በማይበጥ የታሪክ ድርሣንና በከንቱ ውዳሤ ልናድበሰብሰው ብንሞክር “ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ” እንደሚባለው ከመሆን አይዘልም፡፡

ፈጣሪ ሀበሻን መንገድ ላይ ያገኘዋል፡፡ “አንተ ሀበሻ፣ ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ? የፈለግኸውን ጠይቀኝ አደርግልሃለሁ፡፡ ነገር ግን ያን የማደርግልህን ነገር ለጓደኛህ ዕጥፍ አደርግለታለሁ፡፡” ይለዋል፡፡ ሀበሻውም “ላስብበትና ልንገርህ ጌታ ሆይ!” በማለት ለማሰቢያ የሚሆን ፋታ እንዲሰጠው በትህትና ይጠይቀዋል፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሀበሻው አስቦ አስቦ ሲጨርስ እፈጣሪ ዘንድ ይቀርብና “ጌታየ አንድ ዐይኔን አጥፋልኝ!” ብሎ ይጠይቃል – የጓደኛው ሁለት ዐይን እንዲጠፋ – እርሱ ግን በአንድ ዐይኑ እንዲኖር፡፡ ይህን ወደ እውነት የቀረበ ተረት በበሬ አስመስለው የሚያወጉትም አሉ፤ አንዱን በሬውን እንዲገድልለት ይጠይቅና የጓደኛውን ሁለት በሬዎች እንዲገድልለት፡፡

ሀበሾች ስንትና ስንት ደጋግ ማኅበራዊ ዕሤቶች እንዳልነበሩን አሁን አሁን ለይቶልን የምቀኝነት መፍለቂያ ዋሻ መሆናችን በጣም የሚያሣዝን ነው፡፡ ምን እንደሚሻለን እግዜር ይወቅልን፡፡ ከፈጣሪው ጋር የታረቀ እውነተኛ የሃይማኖት አባት ቢኖረን ኖሮ ብሔራዊ የምህላና የእግዚኦታ ዐዋጅ የሚያሳውጅ አደገኛ የቅስፈት ዘመን እንደመጣብን ተረድቶ ሕጻናትና ጥጆች ሳይጠቡ ወደ ላይ እንድንጮህ ያደርግ ነበር፡፡

ይህን ብሶት የምናገረው በሰሞነኛ ጉዳዮች እጅግ ስለተደናገጥኩ ነውና ጥቂት ንጹሓንና መልካም ሰዎችን ይቅርታ ልጠይቅ ይገባኛል፡፡ በነገራችን ላይ ያ ሙግድ አፍ አቦይ ስብሃት የሚሉት ሰድቦናል አሉ፡፡ ሲያንሰን ነው፡፡ ይህ አሳዳጊ የበደለውና ጥላቻንና ቂም በቀልን ሲጋት ያደገ ሰውዬ ምን ብሎ እንደሰደበን በቅጡ አልሰማሁትም፡፡ ነገር ግን ምንም ቢለን ምን ከርሱ ዘንድ ጥፋት የለበትም ባይ ነኝ፡፡ የርሱ አንዱን መልክ የያዘ ነው፡፡ ከመነሻው ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን አይወድም ብቻ ሣይሆን ከአጥፊዎቿ ጋር አብሮና ተባብሮ ይህችን ቅድስት ምድር ከነታሪኳ ከምድረ ገጽ ሊያጠፋት ተነስቷል፡፡ ስለዚህ የርሱን መሳደብ ከቁም ነገር ጥፎ መናደድም ሆነ ጊዜ ማባከን ምን ላይ ተቀምጦ ምንትስ ገማኝ እንደማለት ነው፡፡ ይልቁንስ የኛን ጉድ እንፈትሸው፡፡ ከርሱ የበለጥን ተሳዳቢዎችና “ነፍሰ ገዳዮች” በየሀገራቱ ተደብቀን የምንረጨው መርዝ ሀገርን እያባላ ነው፡፡ ይህ ቀን ሲያልፍ ብዙዎቻችን እምን እንደምንገባ ሳስበው ከአሁኑ ይጨንቀኛል፡፡ ክፉ ነገር እስኪያልፍ ማልፋቱ ከፋ እንጂ ይህ የባለጌዎች ቀን ያልፋል፡፡ ሲያልፍ ግን ዝም ብሎ አያልፍም፤ ብዙ አቧራ አስነስቶና የጭቃ ደለልን ጠራርጎ ነው፡፡ ያኔ የአሁኑ “እዩኝ እዩኝ” ባዩ “ደብቁኝ ደብቁኝ” ይላል፡፡ ያኔ ብዙ ላለማልቀስ የአሁን ሣቅን መቀነስ ይገባል፡፡ ፍርድ አትቀርም፡፡ ፍርድ ደግሞ ለራስ ነው – የምትሠራት ሁሉ ነፍስ ዘርታ ትጠብቅሃለች – የማምለጫ በርም የለህም፡፡ ተረቱም “ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ…” ይላል፡፡

ሰሞኑን ፕሮፌሰር ኃይሌ ላሬቦን ከሥራ እንዲታገድ ለማድረግ “ኢትዮጵያውያን” በልበ ሙሉነት ማለቴ በልበ ድፍንነት ተንቀሳቅሰዋል አሉ፡፡ ምን ዓይነት ጉዶች ነን? በሰው ሀገር ሊያውም የመናገርና ሃሳብን በማንኛውም መንገድ መግለጽ በተግባርም በዐዋጅም በተረጋገጠበት ሀገር የሰው ፍርፋሪ እየበሉ ወገን ላይ እንዲህ መጨከን ምን ይባላል? የስብሃት ስድብ ታዲያ ከዚህ ጋር እንዴት ይወዳደራል? አሁንም እደግመዋለሁ ሲያሰን ነው፡፡ እስኪ የኅሊና ጓዳችሁን ክፈቱና አስቡት – አካላዊ ዐይኖቻችሁን ጨፍኑና በአርምሞ ሆናች ነገረ ሥራችንን መርምሩ – ወዴት እያመራን እንደሆነ ተገንዘቡ፡፡ ይህን ብልግና እኔ ስም አጣሁለት፡፡ አንድን ሰው የፈለግኸውን ያህል ብትጠላው በእንጀራው አትመጣበትም፤ በባህልም፣ በሃይማኖትም፣ በፍጡርነትም ነውርና ትልቅ ወንጀልም ነው፡፡

ከወያኔ በስተቀር እንዲህ ያለ ፍጡር አለ ብዬ አላምንም ነበር፡፡ ወያኔዎች ግን ሲፈጠሩ ጀምሮ ታህተ-ሰብዕ (subhuman) እንደሆኑ ከተግባራቸው ስለተረዳሁ እነሱ ምንም ቢያደርጉ አይገርመኝም፡፡ ዜጎች አማራ በመሆናቸው ብቻ ባልንም ሚስትንም በብጫቂ ወረቀት ከየሚሠሩበት መሥሪያ ቤት በአንድ ጀምበር ያባረሩና እጅግ በርካታ ቤተሰቦችን በርሀብ አለንጋ የገረፉ አሁን ደግሞ ከዚያም በባሰ በአማራ አካባቢዎች በግልጽና በሥውር ብዙኃንን የሚገድሉ መሆናቸውን ለሚገነዘብ ሰው ወያኔን እንኳን ጦም በማሳደር በኦሽትዊዛዊ የጋዝ ቼምበር ታላቅ ዕልቂትን ከመፈጸም ያፈገፍጋል ብሎ ቅንጣት አይጠረጥረውም – “The Evil that Men Do” የሚል ቆየት ያለ ፊልም አለ – ይህን ፊልም እዩና የወያኔን ዕኩይ ተፈጥሮ ተረዱ፡፡ ከነዚህ “ሰዎች” ብሶ መገኘት ነገን እንድንፈራ ቢያደርገን ታዲያ አይፈረድብንም – ግን መጪውን ጊዜ አንፈራውም፤ ስለምናውቀው፡፡ ሰው ዕድሜ ልኩን አያለቅስማ! ደግማችሁ አስቡት – “እገሌን ከሥራ አስወጡልን!”፤ “ሥራ ስጡልኝ” ይባላል እንጂ እንዴት “ከሥራ አስወጡልን” ይባላል? ለሰሚም እኮ ግራ ነው፡፡

“ወገናችን”ን ከሥራ ለማሳገድ ቆርጦ መነሣት ማለት የሚቀምሰውን እህል ውኃ ማሳጣት ማለት ነው – በዚያውም መግደል፤ ግድያ ደግሞ መሣሪያን አይመርጥም – በጥይት መግደልም በርሀብ መግደልም ያው ነው፡፡ እንዲያውም በጥይት መግደል በርሀብ ከመግደል የበለጠ “ሰብኣዊ” ነው ማት ይቻላል፤ ጣር የለውም ቢኖረውም የርሀቡን ያህል አይጠናምና፡፡ “በጊዜ የጮኸ ጅብ አያሳድረኝም” ይላል የሀገሬ ባላገር፡፡ እንደነዚህ ያሉ ማፈሪያ ዜጎች ወደሚቃዡበት የአራት ኪሎ ቤተ መንግሥት ቢገቡ ፊታቸውን የሚያዞሩበትን ሰው በቆንጨራና  በሜንጫ አንገቱን እንደማይቆርጡት ምንም ማስተማመኛ የለንም፡፡ የገባንበት አረንቋ የተለዬ ነው፡፡ እነዚያ ተቻችለውና ተስማምተው ይኖሩ የነበሩ ብልኅና አስተዋይ የጥንት ኢትዮጵያውያን ወዴት ሄዱ ግን? እነምኖች ነን በነሱ ቦታ የተተካነው? እግዚኦ እንበል! ሱባኤም እንግባ፡፡ በቁማችን ተበለሻሽተናል ጎበዝ፡፡

ይህ ዓይነቱ አሣፋሪ ዘመቻ ደግሞ በአንድ ሰው ላይ ብቻ የተወሰነ አይደለም፡፡ አንድ ኢትዮጵያዊ እውነትም ይናገር ሀሰት ሃሳቡን በሃሳብ መሞገት ሲያቅት ወደዚህ ጫፍ የምንሄድበት አጋጣሚ በተለይ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየተበራከተ ነው፡፡ በሀገር ውስጥ በሕወሓት የተጀመረው ይህ ዓይነቱ ወያኔያዊ ደዌ እየተስፋፋ መጥቶ መላው ዓለምን እያዳረሰ ነው፡፡ ምናልባትም በተቃውሞው ጎራም ይህ ነገር ሳይለመድ አልቀረም፡፡ የራስን ጉድፍ ሳያጠሩ የሰውን ጉድፍ መናገርና ማውገዝ ደግሞ አሣፋሪ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ “በራስህ ዐይን ውስጥ ያለን ዕርፍ እሚያህል ጉድፍ ሳታወጣ በሰው ዐይን ውስጥ ያለን ስንጣሪ ጉድፍ ለማውጣት አትሞክር” ይላል፡፡ ችግሩ በስሜት የሚነዳ እንጂ በአስተውሎት የሚራመድ ትውልድ እያጠጠን (እያጠረን) መምጣታችን ነው፡፡ ራስን መመርመር ቀረ፤ ራስን መመዘን ፋሽኑ አለፈበት፤ ራስን ብፁዕ ሌላውን ኃጥዕ ማድረግ የዘመኑ ፈሊጥ ሆነ፡፡ ምን ይሻለናል?

እኛስ ለምደነዋል፡፡ በተለይ ፈረንጆቹ ይህን ነገር ሲሰሙ በተፈጥሯችን ምን ያህል ይገረሙ?

ለሰላም ማስጠበቅ ሥራ – ወይ ቀልድ – በሀገሩ ሰላም ያለ ይመስል – የወያኔው መንግሥት ጦር ወደ ላይቤሪያ ሄደ አሉ – ቀደም ሲል ነው፡፡ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም እንዲሁ ጦር ተልኮ ነበርና በአንድ ካምፕ ውስጥ ሁሉም ይኖሩ ነበር፡፡ የየሀገሩ የጦር አባላት ካለፈቃድ ከካምፕ እየወጡና ነገር እያበላሹ ስለመጡ ወታደራዊ አዛዦች ተቸገሩ፡፡ ያኔ ከየሀገሩ ጦር አንዳንድ ካቦ ተመርጦ ወገን ወገኑን እንዲቆጣጠር ተወሰነ፡፡ ኢትዮጵያውያን ሊመርጡ ሲሉ ጠባያችንን ጠንቅቆ የሚያውቅ የአፍሪካ ጦር አስተባባሪ ኮሚቴ አንድ አባል “ግዴላችሁም ኢትዮጵያውያኑን አታስመርጧቸው፤ ምክንያቱም ለነሱ ‹አትውጡ› ማለት ብቻ በቂ ነው፡፡ እርስ በርስ ስለሚመቀኛኙ አንዱ ሲወጣ ሌላው ይጠቁማልና በነሱ ችግር አይግባችሁ፡፡”

እስከመቼ እንዲህ እየተቀለደብን እንኑር? መቼስ ነው የምናድገው? የፈረንጆች፣ የአፍሪካውያንና የእስያውያን መሣቂያና መሣለቂያ እንደሆንን ለመኖር የመረጥነው ምን ዓይነት ብዔልዘቡላዊ ንፋስ በመካከላችን ቢነፍስ ነው? ይህ ባሕርያችን እኮ ነው የሚያስንቀንና ለጠላቶቻችን እንደትልቅ የማጥቂያ ሥልት ሆኖ የሚያገለግለው – ትልቅ ሽብልቅ አቀበልናቸውና በዚያ ምሣር አለ አንዳች ርህራሄ ይሰነጣጥቁን ገቡ፡፡ ብዙ ሳይለፉ በቀላሉ የሚያሸንፉን በውስጣችን በተሰገሰገው የምቀኝነት መንፈስ ምክንያት ነው፡፡ በዚህ አስቀያሚ ጉዞ ከቀጠልን መቼም ቢሆን ሀገርና መንግሥት አይኖረንም፡፡ ይህን የምለው ምርጫችን ይህ ሆኖ ከቀረ ለማለት ፈልጌ እንጂ ጉድፋችንን መጥረግ ብንጀምር ፈጣሪ የሚታደገን መሆኑን አጥቼው አይደለም፡፡ “እሹ ታገኛላችሁ፤ አንኳኩ ይከፈትላችኋል” አይደለም እንዴ እርሱ ራሱስ የሚለን? ምን ከማን ለማግኘትና እንዴት ማግኘትም እንደምንችል ካላወቅን ከግብጽ ከነዓን ለመግባት ለ40 ዓመታት በበረሃ እንደተንከራተቱት የጥንት እስራኤላውያን መሆናችን ነው – የሣምንቱን መንገድ፡፡ ስለዚህ የምትፈልገውን አለማወቅም ከባድ ችግር ነው፡፡

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እንኳን ይህ ከሥራ አባርሩልን የሚሉት ፈሊጥ በስንት ወገኖቻችን ላይ እንደተሞከረ በጸጸት የምናስታውሰው ነው፡፡ እባክህን አንድኛህ አንባቢ ይህን ነገር ከየመዛግብቱ ልቀምና በማን ላይ ማን ወይም እነማን እንደዘመቱበት ጉዳችንን አስነብበን፡፡ ሀፍረትና ይሉኝታ እንደሆኑ ከሀገራችን ለይቶላቸው ከኮበለሉ 40 ዓመት አለፋቸው፡፡ “ዘይገርም ሻሸመኔ ትብስ ኮፈሌ” አሉ? ይህ እኮ መቅሰፍት እንጂ ሌላ እንዳይመስላችሁ – ሰዎች እንዴት ቢያስቡ ነው – ምን ዓይነትስ አንጎል ቢኖራቸው ነው – ወደዚህን መሰል ቅሌት የሚወርዱት? “እገሌን ከሥራ አስወጡልን!” ብሎ ደጅ ጥናትና አቤቱታ? በሌሎች ሀገሮች ይህን ዓይነት ብልግና የሚታወቅ አይመስለኝም፡፡ ከሰውነት ደረጃ እኮ ተሸቀንጥሮ ወደ አዘቅት መውረድ ነው፡፡

ምቀኝነት እንዲህ ፈሩን ለቅቆ በሰው ሀገር በሚታይ ማፈሪያ ድርጊት ሣይቀር ኢትዮጵያውያንን አንገታችንን እያስደፋን ነው፡፡ ከዚህ በላይ አሣፋሪ ነገር የለም፡፡ ለራሱ በጥገኝነት እየኖረ ከአደጋ የተጠለለ ወገኑን ጉሮሮውን አንቃችሁ ግደሉልን ከማለት የበለጠ ፋሽዝምና ናዚዝም ወይም ወያኔነት የለም፡፡ ይሄ አካሄድ በቀላሉ ፀረ-ዴሞክራሲ ነው ተብሎ ብቻ የሚታለፍ አይደለም፤ በሰው ሀገር እንዲህ ያደረገ ሰው ነገ ሥልጣን ቢይዝ ከፍ ሲል ለመጥቀስ እንደሞከርኩት የፀሐይ ብርሃንንና አየርን ሣይቀር  ለየነገድና ጎሣው በራሽን መልክ እንደሚያድል ጥርጥር የለውም – ለዚያውም የኔ ነው ለሚለው ጎሣ የአንበሣ ድርሻውን እየሰጠ፡፡ ከዚህ አኳያ ወያኔን የሚመርጥ ሰው ቢኖር በበኩሌ አልፈርድበትም፡፡ ሰው እንዲህ እየደደበ የሚሄድበት ምክንያት ደግሞ በጭራሽ አይገባኝም፡፡ በስማም….

 


ሰበር መረጃ …..የሰሜኑ እዝ ወታደራዊ የትጥቅ ማከማቻዎች ተፈተሹ !

$
0
0

ጥር / 29 / 2009

ልዑል አለም

በዋና እዝ ዉስጥ የሚገኙ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች በወረደላቸዉ ትእዛዝ መሰረት ወታደራዊ የትጥቅ ማከማቻዎችን እንዲፈትሹ በወጣዉ ትእዛዝ
የ8ኛ ብረት ለበስ ክ/ጦር አዛዥ ብ/ጄ ጀማል መሐመድ፣ የ31ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ብ/ጄ ተስፋዬ ወ/ማርያም፣ የ35ተኛ ክ/ጦር አዛዥ ብ/ጄ ምስጋናዉ አለሙ፣ የ24ተኛ ክ/ጦር አዛዥ ብ/ጄ ሞሐመድ ተሰማ፣ የ22ተኛ ክ/ጦር አዛዥ ብ/ጄ ገ/ እግዚያብሔር በየነ የ33ተኛ ክ/ጦር አዛዥ ብ/ጄ አማሐ ገብሩ ባጠቃላይ የመሳሪያ መጋዘኖቻቸዉ ላይ ከፍተኛ ዘረፋ መፈጸሙን አምነዋል።
በዚህም መሰረት . . . . . . ከጥቂቶቹ ዉስጥ እነርሱም በነጻነት ታጋዬች እጅ ወድቀዋል ተብለዉ የተገመቱትን የቀላል መሳሪያዎች መጠን ዘርዝረዋል…
Makarov ……..Semi-automatic pistol የጎደለ (201 )
Beretta Model 38…….Sub-machine gun የጎደለ ( 191 )
UZI……..Sub-machine gun የጎደለ ( 542 )
AK-103…….Assault rifle የጎደለ ( 5666 )
AK-47…….Assault rifle የጎደለ (1022 )
AKM……..Assault rifle የጎደለ (993 )
PSL (rifle)………Designated marksman rifle የጎደለ ( 9_ 61 )
BM59………Assault rifleLMG BM-59 MK-4 የጎደለ ( 201 )
G3……….Assault rifle የጎደለ (118 )
Vz. 58……..Assault rifle የጎደለ (1598)
RP-46 “Degtyaryov”………Light machine gun የጎደለ (208 )
RPD……….Light machine gun የጎደለ (””””)
RPK……….Light machine gun የጎደለ ( 558 )
DShK……….Heavy machinegun የጎደለ ( 85 )

ማስመዝገባቸዉን ተከትሎ ወታደራዊ ደህንነቱ መመሪያ አዉርዷል በዚህም መሰረት ከላይ በዝርዝር ከተጠቀሱት በተጨማሪ ያልተመዘገቡና የጠሰወሩ እንዳሉ ሁሉ የህወሃት ወታደሮች ሲኮበልሉ ያላስረከቧቸዉ የጦር መሳሪያዎች ሲታከሉበት ወታደራዊ አደጋዉ የከፋ እንደሆነ የተቀመጠ ሲሆን።
ወታደራዊ ዘረፋዉን ለመቀነስ እንዲቻል በሰሜን ጎንደር፣ በቤንሻንጉል ጉምዝ፣ በጋምቤላና፣ በምሳራቅ ኢትዮጵያ ዙሪያ በቅርበት በሚንቀሳቀሱ የሽምቅ ዉጊያ አቀንቃኝ የነጻነት ታጋዮች ላይ ደምሳሽ ወረራ ለመፈጸም ተወስኖ ወደ ተግባር ጦርነት ተገብቷል።
በዚህም መሰረት በተለየ መልኩ በሁመራ እና አካባቢዉ ላይ ትኩረት የተወሰደ ሲሆን በዚያ አካባቢ ላይ የሚደረጉ የነጻነት ሐይሎችን እንቅስቃሴ ለአካባቢ ልዩ ሐይል እና ለመከላከያ በመጠቆም የተሳተፉ ግለሰቦችን ዝርዝር የያዘ ሰነድ ለወታደራዊ ደህንነቱ ተዛዉሮለታል።
ወታደራዊ ደህንነቱ ለነዚህ የህዝብ ጠላት በተለይም የነጻነት ሐይሎችን እንቅስቃሴ ዝዉዉር ለሚጠቁሙ ግለሰቦች የሚያደርገዉን ጥበቃ ተመልክቶ በትእዛዝ መልኩ ወደታች ካወረደበት ከመስከረም / 2009 ዓ/ም አንስቶ ጠቋሚዎቹ የህዝብ ጠላቶች ማንነታቸዉ ባልታወቁ ግለሰቦች እየታደኑ እርምጃ እየተወሰደባቸዉ እንደሚገኝ ከወታደራዊ ደህንነቱ የወጣ ፍንጭ አረጋግጧል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

ልዑል አለም

ዓረና ዓረየ[1]! . አስራት አብርሃም

$
0
0
አስራት አብርሃም

አስራት አብርሃም

አረና የተሳካ ጉባኤ ማካሄዱ እየተነገረ ነው። አረና ብዙ ዋጋ የተከፈለበት ፓርቲ ነው። እናም በዚህ ሰዓት ተስፋ የሚሰጥ ለውጥ በማሳየቱ የተሰማኝ ደስታ ወደር የለውም። የደስታዬ ምክንያትም የመሠረትኩት ብዙ የለፋሁለት ፓርቲ ከመሆኑም በላይ፣ አረና በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ የራሱ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብዬ ስለማምን ነው። የለውጥ ኃይሉ በማቀናጀትና ማጠናከር ረገድ አዎንታዊ ሚና ሊኖረው ይችላል።

ከዚህ ጉባኤ ውጤት መረዳት እንደቻልኩት የአዲሱ ትውልድ አመራር ወደፊት አምጥተዋል። ነባሩ አመራርም በስራ አስፈፃሚና በማከዕላዊ ኮሚቴ ውስጥ ተካተዋል። ይሄ ጥሩ የአመራር ውህደት የሚፈጥር ነው። ይሄ ለውጥ በተለይ ለነባሮቹ የአረና አመራሮች ለአቶ ገቡሩ አስራት፣  ለወ/ሮ አረጋሽ አዳነ፣ ለአቶ አውዓሎም ወልዱ እና አቶ ብርሀኑ በርሀ ልዩ ኩራት የሚሰጥ ነው የሚመስለኝ። በየጊዜው በፓርቲው ውስጥ ይታዩ የነበሩ ችግሮች ምክንያት ተስፋ ሳይቆርጡ በትዕግስት እስካሁን ቆይተው የልፋታቸውን ውጤት ማየት ችለዋል። የሚያዩበት ሰዓት ላይ ደርሰዋል። አቶ ብርሃኑ በርሀ እንደማነኛውም ሰው የራሳቸው የሆነ ድክመቶች ቢኖራቸውም በዓረና ምስረታ ላይ የነበራቸው የማይተካ ሚና እና የደከሙት ድካም ማስታወስ ያስፈልጋል። ማናችንም ብንሆን ከስህተት ንፁህ አይደለንም፣ አቶ ብርሃኑ በርሀ ከሊቀመንበርነት ቢወርዱም አሁን ባሉበት የማዕከላዊ ኮሚቴ ቦታ ላይ ሆነው ብዙ አስተዋፅኦ ማድረግ የሚችሉ ናቸው። የገብሩ አስራት መንገድ ነው መከተል ያለባቸው፣ ልክ እንደ አቶ ገብሩ በአዎንታዊ መንገድ ተፅዕኖ መፍጠር ይችላሉ፣ በፓርቲ ውስጥ አስተዋፅኦ ለማድረግ መሪ መሆን የግድ የሚያስፈልግ አይደለም። ዝቅ ብሎ በትህትና ማገልገል ታላቅ ፀጋ ነው። አሁን ዓረና ሁለት ነባር ሊቃነ መነቃብርት ይኖሩታል ማለት ነው።

በፊት በፓርቲው ውስጥ የነበሩ፣ ብዙ የደከሙና በሂደት በልዩነት የተለዩት እንደነ አቶ አስገደ ገብረስላሴ ያሉትም ቢሆን ለውጡ የሚያስደስታቸው ነው። ሲመኙት የነበረ፣ ሲታገሉለት የነበረ ጉዳይ ነውና። በእርግጥ ፓርቲው እንዲህ ሲጠናከር ለውጥ የሚፈልግ ሁሉ ደስ የሚያሰኝ ነው የሚሆነው። በአረና ውስጥ ከመጀመሪያው ጀምሮ ችግር የነበረው የአባታዊነት አስተሳሰብ ያከተመ ይመስላል። ያለምንም ጫጫታ ራሱን ገምግሞ፣ በሂደት የአመራር ድክመት ያሳዩትና መሰረታዊ ችግር የነበረባቸው በሌላ አዲስ አመራር መተካት ተችለዋል። እንደ አብርሃ ደስታ፣ ጎቶኦም ፀጋይ፣ ኪዳነ አመነ፣ አንዶም ገብረ ስላሴ፣ ተክለዝጊ፣ ሕድሮም፣ የመሳሰሉ ብዙ ወጣቶች ወደፊት መጥተዋል። የአሁን ፓርቲው ከነበረበት ወደፊት የማራመዱ ጉዳይ በአዲሱ ትውልድ አመራር ጫንቃ ላይ ወድቀዋል። የሀገራችን ፖለቲካ እጅግ አስቸጋሪ ቢሆንም የተሰጣቸውን ኃላፊነት በደንብ ይወጡታል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።

ሌላው እጅግ ደስ ያለኝ ጉዳይ ዶ/ር ማርቆስ ገሰሰ የመሰለ የመርህ ሰው ከደጋፊነት ወደ አመራር መምጣቱ ነው። ዶ/ር ማርቆስ ገሰሰ ማለት ለዓረና ብዙ ነገር ነው፣ ወጣቶችን የሚመክር፣ የሚያበረታታ፣ ለፓርቲው በተቻለው ሁሉ ድጋፍ የሚያደርግ፣ ሌላው ቀርቶ የራሱ ሆስፒታል ህንፃ ላይ ለፓርቲው ዋና ፅህፈት ቤት የሚሆን በነፃ የሰጠ ሰው ነው። ሀወሃትም ዓረናም ለዚህ አቋሙና እምነቱ ብዙ ዋጋ የከፈለ አሁንም እየከፈለ ያለ ጀግና ነው። ብዙዎቹ ባለሀብቶች በምንም ነገር መጎዳት ስለማይፈልጉ ተቃዋሚዎችን ለማገዝ ፍላጎት የላቸውም፣ ዶ/ር ማርቆስ ግን ከእነዚህ በጣም የተለየ ነው፣ ይህም ነው ክብር እንድትሰጠው የሚያደርግህ።

እንግዲህ ዓረና በውህደት መልክም ይሁን በሌላ መንገድ ወሳኝ ሀገራዊ ኃይል የሚሆንበት ጊዜ ወደፊት እየጠበቀው እንደሆነ መጠቆም እፈልጋለሁ። በሀገር ጉዳይ ላይ ተስፋ መቁረጥ አይገባምና ወደፊት ገፍቶ ያሉትን አማራጮች ሁሉ መሞከሩ የተሻለ ነገር ይሆናል። አዲስ ለተመረጡትም ለነባር አመራሮቹም መልካም የትግል ዘመን ይሁንላችሁ ለማለት እፈልጋለሁ።

[1] ዓረየ የትግርኛ ቃል ሲሆን፣ ተስተካከለ ማለት ነው።

በሴረኞች የዐማራ ሕዝብ ተጋድሎ አይቀለበስም! – ሙሉቀን ተስፋው

$
0
0

ሙሉቀን ተስፋው

ከጥር 29 ቀን 2009 ዓ/ም በሰሜን ጎንደር በምዕራብ በለሳ የሚኖሩ ዐማሮች በወያኔ መከላከያ ሠራዊት ቤታቸውና ንብረታቸው እየወደመ ይገኛል፤ የሚያሳዝነው ደግሞ ሌላው ወገናቸው ችግራቸው በሚገባ ያልታወቀ መሆኑ ነው፡፡

ከዚህ የከፋም ችግር አለ፤ የዐማራ ተጋድሎ አስተባባሪ የጎበዝ አለቆች በድብቅ ስብሰባ መጥራታቸውን ወያኔን እንቃወማለን በሚሉ ነገር ግን ደግሞ የዐማራ ሕዝብን ዐማራዊ ተጋድሎ ለቡድናቸው ወይም ለድርጅታቸው ሕልውና አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳድራሉ በሚባሉ ወገኖች ጠቋሚነት መሆኑ ነው፡፡

ከዐማራ ተጋድሎ አስተባባሪ የጎበዝ አለቆች ጋር በመተባበር አንድ ስብሰባ እንዲጠራ ይደረጋል፤ ብዙዎቹ የጎበዝ አለቆች ተጠራጥረው ሳይሔዱ ቀሩ፡፡ ሆኖም ሁሉም ይመጣሉ በተባለበት ሰዐት የወያኔ ወታደሮች እስከአፍንጫቸው ታጥቀው በለሳ መሸጉ፡፡ ሁሉንም ለማስቀረት ቢሞከርም በዐማራ ታጋዮች ላይ ምንም ዓይነት የሰው ሕይወት ሳይጠፋ በጀግንነትና በወኔ የወያኔን አጥር ሰብረው ሊወጡ ችለዋል፡፡ ሆኖም ከመካከል የነበረ አንድ ሰው ጠፍቷል ተብሏል፡፡

የሚያሳዝነው ግን ከቅዳሜ ዕለት ጀምሮ የበለሳ ገበሬዎች ቤትና ንብረት በግፍ እየወደመ ነው፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ መሠረት ከሃያ የማያንሱ ቤቶች በኮዛ አቦ አካባቢ በከባድ መሣሪያ ወድሟል፡፡ ከመቶ ያላነሱ ቤተሰቦችም ያለ መጠለያ ተበትነዋል፡፡ ምን ዓይነት ችግር ውስጥ እንዳሉና እንደሰነበቱ ሌላው ዐማራም አላወቀውም ገና፡፡
የዐማራ ተጋድሎን ለማኮላሸት ለወያኔ መረጃ በመስጠት የተባበሩ አካላት በዐማራነት መደራጀትን እየኮነኑ እንደገና እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ ስንሰማ ደግሞ የበለጠ አዝነናል፡፡ ይህ ጉዳይ በሚገባ እየተጣራ በመሆኑ የዐማራ ተጋድሎ አስተባባሪ የጎበዝ አለቆች ትምህርት የሚወስዱበት አጋጣሚ ይሆናል፡፡

እንደማጠቃለያ ማንም ሰው (ቡድን) የፈለገውን ርዕዮተ ዓለምና አደረጃጀት ይዞ መጓዝ ይችላል፤ ሆኖም በዐማራ ሕዝብ ላይ የሚሸርቡትን ሴራ ማቆም አስፈለጊም ብቻ ሳይሆን ግዴታም ጭምር ነው፡፡ የዐማራ ሕዝብ ትግል ላይቀለበስ ተቀጣጥሏል፡፡


የዐማራ ሕዝብ ትግል ያሸንፋል

 

“ድር ያደራበት ብዕርዎትን ከሰገባው ባያወጡት ይሻል ነበር!”

$
0
0

“…መሃል ፒያሳ ላይ መርከብ እንዲያንሳፍፍልዎ ነበር እንዴ የፈለጉት? ወይስ አይሮፕላን  አኮብኩቦ እንዲያሳርፍልዎ?”

አልታዬ የተባሉ ጸሃፊ በቅርቡ “…ለረጅም አመታተ የጣሉትን ብዕር ድር ካደራበት ሰገባው…” መዝዘው “የተቆለፈበት ቁልፍ” በቃላት ቁልፍ ተቆላልፏል!” በሚል ርዕስ አስነብበውናል።  ዶ/ር በፍቃዱ በቀለ በ“የተቆለፈበት ቁልፍ” መጽሃፍ ላይ በጻፉት ግምገማ ላይ ተነስተው ትችታቸውን ያስነበቡን አልታዬ፣ ከስነ-ጽሁፋዊ ትችታቸው በፊት ያስቀደሙት፣ ዶ/ር በፍቃዱ፣ በየተቆለፈበት ቁልፍ መፅሐፍ ላይ ያቀረቡት ጽሁፍ  “…የወዳጅነት ፍቅር፣ አክብሮትና ስሜታቸውን ነው ወይስ በእውነት ምክንያታዊ ትችታቸውን?!…” በሚል፣ ምናልባትም “speculation” (ተጨባጭ ማስረጃ የሌለው “ቲዎሪ”) ነው። እንኳንስ አይደለም “ወዳጅ”፤ አባት እና ልጅ ቢሆኑስ አልታዬን ምን አገባዎት? ልጅ የአባቱን፣ አባት የልጁን ስነ-ጽሁፍ ስራ ቢተች ምን ችግር አለው? ትኩረትዎን ለምን ሃሳቡ እና ጽሁፉ ላይ አላደረጉም? ወዳጅነታቸውንስ መጥቀስ ለምን አስፈለገ? “speculation” ካልሆነ ደግሞ የዶ/ር በቀለን እና የደራሲውን ወዳጅነት አልታዬ ያውቃሉ? ምናልባትም ጽሁፉ ከእውነተኛ ስነ-ጽሁፋዊ ትችት ይልቅ “character assassination”/ሃሳብን ሳይሆን ግለሰብን ማጥቃት (ad hominem) አያስመስልብዎትም?

በመሰረቱ አልታዬ መጽሃፉን የተቹበት አንድ እና አንድ ጉዳይ ቢኖር ደራሲው ዶ/ር ምህረት ደበበ የተጠቀሙበትን ቋንቋ ነው። “….በየተቆለፈበት ቁልፍ መፅሐፍ ውስጥ ተመሳሳይ ቃላት ከመጠን በላይ ተደራርበው ነው የምናገ…..” ሲሉን፣ ባጭሩ “ለምን ቃላት ተደጋጋሙ” ነው። በግምት 99% የሚሆነው የአልታዬ ትችት “ለምን ቃላት ተደጋጋሙ” የሚል የመሆኑን ያህል፣ ተደጋገሙ ላሏቸው ቃላት ምትክ የሚሆኑ ሌሎች የቃላት አማራጮችን አንዴም (እደግመዋለሁ፤ አንዴም፣ አንዲት ቃል እንኳን ተክተው) አላሳዩንም። ከመጽሃፉ ውስጥ የከበብቧቸውን ቃላት እና ሃረጋት እየጠቀሱ (“ይሄ”፣ “ያ” ወዘተ የሚሉ ቃላት ባይገቡ …እንዲህ…..ቃላት ያልተደጋገሙበት ዓ/ነገር ወይም አንቀጽ ይሆን ነበር…”) ብሎ መተቸትም ያባት ነው። በአንድ ሙሉ አንቀጽ (አንዳንድ እስከ 500 በሆኑ ቃላት በተገነባ) ውስጥ አንድ ቃል ለምን ሁለት ጊዜ ተጠቀሰ…” በሚል እና በመጽሃፉ የሰፈሩትን ተመሳሳይ ቃላቶች እየለቀሙ በማክበብ “ቃላት ተደጋገሙ” ማለት ሙያዊ ትችት አይደለም።

ከስነ-ጽሁፍ አላባዎች ውስጥ አንዱ የሆነው “ቋንቋ” አልታዬ ካዩበት ማዕዘን (የቃላት መደጋገም) በላይ ቢሆንም፣ ቃላት ካለቦታቸው እየተሰደሩ ሲደጋገሙ፣ የቋንቋን ውበት እንደሚያደበዝዙት እርግጥ ነው። አልታዬ ተደጋገሙ የሚሏቸውን ቃላት፣ በሌላ የተሻለ ቃል፣ ቃላት ወይም ሃረግ ሊገለጹ ይችሉ የነበሩ መሆናቸውን እና ባቀረቧቸው ምትኮች ሳቢያ ቋንቋው የተሻለ መሆኑን ቢያሳዩን ኖሮ፣  አላግባብ ተድጋግመው ቃላት የባከኑበት ጽሁፍ መሆኑ ይገለጽልን ይሆናል። አልታዬ የከበቧቸው ቃላት ሁሉ አንድም ቦታ አላግባብ የባከኑም፣ የቋንቋውን ውብት ያደበዘዙም አይደሉም። “… እኔ ነኝ” ያለ የአማርኛ ቋንቋ ሊቅ ቢመጣ፣ አልታዬ በቀኝ በኩል ከመጽሃፉ ቀድቶ በከበባቸው አብዛኛዎቹ ቃላት ምትክ ሌላ ቃላት ቢያስገባ፣ ከደራሲው ሃሳብ የተሻለ ቀርቶ፣ ያለውን ሃሳብ መግለጽ የሚችል ዓ/ነገር መስራት የሚችል አይመስለኝም (ይሄ የቤት ስራ ለአልታዬም ነው)

“የተቆለፈበት ቁልፍ” በሚል ርዕስ በተጻፈ መጽሃፍ፣ “ቁልፍልፍ” በሚል ርዕስ በተጀመረ ምዕራፍ፣ በመጀመሪያው አንቀጽ ላይ “ቁልፉን” የሚል ቃል ለምን ተጠቀሰ የሚል ትችት ማቅረብ የስነ-ጽሁፍ እውቀት ድህነት መገለጫ ነው። በሁለተኛው አንቀጽ፣ መጀመሪያ መስመር ላይ “ተቆልፎአል” በሚለውስ ምትክ ምን አይነት ቃል/ሃረግ ሊገባ ይችል ነበር?–“ተዘግቷል?”፣ “ተከርችሟል?”፣ “ተጠርቅሟል”?

አልታዬ “ቋንቋ”፣ እንደ አንድ የስነ-ጽሁፍ አላባ፣ ምን ማለት እንደሆነ ያወቁ አይመስለኝም። ደራሲው ዶ/ር ምህረት ደበበ የተጠቀመበት የቃላት ድግግሞሽ፣ አንዱ የአጻጻፍ ስልት ነው፣ በእንግሊዝኛ “Repetition” ነው። የመጽሃፉ ርዕስ “የተቆለፈበት ቁልፍ” ራሱ “Repetition” አለው፣ ድግግሞሹ የፈጠረው (በግጥም ውስጥ እንደምናየው የመጨረሻው ድምጽ መመሳሰል አይነት) “ዜማ” አለው፤ በእንግሊዝኛው “Rhythm” እንዲሉ። ግርምታ የሚፈጥር ርዕስ ነው፣ የመጽሃፍ ርዕስ (Eye catchy) መሆን አለበት እንደሚሉት ነው። ርዕሱ ድንቅ ነው። በሁለተኛው አንቀጽ ላይ የተጠቀሱትም የ“ቁልፍ” እርባታዎች፣ ርዕሱን የሚገልጹ፣ ታሪኩንም በሚገባ ለማስተዋወቅ የገቡ ናቸው፣ ( ‘የተቆለፈበት ቁልፍ’ የሚለውን ርዕስ እያሰብን…“ወይ ጉድ! ገና ካሁኑ መኪናው ውስጥ መግቢያ የሆነውን የመኪናውን “ቁልፍ” ረስቶ “ቆልፎበት” ወርዶ፣ የቤቱም “ቁልፍ” እዚሁ መኪናው ውስጥ “ተቆልፎበታል”…. እና ‘ይሄን ሰውየ ምን ሊውጠው ነው?) የሚል የንባብ ጉጉት (suspense) ያጭራል አንቀጹ። ደራሲው በትክክለኛው መቼት (setting)፣ እጅግ ብቃት ባለው (efficiently) ሁኔታ ነው የቃላት ድግግሞሹን  “Repetition” የተጠቀመበት።

“Repetition in literature” ወይም “Repetition as a literary device…” የሚለውን ቀድተህ ጎግል ላይ ብትለጥፈው ምናልባትም በሺዎች የሚቆጠሩ፣ “Repetition is a powerful force in fiction” አይነት ዓ/ነገሮች፣ ከተለያዩ ምንጮች ተኮልኩለው ይደረደሩልሃል። ድግግሞሽ የልብ ወለድ ድርሰት አጻጻፍ አንዱ “ጉልበታም” ስልት/ዘዬ ነው…።

በቀኝ በኩል አላታዬ በሶስተኛው መስመር ላይ ያከበቡት “ከሰው” የሚለው ቃል፣ በሚቀጥለው በ4ኛው መስመር ላይ ከተጠቀሰው “ሰው” ጋር መደጋገሙን ለማሳየት ሲሉ ያደረጉት ነው ብለን እንለፈው። ደህና። በ4ኛው መስመር ላይ የተጠቀሰው “ሰው”፣ በምን ሊተካ ይቻል ነበር? “ተሳፋሪ?” አያስኬድም። ምክንያቱም ሰው የሆኑትን ወያላውን፣ ሾፌሩንም  ታናግራለች። ወይስ ደራሲው ለአልታዬ ሲል አንበሳ ያሳፍርለት እንዴ? አንቀጽ ሶስት ላይ በተጠቀሰው “ታክሲዎች” ምትክ ደራሲው መሃል ፒያሳ ላይ መርከብ እንዲያንሳፍፍልዎ ነበር እንዴ የፈለጉት? ወይስ አይሮፕላን  አኮብኩቦ እንዲያሳርፍልዎ?”

አልታዬ ራሳቸው “…እንደተቆለፈበት ተመጋቢ ዘጋኝ – “የተቆለፈበት ቁልፍ ሲሉን እና በአንድ ዐ/ነገር ውስጥ ሶስት ጊዜ “ቁልፍ” ሲሉን  “Rhythmic Repetition” ነው። እሳቸው የተጠቀሙበትን ይህን ጥበብ ሌላው መጠቀም የለበትም የሚል ህግ ማን እንዳወጣላቸው የሚያውቁት አልታዬ እና የአልታዬ የስነ-ጽሁፍ  እዚሃር ብቻ መሆን አለባቸው። እውነት ለመናገር አልታዬ “…ከላዩ ላይ ጸያፍ ነገር ዓይቶ ወስፋቱ “እንደተቆለፈበት” ተመጋቢ ዘጋኝ…” በሚል የተጠቀሙበት ቋንቋ ልቅ ነው፣ ቢያንስ ለዚህ መጽሃፍ ደራሲ አይገባውም። ደግሞስ ገንቢ የሆኑ ቃላትን በመጠቀም መተቸት አይቻልም እንዴ?

“ቋንቋ” ሃሳብ መግለጫ ነው፤ ሃሳብን በቀላሉ እና በአጭሩ፣ ግልጽ እና በሚገባ ቃላት እና ዓ/ነገሮች አንሰላስሎ ምሉዕ ሃሳብ ማቅረብ ከቻለ፣ የሚፈለገው እሱ ነው። ደራሲው በዚህ ተዋጥቶለታል፣ እንዲያውም አጫጭር ዓ/ነገሮች፣ ግልጽ እና ቀላል አማርኛ መጠቀሙ፣ ከበዓሉ ግርማ አጻጻፍ ስልት ጋር ይመሳሰላል። እኔ አንድም የባከነ ቃልም ሆነ ዓ/ነገር አላገኘሁም።

“…አንድን መፅሐፍ “ምሉዑ” ከሚያስኙት መስፈርቶች አንዱና ዋናው ደራሲው ሃሳቡን ለመግለፅ የሚጠቀመበት የቋንቋ ውበት ነው…” ከሚል እና ስለቋንቋ ውበት ከሚጨነቅ ሰው “…በዚህም ሳቢያ ሀረጋት ሳይወዱ በግድ መንትተው የቃላት ማጥ ፈጥረዋል…” የሚል የቋንቋ ድህነት ማንበብ ያለብን አይመስለኝም። “…ቃላት ከመጠን በላይተደራርበው ነው የምናገኙው። በዚህም ሳቢያ ሀረጋት ሳይወዱ በግድ መንትተው የቃላት ማጥ ፈጥረዋል። ይህ ደግሞ አንባቢን በተገቢው ፍጥነት ከታሪኩ ፍሰት ጋር አብሮ እንዳይወርድ ያዳልጡታል…” በሚለው ውስጥ ያለው “ማጥ”፣ በእንግሊዝኛው “ሜታፎር” የሚሉት ምስል መከሰቻ ይመስለኛል። አልታዬ “…በጉጉት እና በፍጥነት እያነበቡኩት የነበረው ታሪክ ድንገት ቃላት ስለተደጋገሙብኝ፣ ንባቤን መቀጠል አልቻልኩም”፣ ምክንያት? “…በመነተቱት…” ቃላት ምክንያት “ማጥ” አዳልጦኝ ወደቅሁ..” እያሉን ነው። “መንትተው” እና “ማጥ” በዓ/ነገሩ ውስጥ የተፈለገውን ምስል አልከሰቱም።

“…የመፅሐፉ ጠርዝ ቀኝ እጄን እንደመዘነ አጠፍቁት። በጅምር።” የሚለውንም ለመረዳት ብዙ ጊዜ ፈጅቶብኛል፣ ለዚያውም ግብቶኝ ከሆነ እድለኛ ነኝ።  ሲመስለኝ “ጣቶቼ ለንባብ ገጾቹን መግለጡን ስላልገፉበት (ቃላት በመደጋገማቸው ምክንያት?)፣ ገጾቹን የማልገልጥበት እጄ ሚዛኑን መጠበቅ ስላቃተው፣ መጽሃፉ አዘነበለብኝ…?” ማለት ይሆን? የመጽሃፉ ክብደት እጅዎ ላይ አረፈ? ወይስ የእጅዎ ክብደት መጽሃፍዎ ላይ?  አልታዬ እባክዎ ይንገሩን፤ በግራ እጅዎ ነው ወይስ በቀኝ እጅዎ ገጹን እየገለጡት የነበረው? በአውራ ጣትዎ ነበር? ወይስ በቀለበት ጣትዎ?… ተሆነ አይቀር ይንገሩን እንጂ!… ይኼን ያህል “መራቀቅ” ያስፈልግ ነበር? እውነት ለመናገር ቋንቋ የሞተበት ዓ/ነገር ነው።

አልታዪ ደጋግመው በትምህርተ ጥቅስ ውስጥ አስገብተው “ሃያሲው” እያሉ የሚገልጿቸው ዶ/ር ፍቃዱን፣ “ሃያሲ”  የሚለው ስም አይገባህም (“ገ”ን ጠበቅ)፣ አንተ ብሎ ሃያሲ…” የሚል እንድምታ አለው። ዶ/ር ፍቃዱን በሚጽፋቸው ጽሁፎቹ አውቀዋለሁ። ደጋግሞ በሚለቃቸው ጽሁፎቹ–ስለ ስነ-ጽሁፍ፣ ኢኮኖሚ፣ ሳይንስ … ወዘተ ዘርፎች የመፈላሰፍን አስፈላጊነት ደጋግሞ ጽፎ የማነብበው ሰው ነው። ሳላነብብ ያለፍኩት የዶ/ር በፍቃዱ ጽሁፍ ያለ አይመስለኝም። ማንበብ ባህላችን ያለመሆኑ ችግር እንዳለ ሆኖ፣ ጽሁፎቹ ረጃጅም በመሆናቸው ምክንያት ብቻ ሊያነብለት የሚችለውን ሰው ብዛት የሚቀንስ የመሆኑ ጉዳይ እያሰብኩ ሁሌም የምቆጭለት ጸሃፊ ነው። ይሄ የኔ ጽሁፍ ሰሞነኛ ነው። አንዴ ካነበብህ የምትደግመው አይደለም። የዶ/ር በፍቃዱ ጽሁፎች ለብሄራዊ ልማት እና እድገት እንደ “ሪሶርስ” ሊያገለግሉ የሚችሉ የምርምር ስራዎችም ናቸው። ራዕዩ ለአገራችን ብሄራዊ ችግሮች፣ ለወደፊት እድገት እና ልማት ፈር ቀዳጆችም ጭምር ናቸው። ብዙ ጊዜ የሚያነሳቸው “ስለ ቆንጆ ቆንጆ የሆኑ ስእሎች፣ ስነ-ጽሁፎች (literary/artistic beauty” ማለቱ ነው)፣ በስነ-ጥበብ፣ ኢኮኖሚ፣ ወዘተ… ስለመፈላሰፍ… ወዘተ….” በሚሉ ስራዎቹ አውቀዋለሁ።  ስለ ደራሲው “የዘመናችን ፈላስፋነት” በትችቱ ውስጥ ጠቅሶ የጻፈው ዶ/ር ፍቃዱ፣ ያን ለማለት ሙሉ ስልጣን (authority) ያለው ሰው እንደሆነ እመሰክራለሁ። እናም “የተቆለፈበት ቁልፍ”ን ገዝቼ አነባለሁ፣ ሌሎቹንም አበረታታለሁ። አልታዬ መቼም “…እንዴ! ባላነበብከው መጽሃፍ ላይ ነው እንዴ አስተያየት የምትሰጠው …?” የሚል የሞኝ ጥያቄ እንደማያቀርቡብኝ ተስፋ አደርጋለሁ።

እውነት ለመናገር እነ “አሸናፊ ዘ-ደቡብ አ.አበባ …”ን ካነበበ አንባቢ ብዙ እንጠብቃለን። በነገራችን ላይ አልታዬ “አሸናፊ ዘ-ደቡብ አ.አበባ”ን ጨርሶ አላነበቡትም። አሸናፊ የሚታወቅበት አንዱ እና አንዱ የአጻጻፍ ስልቱ ድግግሞሽ መጠቀሙ ነው። ይሄ የሱ፣ የራሱ ብቸኛው የአጻጻፍ ስልቱ ነው። ለምሳሌ እኔና እርስዎ “አበበ ሱቅ ውስጥ ገባና፣ በልኩ ልብስ ካስለካ በኋላ፣ ገንዘቡን ከፍሎ ወጣ…” ብለን የምንጽፈውን፣ አሸናፊ ዘ-ደቡብ አ.አ ቢያገኘው “… አበበ ሱቅ ግብቶ፣ በልኩ አስለክቶ፣ ገንዘቡን አስልቶ፣ ለካሼሪዋ ሰጥቶ፣ ከሱቅ ወጥቶ….” ብሎ ይጽፈው ይመስለኛል። የአሸናፊ ዘ-ደቡብ ዘዬ የቃል “Rhythmic Repetition” ሲሆን፣ የደራሲ ምህረት ደበበ ደግሞ በቃላት ድግግሞሽ “word Repetition” የሚገለጽ የአጻጻፍ ዘዬ መሆኑ ነው–“Repetition is a powerful force in fiction”

አልታዬ ሆይ! እነ “አሸናፊ ዘ-ደቡብ አ.አበባ፣ ዳግላስ፣ ወዘተ…”ን መጥቀስ ብቻውን አንባቢም ሃያሲም ቢያስመስልዎት እንጂ፣ አንባቢም ሃያሲም ሊያደርግዎት አልቻለም። ከቻሉ፣ አንብበው፣ ስለሚጽፉበት ጉዳይ አውቀው እና አስተውለው ቁብ ያለው ጽሁፍ ይጻፉልን፣ ካልሆነ ግን “…ድር ያደራበት ብዕርዎን…” እባክዎ ወደ ሰገባው ይመልሱት።

መዝገቡ ሊበን፣ ከሜነሶታ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

ለአዲስ አበባ መጤ ኦሮሞዎች ናቸው – ሰርጸ ደስታ

$
0
0
ፀጋዬ አራርሳ

ፀጋዬ አራርሳ

ሰሞኑን አንድ ዶ/ር ጸጋዬ አራርሳ የተባሉ ግለሰብ በፎረም 65 ላይ አዲስ አበባን አስመልክቶ የተናገሩት ንግግር ብዙዎች ያደመጣችሁት መሰለኝ፡፡ እኔም ለማደመጥ መከርኩ ነው የሚባለው እንጂ አደመጥኩ ለማለት ይቸግራኛል፡፡ ምክነያቱም ግለሰቡ ሲያወሩ አለማቋረጥ ብቻም ሳይሆን የሚያወሩት ሁሉ ምሁር ነኝ ከሚል ሰው እጅግ ስለከበደኝ ነው፡፡ ጸጋዬ በብዙ ነገር ጥላቻ ያመረቀዘ የሚመስል ንግግር ከዚህም በፊት ሲናገሩ ሰምተናል፡፡ በዚህ ቃለምልልስ የሰማሁባቸውን ያህል ግን ሐበሻ ያሏቸውን ሕዝቦች እንደሚጠሉ አልገመትኩም፡፡ ግለሰቡ እንዲህ ማንነታቸው በይፋ ለሕዝብ ማሰወቃቸው እንደ ጥሮ ነገር ብቆጥረውም ለደጋፊዎቻቸውና ለራሳቸውም እጅግ አዘንኩ፡፡ የሄን ላቆየው ወደተነሳሁበት ነጥብ ልመለሰ፡፡

የኦሮሞ አክቲቪስት ነን የሚሉና የኦሮሞን ሕዝብ ማንነቱን አጥቶ የባዘነ ያደረጉት በኦሮሞ ሕዝብ የሚነግዱ የተወሰኑ ቡድን አባላት የኢትዮጵያን ታሪክ 100ዓመት ብለው ሙጭጭ የሚሉበት ምክነያት ግልጽ ነበር፡፡ ከዚህ ከዘለለ እነሱ ለተነሱበት ዓላማ የሚመች ታሪክ የለም፡፡ እና ሌላው ይቅርና የኦሮሞ ሕዝብ ከደቡብ ወደ ሰሜን የተንቀሳቀሰበትን ታሪክ እንኳን  እንዲነሳባቸው አይፈልጉም፡፡ ይህ የሆነው የዛሬ 400ዓመት ገደማ ነው፡፡ እረ እንደውም ገና 400ዓመትም አልሞላውም፡፡ ከ400ዓመት በፊት እንኳንስ አዲስ አበባ አርሲና ባሌም የሌሎች ሕዝቦች መኖሪያ ነበር፡፡ አዲስ አበባና አካባቢዋም ያኔ የሌሎች ሕዝቦች መኖሪያ ነበር፡፡ ሊሆን የሚችለው ደግሞ ጸጋዬና መሰሎቹ ሐበሻ ብለው እጅግ የሚጠሏቸ የሸዋ ነበር ሕዝቦች ጉራጌ፣አማርኛ ተናጋሪው ሸው የመሳሰሉት ናቸው፡፡ ለአዲስ አበባና አካባቢዋ መጤ ከተባለ ከሌላ ቦታ የመጣው ኦሮምኛ ተናጋሪው ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ታሪክ በውል የሚያውቀው እውነት ነው፡፡ የዛሬ 100ዓመት የነበሩ ሰዎች እኮ የዚያ ቦታ ነባር አያቶቻቸውን ያውቃሉ እኮ፡፡ ይህ ማለት ዛሬ አዲስ አበባና ዙሪያዋ የሚኖራው ኦሮምኛ ሕዝብ ነባር አደለም ለማለትመ አይቻልም፡፡ አብዛኛው ወደ ኦሮምኛ ተናጋሪነት የተቀየረ ነውና፡፡  ጥላቻ ያመረቀዘ ልብ ሕሊና አይገዛውምና ማንም የፈለገውን ቢል እውነት ከእውነትነቷ ሌላ ነገር የላትም፡፡  ለመሆኑ ግን እኖርበታለሁ በሙሉት አገር ጸጋዬ ስለአቦርጅናሎች ምን ያስባሉ;

ሌላው ተናጋሪው ጸጋዬ ሐበሻ የሚባለውን ሕዝብ ምን ያህክል እንሚጠሊት ነበር የራሳቸው አንደበት የጭንቅላታቸውን ማንነት ያሳበቀባቸው፡፡ የሐበሻ ጉዳይ ከተነሳ ደግሞ ኦሮሞም ሐበሻ እንደሆነ እኔ አሳምሬ አውቃለሁ፡፡ ሐበሻ በደም የሚነበብ ነገድ እንጂ ቋንቋም ባሕልም አደለም፡፡ መላዋ ኢትዮጵያ ደግሞ የሐበሻ ምድር ነች፡፡ ሐበሾች ከሌሎች ሕዝቦች ይለያሉ፡፡ ዘመናዊው የመለዘር ጥናት እንደሚያሳየን ሐበሻ በውል የራሱ የሆኑ ሁለት ነገዶች እነዳሉት  እናያለን፡፡ አንዱ አሁን በኢትዮጵያ ምድር የሚኖረው አሪ የተባለው ሕዝብ ሲሆን ሌላው በመቀላቀል ሊሆን ይችላል በሁሉም ጎልቶ የሚታይ ግን ብቻውን የማይታይ ኬንያ ውስጥ ካሉት ማሳዮች ጋር የምንጋራው አንድ ነገድ ነው፡፡ እነዚህ ሁለት ነገዶች ኢትዮጵያዊ መሠረት የላቸው ሆኖ ሐበሻ በተጨማሪ ከመካከኛው ምስራቅ አገራት ከሚኖሩ ላቫንት ከተባሉት ጋር ከ40-50 የሚሆንውን ደሙን ይጋራል፡፡ ሐበሻ የሚባለው ሕዝብ ከመሠረቱ ድብልቅ ማለት ነው፡፡ በእርግጥም ይህን ማንነቱን ዛሬ ሳይንስ በማያሻማ ሁኔታ የሳየዋል፡፡ ይህ ነው የሐበሻ ማንነት፡፡ ከዛ በተረፈ ሐበሻ ተብለው የሚታወቁት አገራት ሰሜን ሱዳን፣የመን፣ ሶማሊያ፣ ጂቡቲና፣ ኤርትራ ውስጥ የሚኖሩትን ሕዝቦች ሑሉ ነው፡፡ ለእነዚህ ሕዝቦች ሁሉ መሠረታዊ አባት ተብለው የሚታመኑ ደግሞ ኢትዮጵያ የምትባለው ምድር ይኖሩ የነበሩ ናቸው፡፡ አሪ አንዱ መሆኑ ተረጋግጧል ሌላው ስለተደባለቀ በትክክል እስካሁን ባይታወቀውም ወደፊት ተካተው በሚጠኑ ሕዝቦች ሊታወቅ ይችላል፡፡ እነዚህ አባቶች ከሌሎች አፍሪካውያንም ፍጹም ልዩ የዘር ሀረግ ያላቸው ናቸው፡፡  ጋዬ ሐበሻ እንዳልሆኑ ማረጋገጫ ሊኖራቸው ይችላል፡፡ ያ ከሆነ ደግሞ በማያገባቸው ሕዝብና አገር ላይ ሊውም በጥላቻ የመናገር መብት ሊኖራቸው አይችልም፡፡ እናቴ ኦሮሞ አደሉም ይላሉ ደግሞ እዛው፡፡ እኔም ያገባሁት ኦሮሞ ካልሆነች ሴት ነው ይላሉ፡፡ ይህን ስሰማ አስደንጋጭ ነው የሆነብኝ ጭራሽ፡፡ ለጸጋዬ ከኦሮሞ ሌላ ሕዝብ አይመቻቸውም፡፡ እናቱን ወይም አባቱን የሚጠላ ደግሞ ….   ጸጋዬ ጥላቻንና ነገርን በማንበብ ጊዜ ከሚያጠፉ ጥቂት ስለ ማንነት ቢያነቡ መልካም በሆነላቸው፡፡ ከዚህ በፊት የሚከተለውን የሐበሻን ማንነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳየውን የዘመናችን ሳይንስ የጥናት ውጤት እንዲያነቡ ጋብዤያቸው ነበር፡፡ ያኔም ኢትዮጵያዊ የሚባል ማንነት የለም ስላሉ ነው፡፡ በቅርብም ለብዙ ሰዎች የሄንኑ ጋብዤ ነበር፡፡ የፈረንጅ ሥምና የኢንጊሊዘኛ ጀርገን ቃላት  ምሁር ከመምሰል ተጨባጭ እውነትንና ጥበብን ቢጋፈጧት እላለሁ፡፡ በድጋሜ ሊኒኩ ይሄውልዎ ያንብቡት፡፡ በዛውም ብዙ ነገር ያውቁበታል፡፡ http://www.cell.com/ajhg/pdf/S0002-9297(12)00271-6.pdf

ሌላው የጸጋዬና መሰል ቡድናቸው ከሚጠላው አንዱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነትን ነው፡፡ ታሪክ ይህች የዚች ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ከማንም በፊት ቅድሚያ በዚያች አገር እንደነበራቸው ሊክደው አይችልም፡፡ ዛሬ ጸጋዬ ሌሎችን መጤ በሚሉበት አካባቢና ዙሪያ ያሉ የኦርቶዶክስ ቤትክርስቲያናት እኮ በሺዎች በሚቆጠሩ ዓመታት በእነዛ ቦታዎች ነበሩ፡፡ እንደው ለምልክት የዙቋላ አቦንና የአዳዲ ማሪያምን ማሰብ በቂ ነው፡፡ እነ ወንጪና የዝዋይ ሐይቆችስ ዛሬም ድረስ ምን እየተናገሩ ነው;

ሌላው ስለአዲስ አበባ ሁሉንም ነገር የሚያውቁት ሆነው ተናግረዋል፡፡ እንደውም ስትመሠረት ጀምሮ የነበሩ ያህል ነበር የሚያወሩት፡፡ አባቴ እጄን እየጎተተ አሳይቶኛል ይላሉ፡፡ ያ መብታቸው ነው፡፡ ለሚኒሊክ ያላቸውን ጥላቻ የሚገልጹበት ቢያጡ የሚኒሊክን ቤተመንግስት ምሽግ እንጂ ቤተመንግስት አይመስልም ይላሉ፡፡ እንደ አንድ ምሁር ይቅርና አንድ ራሱን እንዳወቀ ሰው ጥሩ አደለም፡፡ ጥሩ ያልሆነው ደግሞ ለአደማጭ ብቻ ሳይሆን ለተናጋሪው ነው፡፡ እኔ ዋናውን ቤተመንግስተ አላውቀውም፡፡ ብዙ ሕዝብ ሟቹ ጠ/ሚኒስቴር በሞቱ ጊዜ እድሉን አግኝቶ ገብቶ ነበር፡፡ እኔ ለቅሶ ስላልሄድሁ አላየሁትም፡፡ የሚኒሊክን ቤተመግስት ግን ተጋብዤ ገብቼ ለማየት እድሉ ገጥሞኛል፡፡ ቤተመንግስቱ ውስጡ ከማማሩም በላይ የተሠራበት ቦታ ጸጋዬ እንዳሉት ለምሽግነት ሳይሆን ለመዝናኛነት ታስቦ ነው የሚመስለው፡፡ ተስፋዬ ወታደር ስላልሆኑ ምሽግ እንዴት ያለ ቦታ እንደሚሰራ ባይገባቸው አይደንቅም፡፡ ቤተመንግስቱ ግን ታስቦ የተሠራው የፍል ውሃን ለመጠቀም ነው፡፡ አካባቢውም በወቅቱ ጫካ እንጂ ሰውም ያለበት አልመሰለኝም፡፡ እኔ ጸጋዬና መሠሎቻቸው እጅግ የሚጠሉት ታሪክ ስለሆነ የፈለጉትን ይበሉ እንጂ እውነታው ይሄ ነው፡፡ አሁን ላይ እንኳን ብዙዎች የሚያደንቁት የሚኒሊክን ነው እንጂ ዋናውን ቤተመንግስት አደለም፡፡ እኔ ሁለቱንም ባለማየቴ አላወዳድርኩም፡፡

ሌላው ያሳዘነኝ የጋዘጠኛው አጠያየቅ ነው፡፡ ይሄ ለነገሩ የብዙ ጋዜጠኞች ችግር ነው፡፡ አንድን ጉዳይ አንስተው ለማወያየት ሲሞክሩ ትንሽ እንኳን ዝግጅት አያደርጉም፡፡ ሲሆን ሲሆን ጠለቅ ያለ እውቀት በኖራቸው፡፡ ብዙዎች በዛ ደረጃ አደሉም፡፡ ጸጋዬን ያናገረው ጋዜጠኛም ያየሁበት በሚጠይቀው ጉዳይ ጠለቅ ያለ ዕውቀት እንደሌለው ነው፡፡ ከዚህ ሌላ አብዛኞቹ ጋዜጠኞች ተጠያቂውን ላለማስቀየም ይሁን ሌላ ባይገባኝም ተጠያቂው ተሳስቶም ይሁን አውቆ የተሳሳተ ነገር ሲናገር አያርሙም፡፡ ለሁሉም የታዋቂውን የኤስቢኤስ ጋዜጠኛ ካሳሁን ሰቦቃን አጠያየቅ ቢያደምጡ እላለሁ፡፡ ካሳሁን በሚጠይቃቸው ጉዳዮች ካለው የጠለቀ ግንዛቤ ባሻገር ተጠያቂዎች መስመር ሲስቱ አጣርቶ ይጠይቃቸዋል ሆን ብለውም ከሆነ ሕዝብ ይሄንኑ ማንነታቸውን ያውቅ ዘንድ ከተጠያቂው አንደበት ራሱ ለሕዝብ ያስነብባቸዋል፡፡ ጸጋዬንም ማንነታቸውን ለሕዝብ በይፋ ያጋለጠው ይሄው ጋዜጠኛ እንደሆነ እናስታውሳለን፡፡ ከዚያ በፊት ጸጋዬ ምሁር በሚል የኢትዮጵያ ጉዳይ በተነሳበት ሁሉ ዋና ተናጋሪ እንግዳ ሆነው በየሚዲያው ይቀርቡ እንደነበር አንዘነጋም፡፡ በኢትዮጵያዊነት የማያምን ግለሰብ ዋና የኢትዮጵያ ጉዳይ ተንታኝና መፍትሔ ሰጭ ሲሆን ተመልከቱ፡፡

ሌላው ጋዜጠኞች ነን የምትሉ ቢቻል በአንድ ላይ ካልሆነ ደግሞ በተለያየ ጊዜም ቢሆን የተለያየ አመለካከት ያላቸውን ሰዎች ማናገርን ለመዱ፡፡ ይሄንንም ካሳሁንን አብነት አድርጉት፡፡

ሌላው በተለይ የኦሮሞ ሕዝብ እነዚህን አክቲቪስት ነን እያሉ ከማንነቱ ባዶ እያደረጉት ያሉት የሕዝብና የአገር ጠላት ሆነው የተነሱትን ሊዋጋቸው ይገባል ባይ ነኝ፡፡ እነዚህ ቡድኖች በተለይ የኦሮሞን ሕዝብ ከኢትዮጵያዊነት ተሳትፎው ባዶ እያደረጉት ብቻም ሳይሆን ከአጎራባቾቹ ሁሉ ጠላት ሆኖ እንዲታይ እያደረጉት ነው፡፡ ቡድኖቹ በኦሮሞ ሕዝብ የሚነግዱ የኦሮሞን ሕዝብ እንወክላለን በሚል ጥላቻን በሕዝቦች መካከል ተፈጥሮ ሕዝቡ እርስ በእርሱ ሲባላ ማየትን የሚናፍቁ ናቸው፡፡ እንደው እንበልና ዛሬ ኦሮሞ እየተባለ የሚጠራው ሕዝብ የሚኖረበት ቦታ ሁሉ ይዞ ለብጫው ቢገነጠል በማግስቱ ምን እንደሚመስል አስቡት፡፡ በዚህ ላይ እነዚህ ጠላቶቹ ገዥ ቢሆኑ፡፡ ዛሬ የምናያት ሱማሌ በአንጻሩ ያኔ አሁን ያለችበት ሁኔታ ሰላም የሰፈነባት ያስብላታል፡፡  ወንጀልን በሕዝብ ሥም በይፋ እየተገበሩም ነው፡፡ በቅርቡ በኢሳት ቲቪ ቀርበው የተናገሩትን ፕ/ር ላሬቦን የኦሮሞን ሕዝብ ሰድበሀል በሚል ዘመቻ ከፍተው ሰንብተው ነበር፡፡ ፕ/ሩ የተናገሩት የዚያን ያህል ባልተጋነንም ነበር፡፡ ችግሩ እነዚህ ቡድኖች በአገኙት አጋጣሚ ጥላቻንና በቀለኝነትን ስለሚያስቡ እንጂ፡፡ ከዚህ በፊትም የጀርመን ድምጽ ጋዜጠኛውን ሊውም ምሁራኖችን ስለኦሮሞ ሕዝብ እንዲናገሩ ባወያየ ሁከት መፍጠራቸው አይዘነጋም፡፡ በቃ እነሱ ኦሮሞን ወክለው የትኛውንም ወንጀል ሳይቀር መብት ያላቸው ነው የሚመስላቸው፡፡ አንዳንዶቹ በሚኖሩበት አገር ወንጀል ሊሆን የሚችል ንግግርን መናገራቸውን አንዘነጋም፡፡ የሰውን አንገት በሚጫ እቀጥፋለሁ እያለ የሚናገር ግለሰብ ሥርዓት በአለበት አገር የሚጠይቀው ስላለኖረ እንጂ ይልቅ ከሥራ አደለም ወይህኒ ሊያሶርድ የሚችል ምን አልባትም በጽንፈኛ አሸባሪነት በተጠየቀ፡፡ ዲያስፖራው ከነፈሰው ጋር እየነፈሰ ከሕዝብና አገር ጠላቶች ጋር እየተንጋጋ ብዙ ጊዜ በድሎናል፡፡ ከዚህ በኋላ ዕድል አንሰጣቸውም፡፡ እናውቃለን የሚሉትን ታሪክ እንዲናገሩ ሲጋበዙ በየሚዲያው ምሁር ሆነው የምናያቸው በጥላቻና በበቀል ነው፡፡  ሕዝብ ሁሉ ግልጽ እንዲሆንለት የምንፈልገው ይሄ ቡድን ልዩ ሴራ የየዘ አይሲስን ወክሎ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀስ አካል በመሪ ተዋናይነት የሚመራው ቡድን ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የኦሮሞን ሕዝብ እንደመሣሪያ ሊጠቀምበት ነው የፈለገው፡፡ ዙሩን ከአከረሩት ማክረሩ ለማን እንደሚጠብቅበት ቆይተን እናየዋለን፡፡ ይህ ቡድን ለኦሮሞ ሕዝብ በእውነት የሚታገሉ ቡድኖች እንዳይመጡ ተጠንቅቆ ከሚሰሩት ነው፡፡ የእነመረራና በቀለ ቡድን ለዚህ ቡድን እጅግ ያስፈራዋል፡፡ አሁን ላይም ያለብት ትልቁ ችግር ሕዝብ ፊቱን ወድ እውነተኛ ታጋዮቹተ መመለሱ ነው፡፡

 

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይጠብቅ!

 

አሜን!

ሰርጸ ደስታ

የማለዳ ወግ…ኢትዮ የሞት ፍርደኞች ” ነጻ ” ተብለዋል ፣ ይፈታሉም!- ነቢዩ ሲራክ

$
0
0

• የጅዳ ቆንስል ጉዳዩን ተከታትሎታል ፣ ይለቀቁ ዘንድ ጠይቋል
* ጉዳዩን በቅርብ የተከታተሉት ዲፕሎማት ይመሰገናሉ
* የጅዳ ቆንሰልም ድጋፍ እየሰጠ ነው ፣ ይበረታታል
የሁሴንና ጓደኞቹ የግድያ ወንጀል ጅዳ ፈይሰልያ በተባለ አካባቢ ሲከወን ከሀበሾች አልፎ ያንድ ሰሞን የሳውዲ መገናኛ ብዙሃን መነጋገሪያ ርዕስ ነበር ። ጉዳዩ ሲቦካ ፣ ሀበሾች ” ሳውዲ ወጣት ገደሉ! ” በሚል ከተናፈሰው መረጃ ጀርባ የነበረው እውነት ግን ሌላ ነበር ። ከስራ መጥተው በቤታቸው ውስጥ የነበሩ የሁሴን ቤተሰቦችን ለመዝረፍ የመጡ ሳውዲ ጎረምሳዎች ” ሸባቦች ” ከዝርፊያ አልፈው ሴቶችን እንድፈር ሲሉ አንባጓሮ ተነሳ። ወንዶችን ሴቶችን ለየብቻ ክፍል ውስጥ ዘግተው ስለት ይዘው ከመዝረፍ ወደ ሴቶችን መድፈር ሲያመሩ ነገር ተበላሸ ።
ሟች በያዘው ስለት እያስፈራራ እንደዘረፈ የሁሴንን ሚስት ሊደፍር ሲሞክር ሚስቱ ” ድረስልኝ ” ብላው ሁሴን ደረሰላት ፣ በጩቤ አስፈራርቶ ሊደፍር ይታገል የነበረውን ሳውዲ ጎረምሳ በያዘው ስለት ወግቶ ጣለው ። እናም ሁሴንና ጓደኞቹ ታፍሰው ዘብጥያ ወረዱ ።
ለአመታት በተደረገው ማጣራት ሁሴን በዋና ገዳይነት ፣ ወንድሙና ጓደኞቹ በተባባሪነት ወንጀል በሞት ፍርደኞች መካከል ሆነው ፍርዳቸውን ሲከታተሉ ከርመው ነበር። ከወራት በፊት ፍ/ቤቱ ባሳለፈው ውሳኔ እነ ሁሴን ሚስቱን ከመደፈር ለመከላከል ሲል በእጁ የሰው ህይዎት የጠፋበት ሁሴንና ጓደኞቹ በነጻ እንዲለቀቁ ወስኗል ። ሁሴንና ጓደኞቹ በጅዳ ቆንስል ጉዳያቸውን አስረጅ ጠበቃ አቆሞላቸው ክርክር ባይደረግላቸውም ከአንድ አመት ወዲህ ዲፕሎማት አቶ ያለለት በተደጋጋሚ ወደ ፍርድ ቤቱ በመሄድ ያደረጉትን ክትትል ሳላደንቅና ሳላመሰግን አላልፍም ።
” ነጻ ” ከተባሉ ወዲህ የጅዳ ቆንስል ሁሴንና ጓደኞቹን ዋስ በመሆን ካሉበት የብሪማን እስር ቤት ለማስወጣት ፍላጎቱን ለፍርድ ቤት ማቅረቡን ሰምቻለሁ ! ይህ ከዚህ ቀደም ያልነበረ ፣ ከአመት ወዲህ ያየነው ሊበረታታ የሚገባ ድጋፍ ነው ። እዚህ ላይ በተመሳሳይ ሁኔታ በሞት ፍርድ ተራ የሚጠብቁ ዜጎቻችን ሞልተው ተርፈዋል ። ተመሳሳይ ብቻ ሳይሆን ጠበቃ እስከመቅጠር የደረሰ ድጋፍ ሊደረግላቸው ይግባል ። ህጉ ገደለ ተብሎ ብቻ ይገደል እንደማይል የእነሁሴን ጉዳይ አስረጅ ይመስለኛል ። በተለያየ እጅግ ፈታኝ በሆነ የአእምሮ ፈተናና ጭርቀት ውስጥ ወድቀው ግድያ የፈጸሙ ዜጎች ቢያንስ ሊደመጡ ይገባል ። ፍርዱን ከግምት ውስጥ በማስገባት ወደ ወህኒ ጎራ በማለት ዜጎችን በማወያየትና በማማከር ቆንስልና የኢንባሲ መ/ቤቶች አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ለዜጎች ድጋፍ ያድርጉ ዘንድ ዛሬም እንማጸናለን ! ከታሳሪዎች ባለፈ በተለያየ ምክንያት ጉዳት ደርሶባቸውና ተሰናክለው በየሆስፒታሉ የሚገኙ ዜጎች ዛሬም በለቅሶ የመንግሰት ተወካዮችን ድጋፍ እየተማጸኑ ይገኛሉ ፣ እኒህም ዜጎች ናቸውና በዋናነት የመንግስት ተወካዮች መብታቸውን ከማስከበር ጀምሮ ወደ ሀገር ቤት እስከመላክ የደረሰ ድጋፍ በማድረግ ሊታደጓቸው ይገባል ! እኒህም ድምጻቸውን ሰሚ ያጡ ዜጎች ናቸውና !
ከሁሴን ጋር ያደረግኩት ቃለ ምልልስ እንደ አስፈላጊነቱ አቀርበዋለሁ!
ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ
የካቲት 1 ቀን 2009 ዓም

እጂግ አሰሰዛኝ ዜና (ደብረታቦር) …. በእነ ሐብታሙ አያሌው መዝገብ ተከሳሽ በልብ ድካም ከዚህ አለም በሞት ተለዮች

$
0
0

በእነ ሐብታሙ አያሌው መዝገብ ተከሳሽ በመሆን እጂግ አሰቃቂ ድብደባ የተፈፀመበት የመምህር ተስፋዮ ባለቤት መምህርት አገርነሽ መስፍኔ ሶስት ልጆቿን ለኢትዮጵያ ህዝብ ትታ እርሷ በልብ ድካም ከዚህ አለም በሞት ተለዮች።

የቀብር ስነስርአቷም ትናንት ደብረታቦር ከተማ ተፈጽሟል።
ባለቤቷ መምህር ተስፋዮ በማእከላዊ የተፈፀመበት ድብደባ ከፍተኛ በመሆኑ አዲስ አበባ ከዘመድ ቤት ተጠግቶ ህክምና በመከታተል ላይ ነው።
የዚህ ወንድማችን ሶስት ህጻናት ልጆቹ ሜዳ ላይ ፈሰሱ።
አገርዮ ነብስሽን በገነት ያሳርፋት

ልያ ፋንታ


ጊዜው ለትግራይ አስተማማኝ አይደለም ሲል ብአዴን አስታወቀ

$
0
0

መርጋ ደጀኔ

ብአዴን ሰሞኑን በክልሉ የተደረጉ ስብሰባዎችን በማስመለክት ባወጣው የማጠቃለያ ሪፖርት ላይ የሰላም መናጋት ለገዢው ፓርቲ አመራሮች ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ህብረተሰብ የሚተርፍ ነው። በተለይ ለትግራይ ጊዜው አስተማማኝ አይደለም ሲል ገልጿል።

የትግራይ ህዝብ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ማበር ካልቻለ በስተቀር ጊዜው አስተማማኝ አይደለም የሚለው ብአዴን የክልሉ ህዝብ በህወሃት ላይ ያለውን ጥላቻ በሪፖርቱ ላይ አካቷል።

በህዝቦች መካከል መጠራጠርን እንዲፈጠር የሚያደርጉ የጥፋት ሀይሎችን በጋራ መታገል የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው የሚለው ብአዴን የሰላም መናጋት ለገዥው ፓርቲ አመራሮች ብቻ ስጋት አይደለም የሁሉንም ህብረተሰብ የእለት ተእለት ኑሮ የሚያዛባ በፈለግነው ቦታ ተዘዋውረን ሰርተን መመለስ የማንችልበት እድል ይፈጠራል ብሎአል።

ሪፖርቱ አብዛኛው የብአዴን መካከለኛና ዝቀተኛ አመራርና አባላት በህወሃት ላይ ያላቸውን ቅሬታና ጥላቻ የሚያመልክት ነው። ከጥቂት አመራሮች በስተቀር አብዛኞቹ የብአዴን አባላት ከህወሃት ጋር ያላቸው ልዩነት እየሰፋ በመምጣቱ በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ተናቦ መስራት እየቀረ ነው።

በተለይ ከደህንነት ጋር በተያያዘ በመካከለኛና ዝቅተኛ ደረጃ የሚገኙ የብአዴን የደህንነት አባላት ከህወሃት የደህንነት አባላት የሚሰጣቸውን ትእዛዝ ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ብዙዎቹን የአማራ ክልል የደህንነት ስራዎች ህወሃቶች ተረክበው እየሰሩ ነው። ምንጮች እንደሚሉት በአሁኑ ሰአት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሰበብ ህወሃት የክልሉን የደህንነት ክፍል ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሮታል።

ስርዓቱን ለማገልገል እና ለመታዘዝ ፈቃደኛ አይደሉም የተባሉ ከባህርዳር 11 ከጎንደር 13 ከደብረማርቆስ 9 የደህንነት አባላት ከስራቸው የታገዱ ሲሆን፣ በቦታቸው 39 የህወሃት አባላት ሃላፊነቱን ወስደው የክትትል ስራ እየሰሩ ነው።

የአማራ ተወላጅ የደህንነት አባላት ለመታገዳቸው ምክንያት ሆኖ የቀረበባቸው በክልሉ ስላለው የጸጥታ ሁኔታ በየጊዜው ሪፖርት አያቀርቡም በክልሉ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን እያወቁ እንዳላወቁ ሆነው ያልፋሉ እንዲሁም የሚሰጣቸውን የክትትል ስራ በአግባቡ መስራት አይችሉም የሚል ነው።

ከፌደራል የተላኩ የኮማንድ ፖስት አባላት ሰሞኑን ባደረጉት ግምገማ በክልሉ ያለው የጸጥታ ሁኔታ አስተማማኝ ባለመሆኑ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አይነሳ የሚል ሃሳብ ማቅረባቸውን ኢሳት መዘገቡ ይታወቃል።

 

ቪዲዮ: ፕሮፈሰር ሀይሌ ላሬቦ በኢትዮጵያ ታሪክ እና በኦሮሞ አክቲቪስት ነን ከሚሉ ወገኖች እየቀረበባቸው ላለው ትችት ከመሬት ኢትዮ እስራኤል ድም ጽ ጋር በአደረጉት

$
0
0

Meret Ethio_Irael Radio

ፕሮፈሰር ሀይሌ ላሬቦ በኢትዮጵያ ታሪክ እና በኦሮሞ አክቲቪስት ነን ከሚሉ ወገኖች እየቀረበባቸው ላለው ትችት ከመሬት ኢትዮ እስራኤል ድም ጽ ጋር በአደረጉት

 

የብዙኃን መገናኛዎቻችን የመዝናኛ ዝግጅቶች ጠንቀኝነት! – ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

$
0
0
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ይሄንን ጽሑፍ ለመጻፍ ያነሣሣኝ ጉዳይ እንዲያው ደበር ሲለኝ ቅድም (ሐሙስ ከሰዓት በኋላ 08:20, 2009ዓ.ም.) የሸገር ሬዲዮን (ነጋሪተ ወግ) ስከፍት ምን እሰማላቹሀለሁ! ሰዓቱ የጋዜጠኛና የማስታወቂያ ባለሞያ አንዷለም ተስፋዬ የዝግጅት ሰዓት ኖሮ “አንድ ፈላስፋ ነው!” አለና በመቀጠል “”ስሕተት፣ ወንጀል፣ ኃጢአት የሚባሉ ነገሮችን ዘርዝሮ በመጻፍ “ፈጽሜያቸዋለሁ!” በሚላቸው ላይ ምልክት ምልክት አደረገና “መንግሥት ይሄንን ማድረጌን ቢያውቅ ምን ያህል እስራት ይቀጣኝ ነበር?” ብሎ ሲያሰላው አራት ዓመታት ያህል እስራት እንደሚያስቀጣው አየ፡፡ በተመሳሳይ የሃይማኖት መጽሐፍ ወይም መጽሐፍ ቅዱስ ገለጠና ሲመለከት የሠራው ኃጢአት ለዘለዓለሙ ገሃነመ እሳት ውስጥ ሲቃጠል እንዲኖር የሚያደርግ መሆኑን ያነባል፡፡ ከዛ ሰውየው “እንዴት?” ብሎ ይጠይቃል፡፡ መንግሥት እንኳን ከአራት ዓመታት በላይ ሊቀጣኝ በማይችለው፣ እንደዛሬው ብዙ ሳልበስል ያውም አንዳንዱን ኃጢአት መሆኑን እንኳ ሳላውቅ ባደረኩት ነገር እንዴት እግዚአብሔር መጨረሻ በሌለው ቅጣት ለዘለዓለሙ ሊቀጣኝ ይችላል? እንዴት ዓይነት ጭካኔና ኢፍትሐዊነት ነው? በማለት ጠየቀ!”” አለና ጋዜጠኛው “ሁላችንም ይሄንን ጥያቄ መጠየቅ ስላለብን ነው ወደናንተ ያመጣሁት! እስኪ እናንተ ምን ይሰማቹሀል? ተወያዩበት! የዘለዓለም ቅጣት! ነገሩ አያበሳጭም? ምን ዓይነት ፍርድ ነው? የሰው ልጅ የማይቻል ፍጡር ነውና ገሃነም ውስጥ ቆልፌበት ልረፍ! ነው እንዴ ነገሩ?” አለና ዘፈን አስከተለ፡፡

እንዲህና ሌላም ዓይነት ስሕተቶች በተለይም ደግሞ ለብዙኃን መገናኛ ባለው ከፍተኛ ግምትና ክብር በብዙኃን መገናኛ የሚነገር ነገር ሁሉ እውነት በሚመስለው እንደኛ ላለ ማኅበረሰብ ሊያስከትል የሚችለው አሉታዊ ውጤት ሊገመት ከሚችለው በላይ ነው፡፡

ይሄ ጋዜጠኛ የተናገረው ነገር ሁሉ ሐሰትና ከሃይማኖታዊ አስተምህሮ ጋር ሙሉ ለሙሉ የሚቃረን በመሆኑ “እንዴት ሚሊዮኖች (አእላፋት) በሚያዳምጡት ሬዲዮ (ነጋሪተ ወግ) ላይ ምንም የማታውቀውንና ትክክለኛ ያልሆነን የተሳሳተ መረጃ ሚዛናዊነትን ሳትጠብቅ አፍህ እንዳመጣልህ ትረጫለህ? ያዳመጠህን ሁሉ እያሳሳትክ እንደሆነ ይገባሀል ወይ?” ብየ የተሳሳተውንና ትክክለኛው ምን እንደሆነ፣ በማይጠበቅ ደረጃ አለመብሰሉንም ልነግረው የጣቢያውን የስቱዲዮ (የመከወኛ ክፍል) ስልክ (መናግር) ብቀጠቅጥ ብቀጠቅጥ ይጠራል የሚያነሣው ግን የለም፡፡ ከዚያ “ትክክለኛውን ነገር ለምን የተሳሳተ፣ ያልበሰለና ሰይጣናዊ መልዕክት ለተረጨበት ሕዝብ በማኅበራዊው የብዙኃን መገናኛ አላደርሰውም?” ብየ አሰብኩና ወደእናንተ አመጣሁት፡፡

የብዙኃን መገናኛው እንዴት መጫወቻ መቀለጃ ሆኗል መሰላቹህ! በተለይማ የባጡ የቆጡ የሚቀባጠርባቸው የመዝናኛ ዝግጅቶች! (አብዛኞቹ ማለቴ ነው) እነሱን “ምን ተሳሳቱ?” ብሎ ከመጠየቅ “ያልተሳሳቱት ምንድን ነው?” ብሎ መጠየቁ ይቀላል፡፡

የተቀመጡበት ወንበር ብስለት፣ እጅግ ኃላፊነትና ጥንቃቄ የሚጠይቅ መሆኑን ጨርሶ የማይረዱ (ሳይነገራቸው ቀርቶ አይመስለኝም የሚገባቸው ስላልሆኑ እንጅ) ፣ እዚያ ላይ ቁጭ ብለው የሚናገሩት እያንዳንዷ ነገር በባሕላችን በወጋችን በማንነታችን አዎንታዊ በሆኑ የወል አስተሳሰባችን ላይ ሁሉ አሉታዊ ውጤት የማያስከትል ስለመሆኑ መርምረው አረጋግጠው የመናገር ብቃት የሌላቸው፣ ምንም ስለ ማያውቁት ነገር ተጠያቂነት በሌለበት ስሜት እንዳሻቸው የሚቀባጥሩ፣ የሚያቀርቡት ነገር በባሕል በወግ በማንነት በታሪክ ወዘተረፈ. ላይ የቱንም ያህል አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያስከትል ቢሆንም እንኳ ገንዘብ እስካስገኘላቸው ጊዜ ድረስ ምንም ከማድረግ የማይመለሱ ወይም ከገንዘብ በስተቀር ምንም የማይታያቸው (Business oriented) ፣ በዜግነታቸው ሀገሪቱ ከእነሱ የምትጠብቅባቸው ኃላፊነትና ግዴታ እንዳለ ከነመኖሩ እንኳን ጨርሶ የማይረዱ ወይም መወጣት በፍጹም የማይፈልጉ ወዘተረፈ. ናቸው፡፡
ይሄ እንግዲህ እንደ ወያኔ ዓይነት አገዛዝ ባለበት ሀገር የሚጠበቅ አደጋ ነው፡፡ ምክንያቱም ከላይ የጠቀስናቸው እሴቶች የሚሰሟቸውን የሚጠብቁትንና ብቃት ያላቸውን ዜጎች ሥርዓቱ (The system) ወደጎን ስለሚገፋቸው፣ ስለማይፈልጋቸውና ቦታ ስለማይሰጣቸው ለእነኝህ እሴቶቻችን ዴንታ የሌላቸው፣ ሁለነገራቸውን ገንዘብ የሚገዛቸው ኅሊና ቢስ የመንደር አፈጮሌዎች መፈንጫ ለመሆን እንገደዳለን ማለት ነው፡፡
በዚህ ምክንያት ታዲያ በሀገርና ሕዝብ ላይ የሚደርሰው ጉዳትና ኪሳራ እንዲህ የዋዛ እንዳይመስላቹህ፡፡ ከሁለት ዐሥርተ ዓመታት ወዲህ በኅብረተሰባችን ላይ በሰፊው ለተስፋፋው ኢግብረገባዊነት፣ የሞራል (የቅስም) ዝቅጠትና ሌሎች አሉታዊ ለውጦች፣ የማንነት ቀውስና ኪሳራዎች ሁሉ ምክንያቱ ሌላ ምንም ሳይሆን ይህ ችግር ነው፡፡
ነገር ለማሳጠር ያህል ጋዜጠኛ አንዷለም በሰይጣን እየተጋለበ የረጨውን የተሳሳተ፣ አሰናካይ፣ አሳሳች መልዕክት አርሜ ጽሑፌን ልቋጭ፡፡ እግዚአብሔር የሰይጣን ደቀመዝሙሩ ጋዜጠኛ አንዱዓለም እንዳለው በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ለተሠራ ትንንሽ ኃጢአት “ይሄን ስላደረጋቹህ!” ብሎ ዘለዓለማዊ ቅጣት ወይም ገሃነም ውስጥ የሚጥል ጨካኝና አረመኔ አምላክ ሳይሆን የፈጸማቹህት ኃጢአት የቱንም ያህል ከባባድና እጅግ በርካታ እንኳን ቢሆን የሚምርና ዘለዓለማዊ መንግሥቱን የሚያወርስ፤ ለደግነቱ፣ ለቅንነቱ ወደር የሌለው ቸር አምላክ ነው፡፡ ከኛ የሚጠበቀው ንስሐ መግባት ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሔር ማንንም “ለምን ኃጢአት ሠራህ?” ብሎ አይጠይቅም! የሰው ልጅን ደካማነትና የባለጋራችንን ብርታት ያውቃልና፣ ኃጢአት የሌለበት ሰው የለምና፡፡ እግዚአብሔር የሚጠይቀው ጥያቄ “ለምን ንስሐ አልገባህም?” ብሎ ነው፡፡ የሠራነው ኃጢአት የቱንም ያህል ከባድና ዘግናኝ ይሁን፤ ምንም ያህል ጊዜ ይደጋገም ይብዛ ንስሐ በመግባት ከተጠያቂነት ከተወቃሽ ተከሳሽነት ነጻና ጻድቅ መሆን እንችላለን፡፡ ከዚህ በላይ ቸርነት ደግነት ቅንነት ምን አለ? ከዚህም በላይ እግዚአብሔር እኮ ለእኛ ካለው ፍቅር ብዛት የተነሣ እንደጠፋን እንደረከስን እንዳንቀር አንድያ ልጁን አምላክ እግዚአብሔር ወልድን ተለዋረደ ሞት አሳልፎ የሰጠ ወደር የሌለው ቅን፣ ደግና ቸር አምላክ ነው፡፡ እጅግ ኃጢአተኞች በደለኞች እርኩሶች የነበርነው ንስሐ በመግባት ብቻ ንጹሕና ጻድቅ መሆን ከቻልን ይሄ የሚያሳየው የእግዚአብሔርን ጨካኝነት ነው? ከኃጢአተኝነት ንስሐ በመግባት ጻድቅ መሆን እየቻልን የሠራነው ኃጢአት እንደሚያስፈርድብን ተነግሮን እያወቅን ንስሐ ባለመግባትና በኃጢአት ላይ ኃጢአት በመደራረብ ሰውን ሳናፍር፣ እግዚአብሔርን ሳንፈራ ምድሪቱን ስናጎሳቁል ቆይተን ስንሞት ቢፈረድብን ተጠያቂው ማን ነው?

ለመሆኑ እግዚአብሔር ኃጢአት የተባሉ ነገሮችን “የሚያስኮንኑ ኃጢአቶች ናቸው!” ብሎ ለምን የደነገገ ይመስላቹሀል? በእኛ ላይ ቀንበር ለመጫን ነው የሚመስላቹህ? አትሳሳቱ አይደለም! የሰው ልጆችን ኑሮ ሰላማዊ፣ አስደሳችና ጤናማ ለማድረግ ነው፡፡ የሱ ፈቃድና ፍላጎት ይሄ ቢሆንም እኛ ግን ለእኛው ጥቅም አታድርጉ ተብለን ተከልክለንም እንኳ ቃሉን ባለመስማት ወደሰው ሚስት/ባል በመሔድ ወይም በመዘሞት፣ የሰው ገንዘብን በመስረቅ፣ በመስከር፣ በመጣላት፣ በሐሰት በመመስከር፣ በመመቅኘት፣ በማሟረት፣ ጣዖት በማምለክ፣ ለአባይ ጠንቋይ ለቃልቻ በመስገድ በመገዛት፣ ነፍስ በማጥፋት፣ ሱሰኛ በመሆን የመሳሰሉትን በመፈጸም ኑሯችንን ሰላም የጠፋበት፣ የሁከትና ጎስቋላ እናደርገዋለን፡፡ ታዲያ ማን ነው ተጠቃሚው? ማንስ ነው ተጠያቂው?

እስኪ ልቡናውን ይስጠን! ለንስሐ ሞትም ያብቃን! ከንስሐ ግን ማመን ይቀድማል!!!
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
amsalugkidan@gmail.com

ፕሬዚዳንቱ ስደተኞችን አስመልክቶ የሰጡት ትዕዛዝ ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሊያመራ ይችላል ተባለ

$
0
0

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስደተኞችን አስመልክቶ የሰጡት አከራካሪ ትዕዛዝ መጻዒ ዕድል በአሁኑ ወቅት በዩናይትድ ስቴትስ የፌዴራሉ ፍርድ ቤት እጅ ውስጥ ይገኛል። በመጨረሻ ግን ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሊያመራ እንደሚችል ይገመታል።

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስደተኞችን አስመልክቶ የሰጡት አከራካሪ ትዕዛዝ መጻዒ ዕድል በአሁኑ ወቅት በዩናይትድ ስቴትስ የፌዴራሉ ፍርድ ቤት እጅ ውስጥ ይገኛል። በመጨረሻ ግን ወደ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሊያመራ እንደሚችል ይገመታል።

ይህ የስደተኞችን ወደ ዩናይትድ ስቴትስ መግባት ያቋረጠውና አብዛኞቹ ሙስሊሞች ከሚኖሩባቸው የሰባት ሃገሮች ዜጎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ በጊዜአዊ መልክ የሚያግደው የፕሬዘዳንት ትራምፕ ትዕዛዝ ባለፈው ሳምንት በአንድ የፌዴራል ዳኛ መታገዱ ይታወሳል።

ሁለቱም የሚስተር ትራምፕ ተቺዎችና ደጋፊዎች ይህን ሕጋዊ ጦርነት የሚያዩት በሕገ መንግሥቱ መሠረት ፕሬዚዳንታዊ ሥልጣናቸው የሚፈተንበት የፍትህ ዘርፉ ደግሞ ሕጉን ተመርኩዞ ፕሬዚዳንቱን የመቆጣጠር መብቱ መጠበቁ የሚታይበት ቁልፍ ነጥብ አድርገው ነው የተከራከሩት።

ለፕሬዚዳንት ትራምፕ ስደተኞች ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ለመጓዝ የሚያደርጉትን ጥረት ለማጥበቅ የሰጡት ትዛዝ የአሜሪካውያንን ደኅንነት ለማስጠበቅ በታቀደ ብቻ ነው፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

if(typeof(jQuery)==”function”){(function($){$.fn.fitVids=function(){}})(jQuery)};jwplayer(‘jwplayer-1’).setup({“file”:”http://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2017/02/dd8318c9-4139-4ef2-81d8-d800a99808c8_hq.mp3″});

ታሪክን ምርኮኛ የማድረግ ዘመቻ

$
0
0

ከሰሞኑ የፖለቲካችን የስበት ማእከል ታሪክ እና የታሪክ ባለሙያዎች ሆነዋል። ዶ/ር ሃይሌ ላሬቦ የተባሉ የታሪክ ምሁር ከኢሳት ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ በሶሻል ሚዲያው ከፍተኛ አዋራ ማስነሳቱ ሳያንስ፣ የተዳፈኑ የመሰሉ ጉዳዮችንም በመቀስቀስ ላይ ይገኛል።

በመጀመሪያ የዶክተሩን ቃለምልልስ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በጽሞና ለመከታተል ሞክሬአለሁ። በዚህም ተጠያቂውን ዶ/ር ሃይሌ ላሬቦ ከሙያም  ሆነ ስነምግባር አንጻር የበቃ ችሎታቸውን ለመታዘብ ችያለሁ። ውዝግቡ ከተቀሰቀሰም በኋላ የኦሮሞ አክቲቪስት ነን ከሚሉ ሰዎች በተሰነዘረውን ክስ ላይ ተመስርቼ ቃለ-ምልልሱን በሂሳዊ አይን ለማየት ሞክሬአሁ። ህዝብ የተሰደበበት እና ወደ አንድ ሚዛን ያጋደለ አቀራረብ ፈልጌ ማግኘት ተቸግሬአለሁ። እንዳውም ዶ/ር ሃይሌ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ አወዛጋቢ ቦታ ስለሚይዘው ግራኝ አህመድ በጎ የሆነ እይታ እንዳላቸው መታዘብ ይቻላል። ግራኝ አህመድን  በሚመለከት ያላቸው እይታ በአዲስ አበባ ዩኒቪርሲቲ የታርክ ትምህርት ክፍል እውቅ የታሪክ ተመራማሪ ከነበሩት ፕሮፌሰር መርዕድ ወልደ አረጋይ ጋር ተመሳሳይ እይታ እንዳላቸው ማወቅ ይቻላል። በዚህ መሰረት አክቲቪስቶች ነን የሚሉት ክስ መነሻ ሌላ መሆን አለበት በሚል አዲስ መላምት ጥረቴን ሌላ ምክንያት ቢኖርስ ወደሚል አቅጣጫ ለወጥሁት።

በዚህ ሂደት ካለፉት ጥቂት አመታት ወዲህ የኦሮሞ አክቲቪሰት ነን የሚሉት አክራሪ ብሄረተኞች በዶ/ር ሃይሌ ላይ  ዛቻ እና ማስፈራሪያን ጨምሮ፣ አጓጉል ስሞችን እስከ መስጠት የደረሰ ዘመቻ ውስጥ እንደነበሩ መረዳት ይቻላል። ከዛም አልፎ በተማሩበት የታሪክ ጥናት መስክ ያላቸውን ችሎታ በማጣጣል፣ የዶክትሬት ደረጃቸውን ሃሰተኝነት በመናኘት፣ ማንኛውም መድረክ እንዳይጋበዙ፣ ተደማጭነት እንዳያገኙ እንዲሁም ከሚያስተምሩበት ስራ እንዲባረሩ ያላደረጉት ጥረት የለም ማለት ይቻላል። የነፍጠኞች ተላላኪ ወኪል፣ የኦሮሞ ደመኛ ጠላት ተደርገው በአደባባይ እንዲሳሉም ተደርጎዋል። ይህ አልበቃ ብሎ በተለያዩ መድረኮች ቀርበው ጥናታዊ ጽሁፍ እንዳያቀርቡ ቅስቀሳ ሲደረግ እንደነበረ በቅርብ ግዜ የምናስታውሰው ነው። ለዚህ አንድ ምሳሌ ብንጠቅስ ባለፈው ዓመት ቪዥን ኢትዮጵያ ከኢሳት ጋር ባዘጋጁት ኮንፍረንስ ዶክተሩ እንዳይጋበዙ በአዘጋጆቹ ላይ ጫና ሲደረግ ነበር። ሌላው ዶ/ር ሃይሌን የተመለከቱ ተለያዩ መዛግብትን በድረ-ገጽ በመበተን የማስተማር ችግር እንዳለባቸው እንዳውም ዶክትርነታቸው የሃሰት እንደሆነ ሲነዛ ነበር። ጉዳዩን በቅርብ የምንከታተል ዶ/ር ሃይሌ በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ያሳተሙትን ጥናታዊ የሆነ መፅሃፍ ይፋ ሲደረግ የሚቀርብባቸው ክሶች መሰረተቢስ፣ በጥላቻ የተነሳሱ እንደሆኑ ለመታዘብ ችለናል። ይህ አልበቃ ብሎ፣ ዶክተሩ በሚያስተምሩበት ዩኒቨርሲቲ ላይ ጫና በማሳደር ከስራ እንዲባረሩ ለማድረግ ዘመቻ ተደርጎ እንደነበረ እናስታውሳለን። ሰሞኑንም ይህን አይነቱ ዘመቻ በድጋሚ ተጀምሮ ፊርማ የማሰባሰቡ ስራ እየተከናወነ ይገኛል። እዚህ ጋር ሁላችንም መጠየቅ ያለብን ጥያቄ ግን ለምን ዶክተር ሃይሌ ላሬቦ የስም ማጥፋት ዘመቻ ጥቃትና የጥላቻ ኢላማ ተደረጉ የሚለው ጥያቄ ነው።

ዶክተር ሃይሌ ላሬቦ ተመርጠው የዚህ ሁሉ የስም ማጥፋት እና ማሸማቀቅ የውርጅብኝ ዘመቻ የተከፈተባቸው በሶስት ምክንያቶች እንደሆነ ነው።

አንደኛው በዚህ ወቅት የፖለቲከኞች ቁማር መጫወቻ በመሆን እየተበላሸ ያለውን የሃገራችን ታሪክ ሳይፈሩ እውነቱን ከሃሰቱ በመለየት የመናገር ድፍረት በማሳየታቸው ሲሆን፣

ሁለተኛው የዶክተሩ የት መጣነት (የዘውግ ማንነት) ከደቡብ በመሆኑ ነው።

ሶስተኛው ምሁሩ ከዚህ ቀደም የጎሳ ፖለቲካ ዝንባሌ ባላቸው የታሪክ ጸሃፊዎች የተደረሰውን የታሪክ ልብ ወለድ እርቃኑን በማስቀረት ያሳዩት ቆራጥነት ነው።

በአሁኑ ወቅት ጎሰኞች የልብ ልብ አግኝተው ታሪካችንን በማጣመም ብቻ ሳይወሰኑ፣ ትክክለኛ የሆነው የሃገራችን ታሪክ እንዳይነገር የተለያዩ ማሸማቀቂያዎችን በመጠቀም የታሪክ ባለሙያዎች የዳር ቆመው ተመልካች የሆኑበት ሁኔታ ተፈጥሮአል። የተፈጠረውን አጋጣሚ በመጠቀም የፖለቲካ አጀንዳ ያነገቡ ግለሰቦች በታሪክ ላይ የለየለት ውንብድና በመፈጸም የተወላገደ ታሪክ ሲጻፍና ሲነገር እያየን ነው። በዚህም የተነሳ ብዙዎቹ  የታሪክ አዋቂዎች ስድብን፣ ነቀፋን በመፍራት ብሎም በፖለቲካዊ ተአርሞ (political correctness) ተሸብበው እንዳላዩ ሆነው ማለፍን በመረጡበት ወቅት ነው እንግዲህ ዶ/ር ሃይሌ ወዳደባባይ በመውጣት ሙያቸው የሚጠብቅባቸውን ሃላፊነት ለመወጣት እየሞከሩ ያሉት።

ሳይንሳዊ የጥናት ዘዴን በሚከተል አካዳሚያዊ  ምርምር ምንም ነገር ቢሆን ከመፈተሽ፣ ከመመርመር፣ ከመተችት እና  ነጻ (immune ) አይደለም። በታሪክ ጥናት ዘርፍ ውስጥም ባለሙያው የምርምር ህግን ተከትሎ፣ በአመክንዮ ላይ ተመስርቶ ማንኛውንም ነገር ማጠየቅና እውነተኝነቱን ማረጋገጥ መሰረታዊ ግዴታው ነው። ከዚህ ውጭ የታሪክ ባለሙያው በማህበራዊ መገናኛ ላይ በሚፈጠሩ የጫጫታ ማእበሎች በመርበትበት እና ሙያዊ ግዴታውን ከመወጣት ወደኋላ ማለት የለበትም።

በዚህ በኩል በዶ/ር ሃይሌ ላሬቦ ቃለመጠይቅ ላይ የተነሳውን የሰሞኑ እሰጥ-አገባ ስንመለከት፤ የታሪክን በማህበራዊ መገናኛ ዘዴ ጩህት በማንበርከክ ሃቁን ለማዳፈን የሚደረግ መውተርተር እንደሆነ መረዳት እንችላለን። በዶ/ር ሃይሌ በኩል የተያዘውም አቋም ይበል የሚያሰኝና አሁንም ሳይንሳዊ የሆነውን የታሪክ ጥናት ዘርፍ ፈለግ እስከተተለ ድረስ መቀጠል ያለበት ጥረት እንደሆነ ነው። በነገራችን ላይ በአካዳሚክ  እና  ሃሳብን በነጻነት ጸር የሆኑት፤ የዘመናችን አክራሪዎቹ ተግባት ያስገነዘበን ሌላ ነገር ቢኖር ከዚህ የበለጠ እርምጃ የመውሰድ አቅም ቢሆኖራቸው አሁን በስልጣን ላይ ካለው የህወሓት ቡድን የበለጠ ነገር ሊከሰት እንደሚችል አመላካች ነው።

ሁለተኛውና አክራሪ የኦሮሞ ብሄረተኞችን ከማስቆጣት አልፎ ወደ መረረ የስም ማጥፋት ዘመቻ የከተታችው ምክንያት የዶክተሩ የመጡበት አካባቢ ከደቡብ ኢትዮጵያ መሆኑ ነው። በእነዚህ አክራሪ ብሄረተኞች አመዳደብ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሰሜንና ደቡብ በሚባሉ ሁለት ዘውጎች (dichotomies) የተከፈለ ሲሆን፣ ሰሜነኛው  የአቢሲኒያ ዘውግ የለየለት ጠላት፣ ጨቋኝ እና የቀድሞ ስርዓት ናፋቂ በሚል መለያ ሲጠሩት ኖረዋል። ከዚህ ውጪ ያለው የኦሮሞና ደቡብ ዘውግ ከሰሜነኞቹ አንጻር በተቃራኒ የቆሙ ብቻ ሳይሆኑ የጨቆና እና የብዝበዛ ሰለባ በመሆናቸው አጋር አድርገው ይመለከቷቸዋል። የዶክተር ኃይሌ ታሪክ ትንተና የበለጠ ቁጣን የጨመረው ይህን የሁለት ዘውግ አከፋፈል ዋጋ ቢስ ስለሚያደርገው ነው። እዚህ ላይ ክርክሩ ያለው በአመክንዮ ወይንም ሳይንሳዊ ፈለግን ተከትሎ የሚደረስበት አካዳሚያዊ ድምዳሜ ሳይሆን በአክራሪ ኦሮሞ ብሄረተኞች አይን ይሄኛው ምሁር ከዚህኛው ዘውግ ከመጣ ወገንተኝነት ማሳየት ያለበት ለእውነት ወይንም ሙያዊ ግዴታው ሳይሆን ለመጣበት ጎሳ ወይንም አካባቢ መሆን አለበት የሚለው የጠባብነት መነሻ ነው። ይህ አይነት ጠባብ አክራሪነት በአካዳሚው ዓለም ገብቶ የሚያደርሰው ጉዳት ለጠቅላላው የሃገራችን ታሪክ ብቻ ሳይሆን በኦሮሞ ህዝብ ታሪክ ላይ የሚደረጉ የወደፊት ምርምሮች/ጥናቶችን የተዓማኒነት ጥርጣሬ ላይ የሚጥል ነው።

አክራሪ የሆኑት የኦሮሞ ልሂቃን በዶክተር ሃይሌ ላሬቦ ላይ የመረረ አቋም እንዲይዙ ካደረጉ ምክንያቶች ሶስተኛው፣ ምሁሩ ከዚህ ቀደም የጎሳ ፖለቲካ ዝንባሌ ባላቸው የታሪክ ጸሃፊያን የተደረሰውን ልብ-ወለዳዊ ታሪካ ገላልጠው እርቃኑን በማስቀረታቸው ነው። እኒህ አክራሪዎች ዶክተሩን ጠምደው የያዙበት ምክንያት ሌላ ሳይሆን ለምን እኛ የምንፈልገውን ታሪክ አልነገረንም ነው።

በኦሮሞ ጥናት ዘርፍ ውስጥ አዘውትረው ከሚጠቅሷቸው ጸሃፊያን መካከል ሲሳይ ኢብሳ፣ መኩሪያ ቡልቻ፣ አሰፋ ጃለታ፣ እና ቦኒ ሆለኮምብ (ብቸኛዋ የውጭ ሰው) ስራዎች ብንመረምር የአካዳሚክሱን ዓለም ምርምር ስርዓትን ያልተከተለ፣ የፖለቲካ ዓላማን ለማሳካት ተብሎ ብጭቅጫቂ እውነቶችን ከበዙ ውሸት ጋር በማዳበል የተደረሱ መሆናቸውን መረዳት ይቻላል። እንዲውም በታሪክ እና ስነ-ሰብ ጥናት አንቱ የተባሉ ምሁራን ከላይ በተዘረዘሩት ጸሃፊዎች ስራዎች ላይ ካቀረቡት ሂስ አንዱ ‘በምንም አይነት መለኪያ አካዳሚያዊ ደረጃን የማይመጥኑ’ እንደሆኑ ነው።

እነዚህ ከታሪክነት ይልቅ ለፕሮፓጋንዳ ፋይዳ ታልመው የተጻፉ ድርሳናት ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩ፣ በቂም በቀል እና የቁጭት ትረካዎች ላይ በማተኮር ታሪክ ሊኖራት የሚገባትን የመዳኘት ስልጣን እንዲንጋደድ በማድረግ የፖለቲካ መገልገያ እንድትሆን አድርገዋል። የዶክተር ሃይሌ ላሬቦ አደባባይ ወጥቶ የእነዚህን ሃሳውያን የታሪክ ትርከት ገልብጥቡን ያወጡት። የአክራሪ ብሄረተኞቹን ትርከት በተጨበጠ በታሪክ ማስረጃ ሲፈተን ለእውነት ሚዛን ላይ መቀመጥ እንደማይበቃ ዶ/ር ሃይሌ በትንተናቸው አረጋግጠዋል። አክራሪዎቹ የቆሙበትን የሃሰት ትርክት ከስር መሰረቱ በማናጋታቸው ነው የወከባ እና ማሸማቀቅ ሰለባ የሆኑት።

እንደ ሃገር በኢትዮጵያና በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ምህረት የለሽ ትችቶችን እንዲሁም ማጣጣሎችን እንደ ቋሚ ተግባራቸው  ይዘው የነበሩ እኒህ አክራሪ ብሄረተኞች አለን የሚሉትን የታሪክ ትርከት የሚያጠይቅ ባለሙያ ወደ አደባባይ ሲመጣ ዝም የማሰኘት በዘመቻ ሲጠመዱ ማየትን የመሰለ አሳሳቢ ነገር የለም። ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር የለችም፣ ታሪኳን ደብታራዎች የጻፉት ነው፣ ምኒሊክ ጥቁር አፍሪካዊ አይደለሁም ብሎአል፣ አቢሲኒያ በ19ኛው ክፍለዘመን ባደረገችው ወረራ 9 ሚልዮን ኦሮሞዎች አልቀዋልን የመሳሰሉ የታሪክ ፍብረካዎችን እንድንቀበል ያልተደረገ ሙከራ አልነበረም። ይባሱኑ ባለሙያው ታሪክን በተለየ ዓይን እንድናይ በማድረጉ ሃገር ይያዝልን ማለት፣ አንድ ጸሃፊ እንዳለው አለን በሚሉት የታሪክ መሰረት የራስ መተማመን ችግር (cultural insecurity) እንደሚጎላቸው ያሳያል።

እንደ ወጉ ከሆነ በዶ/ር ሃይሌ ላሬቦ ትንታኔ ወይንም የታሪክ አቀራረብ አለመስማማኝነት ተገቢ ሲሆን፣ ነገር ግን ከጭብጡ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸውን ክሶች በመደርደር አቅጣጫ ለማስቀየር መሞከር እውቀትም ብልጠትም አይደለም። የቀረበውን የታሪክ ትርክት የሚቃወም ወገን አለኝ ከሚለው ማስረጃ እና የታሪክ አተናተን ጋር መቅረብ ሲቻል፣ ጉዳዩን ህዝባችን ተሰደበ ተንቋሸሸ በሚሉ አጓጉል ምክንያቶች ወደሌላ መውሰድ አክራሪ ብሄረተኞቻችን ምን ያህል ሃገራችንን እና ህዝብን ወደ አደገኛ  መንገድ እየወሰዱአት እንዳለ ያመላክታል። ይህ ሁኔታ በዚህ ከቀጠለ በሃገራችን የአካዳሚክ ምርምር ነጻነት እና ሃሳብን በነጻ የመግለጽ ነጻነት የባሰ አደጋ ውስጥ እየገቡ እንዳለ ጠቋሚ ነው። ይህ ድርጊት ታሪክን ከማጣመም የከፋ ወንጀል ባሻገር፤ የሚፈጥራቸው ሌሎች አስከፊ መዘዞችም አሉ። እነዚህ አክራሪ ብሄረተኞች የደረሱበት ነገርን የማደፍረስ እና በዓለም ዓቀፍ ደረጃም ጭምር ሌላ አይነት የኢትዮጵያ ታሪክ ትርከት ተቀባይነት እንዲኖረው ለማድረግ  ፋታ የለሽ  የተቀናጀ ዘመቻ መሰረታዊው ምክንያት የኢትዮጵያ ምሁራን – በተለይ ወጣቶች ቸልተኝነት እና በበቂ ሁኔታ የተቀናጀ እና ተከታታይነት ያለው ምላሽ የመስጠት ጥረት ባለመኖሩ ነው።

(ዶ/ር ነብዩ ጋቢሳ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Viewing all 2265 articles
Browse latest View live