Quantcast
Channel: Amharic News – Medrek
Viewing all 2265 articles
Browse latest View live

ማኅበራዊ ብዙሃን መገናኛ እና የመብት አራማጅነት በዋሽንግተን ዲሲ የተደረገ ውይይት

$
0
0

025ae1-satenaw-newsየኢትዮጵያ መንግሥት በዜጎች ላይ ያደርሰዋል ያሉትን በደል ለማጋለጥ እና የመጻፍ ነፃነትን ለማረጋገጥ ማኅበራዊ ሚዲያ ያበረከተላቸውን አስተዋፆና በየገፆቻቸው ስለ ሠሩት ሥራ ገለፃ በማድረግ አራት የኢንተርኔት ማኅበራዊ ሚዲያ አራማጆች ውይይት አድርገው ነበር።

ዋሽንግተን ዲሲ —የኢትዮጵያ መንግሥት በዜጎች ላይ ያደርሰዋል ያሉትን በደል ለማጋለጥ እና የመጻፍ ነፃነትን ለማረጋገጥ ማኅበራዊ ሚዲያ ያበረከተላቸውን አስተዋፆና በየገፆቻቸው ስለ ሠሩት ሥራ ገለፃ በማድረግ አራት የኢንተርኔት ማኅበራዊ ሚዲያ አራማጆች ውይይት አድርገው ነበር።ከዞን ዘጠኝ ወ/ት ሶሊያና ሽመለስ፣ ከድምፃችን ይሰማ አቶ የደስደስ ያሲን፣ ከአማራ ተጋድሎ አቶ አቻምየለህ ታመሩ እና ከኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ እንዲሁም በግል የፌስ ቡክ ገጹ ከ937 ሺህ በላይ ተከታይ ያለው አቶ ጃዋር መሐመድ አቅራቢዎች ነበሩ።

ሦስት ሰዓት የፈጀው ውይይት የተዘጋጀው ኢቲዮቲዩብ በተባለው የኦንላይን ሚዲያ አማካኝነት ሲሆን ጽዮን ግርማ ከማኅበራዊ ሚዲያ ጋር በተያያዘ የተነሱት ነጥቦች ብቻ አጠር አድርጋ ትዳስሰዋለች።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ድምፅ ያድምጡ።  [VOA Amharic }

if(typeof(jQuery)==”function”){(function($){$.fn.fitVids=function(){}})(jQuery)};jwplayer(‘jwplayer-1’).setup({“file”:”http://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2016/09/VOA_u121bu1285u1260u122bu12ca-u1265u12d9u1203u1295-u1218u1308u1293u129b-u12a5u1293-u12e8u1218u1265u1275-u12a0u122bu121bu1305u1290u1275-_Sept-26-2016_u133du12eeu1295-u130du122du121b.mp3″});

 


ሰበር ዜና – አቡነ አብርሃም በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት በአደባባይ ገሰፁ [ጉዳያችን]

$
0
0

Ethiopian Orthodox Tewahido Church synod member and Archbishop Abune Abraham strongly criticised the current regime of Ethiopia.

abune-abraham-satenaw-news
አቡነ አብርሃም የምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
አቡነ አብርሃም የምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ መስከረም 16፣2009 ዓም በባህርዳር በተከበረው የደመራ መስቀል በዓል ላይ ለተሰበሰበው ምዕመን ስለ እውነት  በአደባባይ መስክረዋል። በአሜሪካ የዲሲ እና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም የነበሩት አቡነ አብርሃም በእዚሁ  አገልግሎታቸው በምእመናን በተለይ በወጣቶች ዘንድ ከፍተኛ ፍቅርን አትርፈው እንደነበር ብዙዎች ይመሰክራሉ። በተለይ በምእመናን መካከል የሚነሱ ግጭቶችን በማስታረቅ እና መናገር እና መስማት የማይችሉ ወጣቶች መንፈሳዊ አገልግሎት በምልክት እንዲማሩ ያደረጉት ጥረት ተጠቃሽ ነው።ከአሜሪካ አገልግሎታቸው በመቀጠል የምስራቅ ሐረርጌ እና የጅጅጋ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው አገልግለዋል።በአሁኑ ወቅት የምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናችው።
አቡነ አብርሃም በዛሬው የባህር ዳር ደመራ ላይ ከመሰከሩት እውነት ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል።
´´
´´ችግሩ ያለው ከመሪዎች እንጅ ከተመሪ አይደለም ….መንግስትን ና የራሱን ሚድያ ገስጹ የህዝብ ጥያቄ መመለስ አለበት ….እኔ ከመፍራቴ አንጻር በዓሉ ባይከበር ደስተኛ ነበርሁ ነገር ግን አባቶቼን ሳይ በየሳምንቱ ቢከበርም አይቆጨኝም።ትናንት አስከሬን እያወጣ አልቅሱ ሲለን ነበር።…..የህዝቡ ጥያቄ መመለስ አለበት። …..ወታደር ከዚህ በኋላ የሰላምን ምላጭ እንጅ የመሳሪያን ምላጭ መሳብህን አቁም።….በየሀገሩ በስደት ያለው ወገናችን መመለስ አለብት ። ……እኛ አባቶች የምናገረውን በተገቢው መልኩ ለህዝብ የማታቀርቡ የመንግስት ሚድያ ካላስተካከላችሁ ከዚህ በኋላ አደባባዩ አትገቡም።እኛ የተናገርነውን ትቆራርጡ ታቀርቡ እና ምእመኑ ምን አባት አለን እንዲል ታደርጋላችሁ። ክርስቲያን እውነት ይናገራል።…….ለእዚች አገር መጠበቅ ቤተ ክርስቲያን አስተዋፅኦ ትልቅ ነው።ቤተ ክርስቲያን ስለ ወታደርም ትፀልያለች።ሕዝብ የሚጠብቁትን ጠብቅ እያለች የምትፀልይ ይህች ቤተ ክርስቲያን ነች።ስለዚህ ልትደመጥ ይገባታል።አንድ ሰው ባልሰራው ከታሰረ፣እግዚአብሔርስ እንዴት ዝም ይላል።ሁላችንም እንደወንድምነት እንተባበር። ስንት ወገናችን በበረሃ አለቀ።……..ዛሬ ስጋት ነው።አሁን የመጣው ሕዝብ ለሃይማኖቴ ልምጣ ብሎ የመጣ እንጂ ማንም ይጠብቀናል ብሎ አይደለም የመጣው።……

……..ያለ በደላቸው የታሰሩት ወንድሞቻችን መፈታት አለባቸው። …..ጠላትን እንዳላንበረከኩ አባቶቻችን ፤ዛሬ ለምን እርስ በእርስ ተከፋፈልን? የተሸከምነው መሳሪያ ከክርስቶስ መስቀል አይበልጥም። …..ወታደሮችና ድንበር ጠባቂዎች ስለ እናንተ ቤተክርስቲያን ስለምትጸልይ የሷ ልጆች ናችሁና ደም አታፍሱ። ´´ የሚሉ ይገኙበታል።
አቡነ አብርሃም ይህንን ሲናገሩ ምእመናን በእልልታ እና በእንባ ስሜታቸውን ይገልፁ ነበር።ከዛሬው የባህርዳር ደመራ በኃላ አቡነ አብርሃም ሕዝብ ወደ ቤቱ ሳይገባ እኔ አልገባም በማለት ህዝቡ ከሄደ በኃላ በእግራቸው ወደ ቤታቸው በፖሊስ ታጅበው ሄደዋል።
በቅዱስ ሲኖዶስ አባል ደረጃ በመስቀል ደመራ ላይ አሁን በስልጣን ላይ የሚገኘው የሕወሓትን መንግስት በግልጽ ስገሰፅ የአቡነ አብርሃም የመጀመርያው ይሆናል። አቡነ አብርሃም እናከብርዎታለን።በእዚህ የመከራ ዘመን ለኢትዮጵያ እንደ አቡነ ጴጥሮስ በአደባባይ ስለ እውነት የመሰከሩ ምስክር ሆነዋልና።እርስዎ የተጋረደውን አዚም ገፈውታል።ፈለግዎን ተከትለው ሌሎች አባቶችን ድምፅ አሁንም በብዛት መስማት እንፈልጋለን። ድምፅ ብቻ አይደለም ምእመኑን በመከራው ሰዓት አብረው እየተንገላቱ የሚያፀኑ ካህናት መብዛት አለባቸው።

አቡነ አብርሃም ያደረጉት ንግግር ኦድዮ ለመስማት ይህንን ይጫኑ ።

ጉዳያችን GUDAYACHN

   የሕዝባዊ እምብኝተኝነቱና ገዥዎቻችን!! [ከሙሉቀን ተስፋው]

$
0
0

የትግራይ ምድር ያበቃላቸው የዘመኑ ናዚዎች የሕብረተሰቡን ግፍና በደል ነዳጅ እየጨመሩ ማባባሳቸው አልበቃ ብሎ ጭራሹን ተደብቆና ሰምተነው የማናውቀውን ምሥጢር በመገናኛ ብዙሃን በመልቀቅ የሕዝቡን ትኩሳት መለኪያ ማድረግ ጀምረዋል።«ጠግበው ዝላይ አበዙ ሲዘሉ መሰባበር ጀመሩ»ኢህአፓን በትግራይ ምድር መታገል እንደማይችል የሞገቱና በጦርነት ያስለቀቁ የትግራይ ወራሪዎች ከምእራብ እስከ ምሥራቅ ከደቡብ እስከ ሰሜን ዘልቀው ሲወሩ ትግራይን የግላቸው ኢትዮጵያን ደግሞ መጀመርያ የጋራ አሁን ከአለው ነባራዊ ሁኔታ ስንነሳ ደግሞ ኢትዮጵያንም የእኛ ብቻ ናት በማለት ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ዜጐች አሳዶ በመግደል እና በማሰደድ ኢትዮጵያ የእነሱና የእነሱ ግብረ-አበሮች አገር ብቻ ለማድረግ የመጨረሻው ምእራፍ ላይ ይገኛሉ።

ሳይደግሱ አይጣሉ ! እንዲሉ በመላው ኦሮምያና በሰሜን ምእራብ ጐንደር ወልቃይት ላይ የተቀጣጠለው ሕዝባዊ አመጽ ያልጠበቁት የቁጣ ወጀብ ይዞ ብቅ በማለቱ እነሆ ህወሃታውያን ሲርበደበዱና የራሳቸውን ጥላ እንኳን ማመን ከማይችሉበት ወቅት ላይ ደርሰናል።የቁጣው ወጀብ በፍጹም እነሱን መሬት ውስጥ ሳይከታቸው እንደማይቆም ግልጽ ቢሆንም በዚህ የሕዝባዊ እምብኝተኝነት እንቅስቃሴ ሂደት ግን አንድ አሳዛኝ ክስተት መፈጠሩ በግልጽ ነጥሮ ሊቀመጥ ይገባዋል።ይኸውም ሁሉም አይነት የተቃዋሚ ኃይሎች በየተሰለፉበት ጎራ አንድ እዚህ ግባ የማይባልና ወንዝ የሚያሻግር ተግባር ሳይፈጽሙ የሕዝባዊ አመጹ ተከታይ ጭራ ሆነው መገኘታቸው በእጅጉ የሚቆጭ ብቻ ሳይሆን አሁንም ቢሆን ይህን የሕዝባዊ እምብኝተኝነት ትግል አማክሎ ለመምራትና ግቡን እንዲመታ የሚያደርግ ሁኔታ ላይ አለመገኘታቸው የተተኪውን ትውልድ ተስፋ ለማጨለም ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ሴራ ነው ብሎ ለመናገር የሚያስችል ይመስለኛል።

ሊገድሉ ሄደው ሲሞቱ እየየው ማለት ራሳቸው ገድለው መርዶ አርጅ መሆን እንመራዋለን የሚሉትን ሕዝብ እየገደሉ በአባሸባሪነት ማሳበብ ልጅ ወላጅን ሳይሆን ወላጆች ልጆቻቸውን የሚቀብሩበት ወቅት ላይ መድረስ ማለት ኢትዮጵያ እንዴት ካለው የከፋ ደረጃ ላይ እንደደረሰች ማሳያ ከዚህ በላይ መቸም ቢሆን ሊኖር አይችልም።የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የኢትዮጵያዊ ማንነት መለኪያው ሀገርንና ሕዝብን ከጥፋት ለማዳን በጋራ ጠላት ላይ የማያዳግም ርምጃ ወስዶ ሕዝብ እፎይታን እንዲያገኝ ማድረግ ሀገሪቱ ሉዓላዊነቷ ተከብሮና ታፍሮ እንዲኖር ማድረግን መሠረት ያደረገ ስለሆነ በተግባር የምንፈተንበት ወቅት እነሆ አሁን ነውና እያንዳንዳችን ፈተናውን ለማለፍ ቁርጠኝነቱ በእጃችን ላይ ይገኛል። ቁርጠኞች የኢትዮጵያ ልጆች በአማራና ኦሮሞ ምድር መስእዋትነትን እየከፈሉ ይገኛሉ በውጭ የሚኖረው ስደተኛ ኢትዮጵያዊም አጋርነቱን በሰላማዊ ትእይንት መሬት አንቀጥቅጥ ትግሉን እያፋፋመ ይገኛል።

እኛና ገዥዎቻችን የተለያየነው ገና ይህ እኩይና ሀሳበ ኩድኩድ ድርጅት ሲመሠረትና ኢህአፓን ከትግራይ ምድር በጦርነት ሲወጋ ቢሆንም ህወሃት ተከዜን ተሻግሮ ሲመጣ ዝምታን መርጠን ከዚያም እቤተ መንግሥታችን ድረስ ገብተው ታሪካዊ እሴቶቻችን ሲያጠፉ፤ሉዓላዊነታችንን ሲያስደፍሩ አንዱ ሲጮህ ሌላኛው ሲቀልድ እዚህ ብንደርስም አሁን ግን አገር ወራሪው ሕወሃት ለእያንዳንዳችን ማነቂያ ገመድ አዘጋጅቶ የእያንዳንዳችን በር በርግዶ በመግባት ማነቅ ሲጀምር ዕንኳን እኛ የጥቃቱ ሰለባ የሆን የራሱ የሥርዓቱ ተጠቃሚ የሆኑትም ዱላው እንደማይምራቸው ተገንዝበው ከሥርዓቱ ለማምለጥ እየባከኑ ይገኛሉ።በተቃውሞ ጐራ የተሰለፉ ኃይሎች ይህን በገዥው ሥርዓት የተፈጠረውን ክፍተትና የእርስ በርስ መናኮር፤የአንድ ጐሣ የበላይነት እየፈጠረ ያለውን ውስጣዊ ንቅዘት በመጠቀም በገዥው ቡድን ውስጥ የህቡ መዋቅር አለመዘርጋት የተቃውሞ ጎራውን እየዘወሩ ያሉ ኃይሎችን ፖለቲካዊ የድርጅት ብስለትና ጥንካሬ አለመኖር በቀላሉ እንድንገነዘበው አድርጓል።

ልማታዊ መንግሥት እያሉ ሲደልሉን የከረሙት ህወሃትና ግብረ በላዎቹ ሞት! የነሱንም በር ማንኳኳት ሲጀምር ይመጻደቁበት የነበረውን ልማትም ማውደም ጀምረዋል።ስብሰባ ዘጠኝ ጊዜ ስብሰባ የስብሰባው አባዜ ከሕዝቡ ውስጥ ያሉ ፋና ወጊዎችን ለመለየትና ለእርድ ለማቅረብ እንጅ ከቶ ሌላ ምንም ፋይዳ የለውም ይህ በ25 ዓመት ውስጥ ከዚህ የታሪክ አተላና ቅጥረኛ ድርጅት ጠንቅቀን የተረዳነው ባህሪ ነው።በአሁኑ ሰአት የአማራና የኦሮሞ ክልሎች አስተዳደራዊ መዋቅራቸው ፈርሶ በህወሃት ቅልብ የአጋዚ ሠራዊት እየተመራ ይገኛል በተለይ በአማራ ክልል ብአዴንና የአማራው ክልል ምክር ቤት ፈርሰው የህወሃት አሽከርነታቸውን አረጋግጠዋል። የሰሞኑ የብአዴን የባህርዳር ስብሰባና ውጤቱ ምን ያህል የበሸቀጠ እጁን ለህወሃት የሰጠ ቅጥረኛ አመራር መካበቱን ያሳያል።የወልቃይትን ጥያቄ መልሱ ሲባሉ ጠገዴን በምትኩ ከሰጣችሁን?ብለዋል ጠገዴ ላይ ለመድረስ መጀመርያ ወልቃይትንና ጠለምትን ማለፍ አለብሕ ከዚህ ወዲያ ግራ መጋባትና መደንበር ውጭ ከዚህ ሥርዓት ምን ይጠበቃል?የአማራ ምክር ቤትና ብአዴን እውን ከሕሊናቸው ጋር ያሉ ቢሆን ኖሮ የወልቃይት ጠገዴና ጠለምትን፤የራያና ቆቦን እንዲሁም የመተከልን ምድር አሳልፈው ባልሰጡ ነበር።

 እኔ ዛሬ ኢትዮጵያዊ ወገኖቼን ህወሃት ገዳይ፤ህወሃት ደም ያሰከረው፤ህወሃት ወራሪ፤ህወሃት አገር ሻጭ፤ህወሃት ዘራፊ፤ህወሃት ተስፋፊ፤ህወሃት ከሕዝብ የተነጠለ፤ህወሃት አሸባሪና ፀረ-ሕዝብ መሆኑን ለመስበክ አይደለም ብዕሬን ያነጣጠርኩት።ይህ የበሸቀጠ ሥርዓት አክትሞለታል ነዳጅ ሆነው ያላሰለሰ ድጋፍ ይቸሩለት የነበሩት ጌቶችም ጀርባቸውን መስጠት ጀምረዋል ስለዚህ ለሀገራችን መጻይ እድልና እጣ-ፈንታ ምን እንሁን ምን እናድርግ በሚለው ጉዳይ ላይ እያንጎላቹ የሚገኙትን ነቃ ብለው አንድ እልባት ያለው ነገር ለመፍጠር በጋራ መላ እንመታ ዘንድ ነው።እዚህ ላይ ልጠቅሰው የምገደደውነገር ቢኖር ሕጋዊ የሆነው በስደት ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶቻችን የገዥውን ቡድን አውግዘዋል ንሳሃ እንዲገባም መክረዋል።በሌላ ወገን ደግሞ የተቃዋሚ ኃይል የሚባሉትንም አንዲት አገር አንድ ሕዝብ እንዳለን እና በጋራ ታግለው ይህን መደዴ የባንዳ ቡድን እንዲጥሉ ሲመክሩ አስተውያለሁ።ከዚህ ወዲያ ግን በዚህ በጀመሩት መንገድ መሄድ ከፈለጉ ሕጋዊ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ባለፈው አይነት መንገድ ማስተናገድ እንደማትችል በግልጽ አማርኛ ተናግረዋል።

የሕዝቡ እምብኝተኝነት መሪ የሌለው መሆኑን ከሚያሳዩ ነጥቦች ጥቂቶቹ ኦሮሞ አካባቢ ሲገሰግስ አማራው ላይ አዝጋሚ ሁኔታ ይታያል አማራው አካባቢ ላይ ፍጥነት ሲጨምር ኦሮሞው ላይ አዝጋሚ ሆኖ ይታያል።፤ይህ በአማራውና በኦሮሞው አካባቢ የተከሰተ ሲሆን ሌሎች አካባቢዎችም ችግሩ ሁሉንም እኩል እየጋረጠ እያለ ትንሽ እንኳን የመፍጨርጨር ሁኔታ አያሳዩም ይህ ማለት የተቃዋሚ ኃይሎች በዚህ አካባቢ አንድም የሠሩት ነገር እንደሌለ አመላካች ነው።፤ችግሩን በነፍጥ እናስወግዳለን ብለው የኢሳይያስን መንግሥት አምነው ወደ አሥመራ ያመሩት ኃይሎችም ሥርዓቱ በሕዝባዊ እምብኝተኝነት እስኪወገድ የሚጠብቁ ካልሆነ በስተቀር ጊዜው አሁን ነበር በሌሎች አካባቢዎች መድረስ ባይቻልም ከፊት ላፊታቸው በእሣት እየነደደች ወደ አለችው ጎንደር እንኳን ደርሶ እርዳታ መስጠት አልቻሉም።ይህን ጉዳይ እኔ ብቻ ሳይሆን ሁላችንም በደንብ ልናስብበትና እንድምታው ምንድን ነው ከሚለው መደምደሚያ ላይ ልንደርስ ይገባናል።

ብዙዎቹ ድርጅቶች በውጭ የተደራጁ ሲሆኑ ከፊሎቹ ደግሞ በሀገር ውስጥ ነው።እነዚህ ድርጅቶች ትግልንና የትግልን ባህርይ በውል የተገነዘቡ ናቸው ለማለት በእጅጉ ይከብዳል።ለምሳሌ የሰላማዊ ትግሉን በር ጥርቅም አደርጎ ከዘጋው የትግራይ ወራሪ ቡድን ጋር ለመታገል ተነስቻለሁ ብሎ ማወጅ ለወራሪው ቡድን ላሜ ወለደች አይነት ነገር ነው የሚሆነው ለምን ከሕዝቡ እንዳይደርሱ የሚያደርግ እቅድ እንዲነድፍ አረንጓዴ መብራት ማሳየት ነው-ቢያንስ በሕቡእ ተደራጅቶ ሕዝቡን አደራጅቶ መዝለቅ ነበረባቸው አላደረጉትም።ሌላው በውጭ የሚኖሩ የተደራጁ የተቃዋሚ ኃይሎች መጀመርያ ከሕዝብ ጋር ሊያገናኝ የሚችል መረብ ሳይዘረጉ በኃይል ተገፍተው የተሰደዱ ሲሆን እንዴት ከሕዝብ ጋር ሊያገናኝ የሚችል መረብ መዘርጋት እንዳለባቸው ብውል ያሰቡበት አይመስልም በዚህ ላይ አንዱ በሌላኛው ላይ ጣቱን መቀሰርና የመጥለፊያ ወጥመድ ከማጥመድ በስተቀር ትብብርና መደጋገፍን ሲያሳዩ አይስተዋሉም።ስሜተኝነት ይበዛል ጥቂት የሰው ኃይል አለኝ የሚሉት ደግሞ ከህወሃት በከፋ መልኩ ሕዝቡን በጋራ እንዳይቆም እያመሱት ይታያሉ ምስኪኑ ስደተኛ ወገኔም ያለቦታው እየገባ ከማጫፈር ባለፈ እየሄዳችሁበት ያለው መንገድ አላማረኝም እዚህ ላይ ቆም በሉ ሕዝቡንም ሆነ አገሪቱን አይበጅም ብሎ መሞገት አልቻለም።እንግዲህ ይህ ሁሉ ተዳምሮ የቅጥር ነብሰገዳዮችን እድሜ ማራዘሙ ግልጽ ነው።አድሎአዊነት ራስን መካብ በመገናኛ ብዙሃን አካባቢ የተማከለ መረጃ ለመሆን ብዙ ጉለት ያለው ቢሆንም ያችውኗን ከፍ አድርጎ በመያዝ የአምልኩኝነት አባዜ ይታያል።እንደ ጀግንነት የሚቆጠርበት ሁኔታ ይስተዋላል፤የፖለቲካ አክቲቪስቶች ስለተለያዩ አካባቢዎች በተናጠል ከማሰብ የወጡ አይደሉም። እንግዲህ ኢትዮጵያችን ይህን ሁሉ ሸክም ተሸክማ ነው ቅጥረኛውን የትግራይ ወራሪ ቡድን ከሕዝብ ራስ እናወርዳለን የሚሉትን እያስተናገደች የምትገኘው።ምናልባት ይህ ሰው እንዴት እንዲህ መዳፈር አበዛ ልትሉኝ ትችሉ ይሆናል? እኔ ከራሴ እየደረሱ የተመለከትኳቸውን ገጠመኞች ነው እየገለጽኩ ያለሁት። መፍትሄው ምን ይሁን የሚለውን የጹፌ ማጠቃለያ አድርጌ የዛሬውን ዝግጅቴ አጠናቅቃለሁ።

አንድ፦

እኛ ከ1950ዎቹ አመታት ጀምሮ አዲስ ስርአት እናመጣለን ብለን ራሳችን የለውጥ ሐዋርያ በማድረግ እየተወዛወዝን ዛሬ ላይ የደረስን ኃይሎች ሊህቃንና የፖለቲካ ጠበብት ነን ባዮች የታገልንለት ዓላማ ፋይዳ ቢስ ሆኖ ከሃዲዎችንና አገር አጥፊዎችን ተክቷል።አሁን ይህን የጎጠኛና የወራሪ ቡድን መውለቂያው እንደደረሰ ጥርስ እያናጉት የሚገኙት በዚህ አስከፊ ሥርዓት ተወልደው አድገው ይህ ሥርዓት ለሀገርና ለትውልድ የማይበጅ በመሆኑ መወገድ አለበት ብለው ግንባራቸውን ለጥይት ሰጥተው ገጥመውታል።ለዚህ ጦስ ያበቃናቸው እኛ ስንሆን እነሱ ግን ይህን አደረጋችሁ ብለው ጣታቸውን አልቀሰሩብንም ስለዚህ ትግሉን ሊያፋጥን የሚችል ድጋፍ ከመስጠት ባሻገር ሥልጣን እይዛለሁ ብሎ በልቡ የሰነቀ ሁሉ እጁን ሊሰበስብ ይገባዋል።

 ሁለት፦

ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል ከየት የሌለ ታሪክ እየደረትን አዲሱን ትውልድ ግራ አጋብተናል ይህን መፋቅና ማስተካከል ይጠበቅብናል።ለረጅም አመታት አንዱን ሕዝብ ከሌላው ሕዝብ ለማናከስ የተጠነሰሰው ሴራ ጎንደር ላይ ከፍ ብሎ በተጣራ ድምጽ ሲመክን አስተውለናል። «የጎንደር ወጣቶች ራሳቸው እየሞቱ የኦሮሞው ሞትም የእኛ ሞት ነው ማለታቸው» «የኦሮሞ ወጣቶች ጎንደር ላይ የሚፈሰው ደም የወንድሞቻችን ደም ነው» በማለታቸው ምን ያህል የትግል አጋርነትና ትሥስር እንደፈጠረ አስተውለናል።ይህን ለማበረታታት በሀገር ቤትም ሆነ በውጭ የተደራጁ ተቃሚ ኃይሎች ከዚህ ትምህርት ወስደው አንድ ጠንካራ የጋራ ግንባር ፈጥረው እየተካሄደ ያለውን ትግል ማጎልበት አለባቸው።

 ሦስት፦ሞረሽ ወገኔ የአማራ ድርጅት በጠራው የገቢ ማሰባሰቢያ ምሽት ሁለት ወጣቶች ወደ መድረክ ወጥተው ምሁራንና ፖለቲከኞችን አንድ ጠበቅ ያለ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።ይኸውም ከቻላችሁ እርዱን የማትችሉ ከሆነ መንገዱን ልቀቁልን አታደናቅፉን ነበር ያሉት።እውነተኛ አባባል ነው እኛ አላማረብንም ጊዜውም አልፎብናል ስለዚህ በዚህ በአዲሱ ትውልድ ጊዜ መቀለዱን ተትን አቅማችን በፈቀደው መጠን እንርዳቸው መንገዱን ላይመለሱ ጀምረውታል።

አራት፦

የሀገርና የሕዝብ ጠላት የሆነው ወራሪው የህወሃት ቡድን አንድ የማይወደው ነገር ቢኖር አንድነት የምትለዋን ቃል ነው እኛ ደግሞ ይህን እያወቅንና እየተረዳን አንድነትን ሊያመጣ የሚችለውን መንገድ ለመያዝ አልቻልንም አሁንም ስለአንድነት እየሰበክን ነው አንድነትን ለማምጣት ደግሞ ግልጽና በውስጥ ቅንነት ሊኖረን ይገባል እኛ ደግሞ ግልጽና ቅኖች አይደለንም። ለዚህ ዝግጁ ነኝ የሚል ካለ የምንንም ፈቃድ መጠየቅ ሳይኖርበት መጀመር ይችላል። ለምሳሌ ሁለቱ አንጋፋና ሰፊ ሕዝብ ያላቸው አማራውና ኦሮሞው አሁን የተጀመረውን ትብብር አጠናክረው ቢቀጥሉና በማእቀፋቸው ውስጥ ያሉ ቡድኖችና ድርጅቶችን ወደ ጋራ ትግሉ መሳብ ቢችሉ የአንድነት ውጥን ተጀመረ ማለት ይቻላል።ወደ ሌሎች ደግሞ ቀስ በቀስ ማቅናት ይቻላል።ባልሳሳት በዚህ መንገድ የተሄደበት አይመስለኝምና እንሞክረው።

ከዚህ ባሻገር በአማራ ክልል በስለላና ወጣቱን ትውልድ እያስበሉ ያሉ ግለሰቦችን ስም ዝርዝር ከዚህ ጹሑፍ ጋር አያይዥ ለማቅረብ ሞክሪያለሁ። በሙሉቀን ተስፋው ተዘጋጅቶ ወልቃይት ዳትካም ላይ የተወሰደ።ሲሆን ከነዚህ 72 ቅጥር ነብሰጋዳዮች ውስጥ በብዛት ከደብረታቦርና ወሎ ለበረከት ስምኦንና አዲሱ ለገሰ ኪራይ ስብሳቢ የነበሩ፤በደርግ ጊዜ በቁንጅና ለስለላ ተሠማርተው የነበሩ እንደ ደሴ አሰሜ ያለው ደግሞ አብደራፊና ማሰሮ ደንብ ትክል ድንጋይ በነበረበት ጊዜ በርካታ የአርማጭሆ ፤ወልቃይትና ጠገዴ ተወላጆችን ከነቹቹ አለባቸውና ሹመት መልካሙ ጋር በመሆን የጨፈጨፈ ይገኙበታል።  September 27, 2016 More

Print PDF

የዘረኛ የትግራይ ወያኔ አገልጋይ በመሆኑ አማራ ወጣቶችን የሚያስገድሉ 72 ባለሥልጣናትና ደህንነቶችን ስም ዝርዝር ከዚህ በታች ያንብቡ።

(ከሙሉቀን ተስፋው)tigist-satenawnews-6

 

ወ/ሮ ገነት ገ/እግዚአብሔር – የአማራ ክልል የኢንዱስትሪ ከተማ ልማት ቢሮ ኃላፊ

ከሕወሓት መልዕክት እየተቀበሉ ወጣቱን በማሳፈስ እና ጊዚያዊ የፌድራል ፖሊስ እና መከላከያ ኃይል ጊዚያዊ ማዘዥያ እዝ ከመንግሥት በጀት በመመደብ፤ መኪና በማቅረብ እና በማቀናጀት በቀጥታ እየመሩት ያሉ አማራ ነን የሚሉ ባለስልጣናት ታወቁ፡፡ የአማራውን ተጋድሎ በሚመሩ የጎበዝ አለቆች ከተባባሪ የአማራ ተወላጅ የመንግሥት ባለሥልጣናትና የፖሊስ ኃላፊዎች ጋር በመተባበር 72 ሕወሓትና የሕወሓት ቅጥረኛ ባለሥልጣናትና ደኅንነት አባላት በስም ተለይተዋል፡፡

ጥናቱን ያካሔደው የጎበዝ አለቆች ቡድን / ገነት /እግዚአብሔር የተባለችውን የትግራይ ተወላጅና የክልሉ የኢንዱስትሪ ከተማ ልማት ቢሮ ኃላፊዋን በቀዳሚ ጠላትነት አስቀምጧል፡፡

ሁለተኛው አቶ ብናልፍ አንዷለም ሲሆን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ እና ም/ርዕስ መስተዳድር ሲሆን በየቦታው የታሰሩ እና የታጎሩ የአማራ ልጆችን ጉዳይ ይዞ በመምራት እና አስካሁን የታሰሩት ያለምንም መፍትሔ ብርሸለቆና ሰባታሚት ብሎም በየጣቢያው ለሚሰቃዩ ወገኖች ዋናውን ኃላፊነት ድርሻ ወስዷል፡፡

በተጨማሪም አቶ ደሴ አሰሜ፤ የአማራ ክልል አሰተዳደር እና ፀጥታ ጉዳየች ቢሮ ኃላፊ፣ አቶ አየለ አናውጤ የክልሉ የመረጃ እና ደህንነት ጉዳይ ዋና የስራ ሂደት መሪ፣ አቶ ደሴ ደጀን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር፣ አቶ የማነ ነገሽ የአማራ ክልል አሰተዳደር እና ፀጥታ ጉዳዩች ቢሮ የመረጃ እና ስምሪት ኮሚቴ አባል ናቸው፡፡

በተለይም በአሁኑ ስዓት በመላው የአማራ ክልል እየተቀጣጠለ ያለውን አመፅ እና ከግብ እንዳይደረስ ሕወሓት አዋቅሮ እያሰራቸው የሚገኙ የክልሉ 72 ባለስልጣናት እንደሚከተለው ይቀርባሉ፡፡

 

  1. ኮማነደር ኢሳያስ ገ/ ኪዳን ከብሄራዊ ደህንነት መረጃ
    2. አቶ ይርሳው ታምሬ
    3. አቶ ብናልፍ አንዷለም
    4. አቶ አለምነው መኮንን
    5. ዶ/ር ተሾመ ዋለ
    6. አቶ ፍርዴ ቸሩ
    7. አቶ አወቀ እንየው
    8. አቶ አየልኝ ሙሉዓለም
    9. አቶ አየነው በላይ
    10. አቶ ደሴ አሰሜ
    11. አቶ ዘመነ ፀሃይ
    12. አቶ ንጉሱ ጥላሁን
    13. አቶ ተስፋየ – የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ገበያልማት ቢሮ ኃላፊ
    14. አቶ ፈንታ ደጀን
    15. አቶ ደሳለኝ ወዳጀ
    16. አቶ በላይ – በጤና ቢሮ የወባ መከላከል የስራ ሂደት መሪ
    17. አቶ ሃብቴ – በትምህርት ቢሮ የአይሲቲ ክፍል ኃላፊ
    18. አቶ ማማሩ ጽድቁ
    19. ም/ኮሚሽነር ደስየ ደጀን
    20. አቶ መኮንን የለውምወሰን – የአብቁተ ዋና ዳይሬክተር
    21. አቶ መላኩ አለበል – የኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ
    22. አቶ ምስራቅ የሙሉዓለም – ባህል ማዕከል ስራ አስኪያጅ
    23. አቶ ምትኩ – የጥረት ኮርፖሬት ምክትል ስራ አስፈፃሚ
    24. አቶ ስዩም አዳሙ
    25. አቶ ሙሉጌታ ደባሱ
    26. አቶ ስዩም አድማሱ
    27. አቶ ተፈራ ፈይሳ
    28. አቶ ሺፈራው – ግብርና ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ባለሙያ
    29. አቶ ተስፋየ – የልህቀት ማዕከል ኃላፊ
    30. አቶ ቴዎድሮስ – የቀድሞ ጣና ሃይቅ ትራንስፖርት ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ የነበረ አሁን መቅደላ ኮንስትራክሽን
    31. አቶ ዘላለም ህብስቱ
    32. አቶ የማነ ነጋሽ
    33. አቶ ጌትነት – የገጠር መንገድ ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ
    34. አቶ ስለሺ ተመስገን
    35. አቶ ዘላለም – የግብይት ልማት የስራ ሂደት መሪ
    36. አቶ ዳንኤል – የሆቴሎች ማህበር ፕሬዚደንት
    37. አቶ ኃ/ኢየሱስ ፍላቴ
    38. አቶ ብርሃኑ – የባህል፣ ቱሪዝምና ፓርኮች ልማት ቢሮ ም/ኃላፊ
    39. አቶ ላቀ ጥላየ
    40. አቶ ሙሃመድ – አልማ ምክ/ስራ አስፈፃሚ
    41. አቶ አለማየሁ ሞገስ
    42. አቶ አጉማስ – የከተሞች ልማትና ግንባታ አክስዮን ማህበር ኃላፊ
    43. አቶ ደመቀ – የከተሞች ልማትና ግንባታ አክስዮን ማህበር ባለሙያ
    44. አቶ አሻግሬ – የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ የህፃናት የስራ ሂደት መሪ
    45. ዶ/ር ፋንታሁን መንግስቱ
    46. አቶ አየለ አናውጤ
    47. አቶ ሃብታሙ – የርዕሰ መስተዳድሩ ፕሮቶኮል
    48. ወ/ሮ ገነት ገ/እግዚአብሄር
    49. ወ/ሮ አበራሽ – በክልሉ ምክር ቤት የማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የነበረች ነባር ታጋይ
    50. አቶ ፈለቀ ተሰማ
    51. አቶ ጌታ ኪዳነ ማርያም
    52. አቶ ገሰሰው – ግብርና ሜካናይዜሽን ተመራማሪ
    53. አቶ ዳኜ – በጤና ቢሮ የሃይጅንና ሳኒቴሽን ባለሙያ
    54. አቶ ፈንታው አዋየው
    55. ወ/ሮ ዝማም አሰፋ
    56. ዶ/ር አምላኩ አስረስ
    57. አቶ ደጀኔ ምንልኩ
    58. ወ/ሮ ትልቅ ሰው ይታያል
    59. አቶ ላቀ አያሌው
    60. አቶ ባይህ ጥሩነህ
    61. አቶ ጥላሁን – የክልል ም/ቤት የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ
    62. አቶ ፍስሃ ወ/ሰንበት
    63. አቶ ጌታቸው – በት/ት ቢሮ የፈተና ኤክስፐርት
    64. ዶ/ር ይበልጣል ቢያድጌ
    65. አቶ አቃኔ አድማሱ
    66. አቶ የኔነህ ስመኝ
    67. ኮማንደር ሰይድ – የፖሊስ ኮሚሽን
    68. አቶ አስናቀ – በኢት. ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ኃላፊ
    69. አቶ ሙሉጌታ – ከግብርና ምርምር ኢንስቲቲዩት
    70. አቶ ባየ – ከልህቀት ማዕከል ኃላፊ
    71. አቶ አምባው አስረስ
    72. ወ/ሮ ወርቅሰሙ ማሞ

የአንድ ሕዝብ አንድ ሀገር ድርጅት ምንድን ነው? [አንዱዓለም ተፈራ  – የእስከመቼ አዘጋጅ]

$
0
0

ረቡዕ መስከረም ፲፰ ቀን ፳፻፱ ዓመተ ምህረት

ውድ ኢትዮጵያዊያን፤

ethiopia-675-satenaw-newsበፈረንጆቹ አቆጣጠር Sep. 18, 2016 አንድ ኢሜል ደረሰኝ። ሁለት መዝገቦችን አባሪ አድርጎ ነበር፤ አረንጓዴ ብጫ ቀይ ባሸበረቀ ምልክት፤ አንድ ሀገር አንድ ሕዝብ ከሚል ድርጅት። ሁለቱን በየተራ አነበብኳቸው። ወዲያው የበለጠ ለመረዳት፤ ከተወሰኑ ጥያቄዎች ጋር መልስ ላኩላቸው። ድምጻቸው ጠፋ። ቀጥለው ከአንድ ሳምንት በኋላ፤ አሁንም የጀምላ፤ “ድረገጻችን እይ!” ጥሪ ላኩልኝ። “ምነው መልስ ነፈጋችሁኝ!” በማለት መለስኩላቸው። ቀጥለው፤ “ያንተን ኢሜል አለገኝንም” ሲሉ መለሱልኝ። እድሜ ለቴክኖሎጂው ምጥቀት፤ በቀኗ የላኳትን ኢሜል ወደነሱ መራኋት። አይጥ እንደዋጠች ድመት፤ ድምጻቸውን አጠፉ። በዚህ ጥርጣሬዬ ላይ፤ በቫይቨር አንድ ቡድን ተፈጥሮ፤ የዚያ አባል ተደርጌ፤ ስልኬ በቫይቨር መልዕክት ይጣድፍ ገባ። “እንዴ! ይሄ የምን ቡድን ነው? እኔንስ ማነው ከዚህ ያስገባኝ?” ብዬ ላክሁ። መልስ የለም። እንዲህ ከሆነ አልኩና፤ “በሉ ያስገባችሁኝ ከማላውቀው ቡድን ስለሆነ፤ ያስገባኸን ሰው፤ ስልኬን ሰርዝ።” በማለት ጻፍኩ። ወይነሱ! ጉዳያቸውም አልሆነ። ሳገላብጥ፤ ያስገባኝን ስልክ ቁጥር አገኘሁ። ብዙም ጥረት የሚጠይቅ አልነበረም። ያንን ቁጥር በመጻፍ፤ “አንተ ሰው ስሜን ሰርዝ አልኩ።” ወይ ፍንክች! የስልኩን ባለቤት ስም አግኝቼ፤ ስሙንና የስልክ ቁጥሩን በማስፈር፤ “አንተ ሰው የስልክ ቁጥሬን ከዚህ የቡድን መልዕክት አውጣው!” አልኩት። ይሄን ሁሉ ያደረግሁት፤ እንደኔ ሌሎችም ተመሳሳይ ችግር አጋጥሟቸው ይሆናልና፤ እኔ ጥዬ በቀላሉ ከመሄድ፤ ምንአልባት ሌሎችም ይታዘቡት ይሆናል በማለት ነበር። በመጨረሻ ይህ ስም የስልኩ ባለቤት ሳይሆን፤ ስልኩን ከሁለት ዓመት በፊት ያስረከበውና ዛሬ ሌላ ስልክ የያዘ ሰው ስም ነው። ማለትም፤ በድሮ ባለቤቱ ስም፤ አሁን ተጠቃሚ በመሆን የወሰደ የድብቅ ድርጅት ስልክ ነው። የት እየሄደ እንደሆነ ገምቱ!

ዋናው ነገር፤ ይህ የተቀነባበረ፤ የፀረ-ትግሉ ቡድን ስልታዊ እርምጃ ነው። እኔ ከብዙዎቹ በተለየ መንገድ፤ በኢትዮጵያ ሀገራችን እየገዛ ያለውን የትግሬዎች ቡድን በጣም አደንቃለሁ። ይህ የትግሬዎች ቡድን ዓላማውን በደንብ ያውቃል። ለዚህ ዓላማው የማያደርገው ነገር የለም። ከዚህ ዓላማው ደግሞ ፍንክች አይልም። ዓላምውም አማራውን ከምደረ ገፅ ማጥፋትና ኢትዮጵያን መበታተን፤ ከዚያም የትግራይን ሪፑብሊክ ማቋቋም ነው። ይህን ለማድረግ የማያውጠነጥነው ሴራ፤ የማይደርተው ነገር የለም። እናም ጎበዝ ነው። ይህ ቡድን ይህን ሠራ፤ ያንን ደገመ ቢባል ደንታው አይደለም። አንዳንዶቻችን ዛሬ ይሄን ሠራ፣ ነገ ያን ደገመ ማለቱን ትግል አድርገን ይዘነዋል። ይህ ወራሪ ቡድን ግን ይስቃል። እኛ ምን እያደረግን ነው? የዚህን የአማራን ዘር አጥፊና ፀረ-ኢትዮጵያ ቡድን ተግባር መዘርዘር ላይ ተወዝፈናል።

እኔ ለዚህ ለደረሰኝ ኢሜል መልስ ስሠጥ፤ አንድ ነገር ይዤ ነው። ማንኛውም የሕዝብ ወገን የሆነ ድርጅት ሲልክልኝ፤ ምንም እንኳ መርኀ-ግብሩ ፍፁም የማልወደውም ቢሆን፤ የሕዝብ አካል ነውና፤ በጠቅላላ ሀገራዊ ትግሉ ይታቀፍ ዘንድ፤ ወደ አንድ እንድንካተት በማለት ነበር። ከዚህ በፊት፤ በትግሉ ያሉ ድርጅቶች በአንድነት እንዲሰባሰቡ ብዙ ሙከራ አድርጌያለሁ። አልተሳካልኝም። አሁንም ይህን ወራሪ ፀረ-ኢትዮጵያ አጥፊ ቡድን በአንድነት እስካልተነሳንበት ድረስ፤ ትግሉ ይራዘማል። ወደ ዋናው መልዕክቴ ልመለስ። ይህ የተላከልኝ ኢሜል – ለብዙዎቻችሁ ተልኮላችኋል – ሀገር ወዳድ የሚመስልና፤ ከአማራው ክፍል የወጣ የሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎችን ታሪክ ያላካተተ ከመሆኑም በላይ፤ ሌሎች አማራውን እንዲጠሉ “ይሄው የአማራው አደረጃጀት!” በማለት ይህ የትግሬዎቹ ገዥ ቡድን ለቀመረው ማቃቃሪያ ዘዴው፤ መረጃ እንዲሆን ነው። እናም የኢሜሎችን አድራሻዎች ከየትም ሰብስቦ፤ የስልክ ቁጥሮችን ለቃቅሞ ዶሴውን አዘጋጅቷል። ብዙዎቻችን ባለማወቅ መንገድ የዚህ ስብስብ አባል ተደርገናል። ተመከቱ፤ ይህ የትግሬዎች ገዥ ቡድን፤ የመንግሥታዊ መዋቅሩን ለሱ ዓላማ ሙሉ በሙሉ ሲያውለው! ይህ ለማንኛችንም አዲስ አይደለም። ነገር ግን፤ ዘዴው አዲስ ነው፤ ቢያንስ ለኔ።

እናም ለዚህ የትግሬዎች ቡድን አንዱ የትግል ማደናቀፊያ፤ ታጋዮችን መከፋፈል ነው። ይህ ድርጅት የተፈጠረው፤ ይህን በተግባር ላይ ለማዋል ነው። በሀገር ውስጥ አልሠራለትም። በሀገር ውስጥ ትግሉ በግልጽ ተቀምጧል። በውጪ ላለነው መንገድ አለው። አሁን በውጪ ባለነው ታጋዮች በኩል ሁለት ክፍሎች ዘልቀው ይታያሉ። የመጀመሪያው ክፍል፤ በእድሜ እንደኔ በገፋነውና፤ “ኢትዮጵያዊ ነኝ!” እያልን ባደግነው በኩል የሚቀነቀነው ነው። እኔ በንጉሰ ነገሥቱ ጊዜ፤ በዩኒቨርሲቲ ተማሪነትና በአስተማሪነት ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊነት ታግያለሁ። በደርግ ጊዜ ከጥንስሱ ጀምሮ እስከ ትጥቅ ትግል ድረስ፤ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊነት ታግያለሁ። ይህን የትግሬዎች ቡድንም ታጥቄ በጦርነት፤ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊነት ታግያለሁ። ይሄን ሁሉ ያደረግሁት በኢትዮጵያዊነቴና ለአንዲት ኢትዮጵያ ነበር። በዚህ ክፍል ያለነው በዚህ ዓላማ እንዳለን ነን። ከአርባ ዓመት ወዲህ ያሉትና የዛሬዎቹ ወጣቶች ደግሞ፤ ዛሬ በምድሯ ላይ ባለው የፖለቲካ ሀቅና፤ ዓይኑን አፍጥጦ ጎልቶ በመጣው ቅራኔ ተመስርተው፤ በትግሬዎቹ ገዥዎችና፤ እንዲጠፋ በፈረዱበት አማራ፤ በትግሬዎቹ ገዥዎችና በደሉ በበዛበት ኦሮሞ፣ አኝዋክ፤ ኦጋዴኒ፣ ወዘተ. ሆኗል። እኒህ ሁለት ክፍሎች፤ ማለትም ወጣቶቹና ቀደምተኞቹ፤ አንድ ጠላት አለን፤ የትግሬዎቹ ገዥዎች። እናም ባንድነት ብንሰለፍ የዚህን ወራሪ እድሜ ልናሳጥር እንችላለን። በመካከላችን ያለውን ክፍተት ለማስፋትና እርስ በርስ ለማባላት፤ ይህ ወራሪ የትግሬዎች ቡድን እየጣረ ነው። የግድ ይሄን ተገንዝበን፤ ተመካክረን ወደ አንድ ሰፈር መሰባሰብ ግዴታችን ነው። አንዳችን የሌላችን ጠላት አይደለንም።

በኔ በኩል እስከዛሬ በኢትዮጵያዊነት መታገሌ ትክክለኛና የምኮራበት ታሪኬ ነው። ይህ ከአርባ አምስት ዓመት በላይ የሆነው ትግሌ፤ በተጨባጩ የሀገራችን የፖለቲካ ሀቅ ተመርኩዤ የወሰድኩት የፖለቲካ ትግል ነበር። በሌላ በኩል ደግሞ፤ ምን ጊዜም ቢሆን፤ የፖለቲካ ትግል የትናንት አይደለም። የፖለቲካ ትግል እኛ እያንዳንዳችን ወይም በጥቅል በያዝነው እምነት ላይ አይመሠረትም። በኛ ፍላጎትም አይካሄድም። ምኞት ጥሩ ነው። ፍላጎት ጥሩ ነው። ምኞትና ፍላጎት ግን በመሬቱ ላይ ያለውን ሀቅ አይተኩም። የፖለቲካ ትግል በመሬቱ ባለው የፖለቲካ ሀቅ ላይ የተመሠረተ ነው። በሀገራችን ባለው የአሁን የፖለቲካ ሀቅ ላይ የተመሠረተ ትግል እንጂ፤ በኔ ጭንቅላት ወይንም ፍላጎት ላይ የተመሠርተ ትግል ዕርባና የለውም። ስለዚህ እኔ እስከዛሬ የነበረኝ አቋምና ያደረግሁት የፖለቲካ ትግል ትክክልነት እንደተጠበቀ ሆኖ፤ አሁን ግን፤ በሀገራችን ያለው ተጨባጭ የፖለቲካ ሀቅ፤ ሌላ ትግል ጠይቆኛል። አቤት ብየዋለሁ። በሀገራችን ያለው የፖለቲካ ሀቅ፤ የትግሬዎች የበላይነትና የአማራዎች እንዲጠፉ መደረግ፣ የትግሬዎች የበላይነትና የኦሮሞዎች መደቆስ፣ የትግሬዎች የበላይነትና የእኝዋክ ከቁጥር ውጪ መደረግ፣ የኦጋዴኑ መበደል ነው። እናም ትግሉ፤ “አማራ መሆኔ ለመጥፋት ከዳረገኝ፤ ለአማራነቴ፤ ለሕልውናዬ መታገል አለብኝ!” ሆኗል። ኦሮሞውም፤ አኝዋኩም፣ ኦጋዴኑም፣ በተመሳሳይ መንገድ።

አሁን በውስጤ፤ የፖለቲካ አማራ ተፈጥሯል። አማራነትን ፈልጌ ወይንም ኦሮሞነትን ጠልቼ አልተወለድኩም። ኢትዮጵያዊነቴን ስወለድ ያገኘሁት የፖለቲካ ማንነት ነበር። ያኔ ሌላ የፖለቲካ ማንነት አልነበረም። አማራነት በሰውነት ውስጥ የሚዘዋወረውን ደም መምጫ ተናገሪ እንጂ ሌላ ሚና አልነበረውም። አሁን ግን አማራነቴ የፖለቲካ ማንነት ሆኗል። ያን ወደድኩም ጠላሁም መቀበል፤ ግዴታዬ ሆኗል። ይሄ ለሁላችሁም ግልጽ ስለሆነ ማተቱ መደረት ነው። እኔም በአማራነቴ፣ የአማራውን ሕልውና ለመጠበቅ፤ አማራ ነኝ ብዬ ተነስቻለሁ። ለአማራው በአንድነት መነሳት እታገላለሁ። ለሃያ አምስት ዓመት ተዘርዝሮ የማያልቅ በደል የደረሰበት ወገኔ፤ ሕልውናውን ለመጠበቅ ትግል ላይ ነው። ያሁኖቹ ከአርባ ዓመት በታች ያሉት ወጣቶች የያዙት ትግል ይህ ነው። አሁን በሀገራችን ባለ የፖለቲካ ሀቅ የጎላ ቅራኔ ላይ የተመሠረተ! ለዚህ ሲታገሉ፤ ይህ የኔ ትግል ሆኗል። እስከዛሬ ኢትዮጵያዊያን ታጋዮች ወደ አንድ እንድንሰባሰብ ጥሬ ነበር። ዛሬ ትምህርት ወስጃለሁ። እኔ ስለፈለግሁ የሚሆን ነገር የለም። በቦታው ያሉ ታጋዮች ወሳኞቹ ናቸው። የወደፊቷ ኢትዮጵያ ዕድልና ዕጣ፤ በምናውቃቸው በውጪ ባሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ሳይሆን፤ በትግሉ በተሰማሩት የአማራ ወጣቶች፤ የኦሮሞ ወጣቶች፣ የአኝዋክ ወጣቶች እና አሁን በትግሉ በሀገራችን በተጠመዱት ታጋዮች እጅ ነው። አሁን የምጥረው፤ በአማራ ስም ተለያይተው የሚንቀሳቀሱ በውጪ ያሉ ታጋዮች፤ ወደ አንድ እንዲሰባሰቡ ነው። በጎን ደግሞ ሌሎችም ተሰባስበው በዚህ በወራሪ የትግሬዎች ቡድን ላይ እንዲነሱ ነው። ይህ በሀገራችን ላይ ያለው የፖለቲካ ሀቅ ግድ ያለው ነው። እኔ ሀቁን ተቀብዬ መታገል እንጂ፤ ራሴ በጭንቅላቴ ሀቅ ፈጥሬ፤ በዚያ ሀቅ መታገል አይደለም ሀገራዊና ታሪካዊ ግዴታዬ። ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ ከማንም ጋር ለመሥራት ዝግጁነቴን አብስሬ፤ ታታሪው የትግሬዎች ቡድን የሚያደርገውን አስተውለን መገንዘብ አለብን! እላለሁ። ገና ለገና ነገ በትግሬዎች ላይ አደጋ እንዳይደርስ ትግሬዎች ግራና ቀኝ አሁን በአማራው ላይ የግፍ ዶፍ ለሚያደርሱት ትግሬዎች ሲቆሙ፤ እኔ አማራ ነኝ የማልልበትና፤ ለአማራው እንዳልቆም የሚያግደኝ አእምሮ የለኝም። ዛሬ በአማራው ላይ ኢንተርሐውሜ እየተሰራ፤ ነገ በትግሬዎች እንዳይሠራ ብሎ መቆም መታወር ነው።

*ፋሲል ከነማ፡ እንደማንነት መገለጫ* (ዳዊት ግርማ)

$
0
0

fasil-kenema-satenaw-news
ፋሲል ከነማ (አጼዎቹ) ጎንደር ፋሲለደስ ኳስ-ሜዳ ላይ ከኢትዮጵያ መድን ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ0 በማሸነፍ አራት ጨዋታዎች እየቀሯቸው ነበር ወደፕሪሚየር ሊግ መግባታቸውን ያረጋገጡት፡፡ ፋሲል ጅማ አባ ቡናን 3ለ1 በማሸነፍ ደግሞ የከፍተኛ ሊጉ ቁንጮ ሆነው በዋንጫ ደምድመዋል፡፡ ፋሲል ከነማ አመቱን ሙሉ በከፍተኛ ሕዝባዊ መነሳሳትና ድጋፍ ሲደገፍ እንደነበረ እናስታውሳለን፡፡ ቡድኑ ኢትዮጵያ ውስጥ በክለብ ፍቅር፣ ከሜዳ ውጭም አብሮ በመጓዝ በከፍተኛ የደጋፊ ቁጥር ከሚደገፉ እግር ኳስ ቡድኖች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ የእግር ኳስ ቡድኑ በሃገር ውስጥና ውጭ የደጋፊዎች “የፌስቡክ ገጽ” ቅስቀሳ በማድረግ፣ መረጃዎችን ፈጥኖ በማድረስና የግጥሚያ ላይ ቀጥታ (ትኩስ) መረጃዎችን በየደቂቃው በማድረስ ተምሳሌትነት እንደነበረው ማንሳት ይቻላል፡፡ ከምንም በላይ ደግሞ ፈረንጆቹ  12ኛ ተጫዋች የሚሉት ደጋፊ ፋሲለደስ ላይ 12ኛና 13ኛ ሆኖ ተሰልፏል፡፡ የአንጋፋው ክለብ ደጋፊዎች ከተጫዋቾች ባልተናነሰ ተጫውተዋል፡፡ ቀይና ነጩን መለዮና የአንገት ፎጣ (ስካርፕ) በማድረግ ጎንደር ላይም ከጎንደር ውጭም ከቡድናቸው ጋር አብረው ተጉዘዋል፡፡ በጩኸታቸው የኢያሪኮን ግንብ እንደናጡት ቤተ አይሁድ፣ ፋሲሎችም በጩኸታቸው ተጋጣሚን በማርበድበድ፣ ተጫዋቾቹን በማነሳሳት ተአምር ሰርተዋል፡፡ ይሄ ሁነት የሚጨምር እንጂ የሚቀንስ እንደማይሆን ይጠበቃል፡፡ ከፋሲለደስ ከተማ ውጭ ያሉ ጎንደሬዎች፣ ከጎንደር ውጭም ያሉ አማራዎች ከአማራ ውጭም ያሉ ሌሎች ኳስ ወዳዶች በክለቡ ፍቅር ሲወድቁ እያየን ነውና፡፡

በመቀጠል ኳስን የማንነታቸው መገለጫ ያደረጉ ሃገራትን፣ በኳስ ቡድናቸው ማንነታቸውን ያወጁና የገለጹ ቡድኖችንና ማህበረሰቦችን፣ እና የኳስ ቡድኖችን ተያያዥ አለማቀፋዊ ታሪኮችን በማቅረብ የፋሲልን እውነታ በዚያ መለኪያነት ላቅርብ፡፡

** ኳስ እንደማንነት ማሳያ **

*ዓለም አቀፍ አውድ*

ማንነት የአንድን ተመሳሳይ ስነ ልቦናዊ ስሪት ያለው ሕዝብ ልዩ ልዩ እሴቶች ያቀፈ መገለጫ ነው፡፡ ማንነት የአንድ ማሕበረሰብ ማን እንደሆነ ማሳወቂያ፣ የእኔነቱ መገለጫ ነው፡፡ የማንነት ጽንሰሃሳብ ውስብስብና ገጸ-ብዙ ነው፡፡ ይህን ማንነት ግለሰቦች ከተለያዩ የባህል እሳቤዎች አንጻር በመቃኘት ይገልጹታል (Archetti, 1994)፡፡ እንደ Archetti  ገለጻ የእግር ኳስ ቡድኖች ማንነትን በመሳል ረገድ ሁነኛ ማሳያዎች ናቸው፡፡

እግር ኳስ የማንነታቸው መለኪያ የሆኑ በርካታ ሃገራትና ማኅበረሰባት አሉ፡፡ ብራዚል ውስጥ ኳስ ሁነኛ የሃገሬው መገለጫ ነው፡፡ ኳስ ብራዚል ሃገር ከጨዋታነት የዘለለ ትርጉም አለው፤ሁሉ ነገራቸው ነው ማለት ይቀላል፡፡ የአያሌ ብራዚላውያን ህጻናት ህልም “ስመጥር ኳስ ተጫዋች መሆን” ነው፡፡ ብራዚል የእግርኳስ ቱሪዝም መዳረሻ ሃገር ናት፡፡ ውብ የባህር ዳርቻዎቿን ከውብ ቆነጃጅቷ በተጨማሪ ህጻናት አሸዋ ላይ ኳስ ሰያንቀረቅቡ ትመለከቱባቸዋላችሁ፡፡ በርካታ የዓለማችን ታላላቅ እግር ኳስ ቡድኖች መልማዮች የታዳጊዎች ፕሮጄክቶችንና የሊግ ውድድሮችን በመታደም የወደፊቱን የኳስ ንጉስ ህጻን ቀድሞ ለመቅለብ ወደብራዚል ይጎርፋሉ፡፡ የአውሮፓ ኃያላን ክለቦች የታዳጊ ማሰልጠኛዎችን ብራዚል ውስጥ ከፍተዋል፡፡ እናም ኳስ ለብራዚል ከዋነኛ የእድገት ምንጮቿ ውስጥ አንዱ ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2007 ዓ.ም የወጣ መረጃ እንደሚጠቁመው በዓመት በአማካይ 100 ፕሮፌሽናል ተጫዋቾች በሽያጭ ከብራዚል ወደተለያዩ ክለቦች ያመራሉ፡፡ ከዚያም ረብጣ ዶላር ወደእናት ሃገር ይዘንባል፡፡ ኳስ ማንነት ነው- ብራዚል፡፡ ብሔራዊ መለዮም ነው፡፡

ፍራንሲስኮ ሪቻቲ `La Roma: Soccer and Identity in Rome` በሚለው መጣጥፉ የ20ኛው ክ/ዘ የሮም ታሪክ፣ ባህልና ማንነት ከዋናው ክለቧ ከኤ.ኤስ ሮማ ጋር እንደሚቆራኝ ይናገራል፡፡ የ“ሮማ” ቡድን በሮም ነዋሪ የለት-ተለት የህይወት እንቅስቃሴ ውስጥ ጉልህ ሚና  ይጫወታል ይላል፡፡ 48 በመቶው የሮም ህዝብ ሮማን ይደግፋል፤ 12 በመቶው ደግሞ ሌላኛውን የሮም ከተማ ክለብ ላዚዮን ሲደግፍ ቀሪው ደግሞ ለኳስ ደንታቢስ ነው የሚለው ሪቻቲ ደንታቢሱም ቢሆን በቤተሰቡ፣ በጓደኛው አሊያም በስራባልደረባው በኩል ሮማ ሕይወቱ ውስጥ አይጠፋም ይላል፡፡ እናም ሮማ የሮም መለያ ነው፡፡

ቤል (1994)፣ እንደሚለን እግር ኳስ በተለይ ከ19ኛው ክ/ዘመን ማብቂያ ጀምሮ በብሪታንያ ቁልፍ የማንነት መገለጫ ሆኗል፡፡ ለምሳሌ የካርዲፍ ከነማ እግር ኳስ ቡድን ዋነኛ የዌልስ ብሔራዊ ማንነት መፍጠሪያ፣ ማቀጣጠያና መገንቢያ ተደርጎ ይወሰዳል- እንደ ጆንስ (2000) ጥናት፡፡ ጋሪ ሮጀርስና ጆይል ሩክውድ “Cardiff City Football Club as a Vehicle to Promote Welsh National Identity” በሚለው ጥናታቸው እንደሚያስረግጡት በብዙኃኑ የዌልስ ዜጋ ዘንድ ካርዲፍ ከነማ ማለት “ዌልሳዊነት” ማለት ነው፡፡ በተለይ ደግሞ ከእንግሊዛዊ ማንነት የሚለዩበት ማኅበራዊ መለዮ ነው፡፡ ደጋፊዎች ይህን አባባል ያዘወትሩታል፡- “ከነማ (ካርዲፍ) ሲጫወት ስንመለከት ስለ ዌልስ እንዘምራለን” ይቀጥላሉ፡- “ባንዲራችን እንለብሳለን፤ እንግሊዛዊ ተቀናቃኞቻችንን በየሳምንቱ እንገጥማለን፤ ዌልሳዊ መሆናችንን እናፈቅራለን፤ ለዚህ ፍቅራችን ክለባችን ድምጽ ይሆነዋል፤ እናም ዌልሳዊነታችንን እንድናንጸባርቅ ይረዳናል”፡፡ አንዳንዶች “እንግሊዝ-ጠል ብሔርተኛ ተቋም” አድርገው አሉታዊ ምስል ሊያላብሱት ይሞክራሉ፡፡ በዚህ ረገድ ባሳለፍነው የአውሮፓ ዋንጫ ዌልሳዊው ጋሬት ቤል “እንግሊዛውያንን እንጠላቸዋለን” ብሌ የተናገረውንና ባንጻሩ እንግሊዛዊው ጃክ ዊልሼል ለቤል የሰነዘረውን የጥላቻ ጥላቻ መልስ ማስታወስ ይቻላል፡፡

መቀመጫው በሃገረ ዮርዳኖስ የሆነው አል ዊህዳድ የተባለው ክለብ የፍልስጤም ብሔርተኝነት ምልክት/መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ በዘመነ አፓርታይድ ጥቁር ያልተካተተበት ብሔራዊ ብድን ደ/አፍሪቃ ያበጀች ሲሆን፤ ጥቁሮቹ በበኩላቸው የነጻነት ትግሉ አካል የሆነ በተለይ ከነጻነትም በኋላ ዊሊ ማንዴላ የምትመራው የስፖርት ቡድን ነበር፡፡ ግብጽ ሃገር ውስጥ እግር ኳስና ፖለቲካ የተሳሰሩ ናቸው፡፡ ለአብነት ያህል ዝነኛው ቡድብ አል አህሊ የግብጽ ሕዝብ መለያ ሆኖ ነው የሚታየው። አል አህሊ በግብጻውያን በራሳቸው የተመሠረተው የመጀመሪያው ክለብ ሲሆን የግብጽ ብሔራዊ መለያ ነው። የየቡድኖቹ ደጋፊዎች በአገሪቱ ፖለቲካ ላይ ትልቅ ሚና ያላቸው ሲሆን ስታዲዮሞችም ብሶትን ለመግለጽ አመቺ ቦታዎች ናቸው።

በስፔን እግር ኳስና ፖለቲካ የማይለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ በተለይ ደግሞ ዋና ዋናዎቹ ፕሮፌሽናል ቡድኖች ከተመሰረቱበት ከ19ኛው ክ/ዘመን መገባደጃ ወዲህ፡፡ ስፔናዊው አምባገነን ፍራንሲስኮ ፍራንኮ (1936-1975 እ.ኤ.አ) በ1950ዎቹ በዓለምአቀፉ መድረክ አዎንታዊ ገጽታን ለመገንባት እግር ኳስን እንደሁነኛ መሳሪያ ተገልግሎበታል፡፡ አዲሲቷንና ማዕከላዊቷን የተረጋጋች ስፔን በዓለም ለማስተዋወቅ ትልቁን የአገሪቷን ቡድን ሪያል ማድሪድን እንደመሳርያ ተጠቀመ፡፡ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ በ1956 ሲጀመር፣ ማድሪድም ለአምስት ተከታታይ ጊዜ አሸናፊ ሆኖ በአውሮፓ ሲነግሥ፣ ጄኔራል ፍራንኮ የሎስ ብላንኮዎቹ መደበኛ ተመልካችና የቅርብ ደጋፊ በመሆን ረብጣ የፖለቲካ ትርፍ ሊሸምት ችሏል፡፡ ማድሪድም የስፔን ብሔራዊ ማንነት ማሳያና መለኪያ ሆኖ እስከ ዘመናችን ገሰገሰ፡፡ የማንነት ጥያቄን ፖለቲካ አላብሶ በእግር ኳስ ሜዳ በማንጸባረቅ ወደር እንደማይገኝለት የሚነገርለት የካታሎን ተገንጣዮች ተወካይ ባርሴሎና ከዚህ በተጻራሪ ቀጥሎ ይመጣል፡፡ የካታሎኒያ ብሔርተኝነት ማሳያው ባርሴሎና በፍራንኮ ፈላጭ ቆራጭ ዱላ ተደቁሷል፡፡ ቡድኑም የብሔርተኝነት ንቅናቄውና የጸረ-ፍራንኮ ትግል ዋነኛ ማዕከል ሆነ፡፡ በፍጹም ራሳቸውን ስፔናዊ አድርገው የማይቆጥሩት የካታሎን ተገንጣዮች ከስፔን የተለየ ማንነትን ለማራመድና ተገንጥለው ነጻ የካታሎን መንግስት ለመመስረት ያላቸውን ህልም ለማሳካት በባርሴሎና እግር ኳስ ቡድን በኩል ብዙ ተጉዘዋል፡፡ ባርሳም የዚህ ፖለቲካዊ ውዝግብ ትልቅ ባለድርሻና “ሲምቦል” ነው፡፡ በተለይ የሊጉ ጠንካራዎቹ ክለቦች የስፔን ብሔራዊ ማንነት ማሳያ ተደርጎ የሚወሰደው ሪያል ማድሪድና የመገንጠል ጥያቄ አንጋቢዋ ካታሎን ግዛት ተወካዩ ባርሴሎና ቡድኖች ሲጫወቱ (ኤል-ክላሲኮ)፣ ከ“ደርቢ” ጨዋታ ተቀናቃኝነት በላይ፣ ጦር የተማዘዙ ሁለት ሉዓላዊ ባላንጣ ሃገራት የሚያደርጉት ፍልሚ እስኪመስል ድረስ ከኳስ ጨዋታነቱ ይልቅ የፖለቲካ ድባቡ ያመዝናል፡፡

በስፔን የብሔራዊ አንድነት አቀንቃኞች አማካኝነት በካታሎኗ ባርሴሎና ከተማ እንደተመሰረተ የሚነገርለት ስፓኞል እግር ኳስ ቡድንም ከስሙ ጀምሮ በስፔን ብሔርተኝነት መንፈስ የተቃኘ የባርሴሎና ቡድን የከተማ ተቀናቃኝ ነው፡፡ ይህም በስፔን ያለ የኳስና ማንነት መስተጋብር ሌላ ማሳያ ነው፡፡ ሌላው የስፔን ላሊጋ ተሳታፊ ቡድን የባስክ ተገንጣዮቹ አትሌቲኮ ቢልባኦም በባርሴሎና አንጻር የሚቀመጥ ነው፡፡ እነዚህ የሁለት ነጻነት ጠያቂ ክፍላተ ሃገራት ካታሎኒያና ባስክ ክለቦች ባርሳና ቢልባኦ በማኅበረሰባቸው ዘንድ ከእግር ኳስ ቡድንም በላይ ስዕል ነው ያላቸው፤ እንደብሔራዊ ቡድንም ይቆጥሯቸዋል፡፡ ለዛም ነው “የስፔንን እግር ኳስ ከፖለቲካዋ ነጥሎ ማየት አይቻልም” የሚለው አባባል ግዘፍ የሚነሳው፡፡

*የእኛ አገር አውድ*

ብራድሊ (1995) እንደሚለው የእግርኳስ ደጋፊዎች የቡድናቸውን ድል በመመልከት ጉልህ የሆነ ስነልቦናው ርካታ ያገኛሉ፡፡ ደጋፊነት ከስፖርታዊ አውድ ውጭም በህብረተሰቡ የለትተለት ኑሮ ውስጥ ስፍራ አለው፡፡ ይህም ማኀበራዊ ድርጊቶች፣ ሚዲያ ሽፋኖች፣ መለዮዎችን በመልበስ፣ የክለባቸውን መዝሙር በመዘመር፣ ምልክቶችን በማድረግ ታሪካቸውንና የቀንከቀን እውነታዎቻቸውን በማንጸባረቅ ይገለጻል ይለናል፡፡

ወደሃገራችን ስንመጣ ስፖርት ዘርፈ ብዙ የማንነት መወከያ ሆኖ ሲያገለግል አይተናል፡፡ ሩጫ የብሔራዊ ማንነታችን መገለጫ ሲሆን፤ የክለብ እግር ኳስ ደግሞ የተለያዩ ቡድኖችን አላማ ማራመጃነት ሲውል ነበር፡፡ በተለይ በ1960ዎቹና 70ዎቹ የነበሩ የአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ አስመራ፣ ሻሼመኔ፣ ጎንደርና ጅማ ላይ የተቋቋሙ ህዝባዊ መሰረት ያላቸው ክለቦች የፖለቲካ ማንነት ማራመጃ ነበሩ፡፡ ገነነ መኩሪያ ኢህአፓና ስፖርት በተባለው ባለሁለት ቅጽ መጽሐፉ 60ዎቹ መጨረሻና 70ዎቹ መጀመሪያ ላይ የነበሩ የሊግ ክለቦች ዋነኛ የኢህአፓ አላማ ማቀንቀኛ እንደነበሩ ይናገራል፡፡ ህዝባዊነት ያላቸው እንደ “አንድነት”፣ “ቅዱስ ጊዮርጊስ”፣ “ቴዎድሮስ” እና “ምድር ባቡር” (ድሬዳዋ)፣ መሰል ክለቦች ኢሃፓን ደግፎ ደርግን መንቀፊያ ነበሩ፡፡ ኢህአፓም ከህቡዕነት ግዘፍ እስከመንሳት ድረስ በክለቦቹ ውስጥ እጇ ረዥም ነበር፡፡ የኢህአፓ አባላት የነበሩና ፖለቲካውን ከልባቸው የሚያንቀሳቅሱ ተጫዋቾች ነበሩባቸው፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዘመነ ወያኔም የደርግ ጊዜውን ያክል ጠንካራና የተደራጀ ባይሆንም አልፎ አልፎ ፖለቲካዊ ተቃውሞዎች በአዲስ አበባ ስታዲዮምና በትንሹ ደግሞ በክፍለ ሃገር የኳስ ትዕይንቶች ላይ (ባለፈው ዓመት የጎንደር ፋሲለደስ ስታዲዮም የ“ወልቃይት አማራ ነው” የማንነት ጥያቄና በአጸፋው አዲግራት ላይ የፋሲል ደጋፊዎች ላይ ነውጠኛ ደጋፊዎች የወሰዱት ጠብ-አጫሪ ርምጃ እንዳብነት ሊጠቀስ ይችላል) ሲንጸባረቅ ይስተዋላል፡፡ “ሳንፈልጋቸው 20 ዓመታቸው” የሚለውን የሚስማር ተራ ህብረ ዝማሬ በዚህ ረገድ ማውሳት ይቻላል፡፡

ዐማራና ስፖርት

በኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ የዐማራ ህዝብ ያለ ተወካይ ለረዥም ዓመታት መቆየቱ ይታወቃል፡፡ ደሴ ጥቁር አባይ በአንድ ወቅት ብቅ ብሎ ጠፋ፤ ወልድያ ከነማ በ2007 ዓ.ም የውድድር ዘመን ደርሶ ተመለሰ፡፡ አምና በ2008 ዓ.ም ወደዋናው ሊግ ለመግባት በተደረገው ውድድር በከፍተኛ ሊግ ከቀጠና አንድ ፋሲል ከነማና ወልድያ ከነማ ሁለቱንም ኮታዎች በመጠቅለል አላፊ ሆነዋል፡፡ በዚህም በ2009 የውድድር ዓመት ሁለት ቡድኖች ዐማራን ይወክላሉ፡፡ እነዚህ ሁለት ቡድኖች የዐማራ ብሔርተኝነት ማነቃቂ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የዚህን ህዝብ ከኳስ መድረክ ለዘመናት ርቆ መቆየት ገዢው መንግስት ይህንን ህዝብ ለማጥፋት ከሚያራምደው እኩይ አጀንዳ ጋር አመሳስለዋለሁ፡፡ በ25ዓመታት ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዐማራዎችን የፈጀው የደደቢቱ መንግስት፣ የዚህን ህዝብ የበላይነት ከሚቀለብስባቸው መንገዶች አንዱ ስፖርት እንደሆነ ከግምት የዘለለ እውነታ ነው፡፡ እንደኦሮምያ ለሩጫ አመቺ የሆነ የአየር ንብረትና መልክዓምድራዊ አቀማመጥ ዐማራ ውስጥ አለ፤ በተለይ ሸዋና ጎጃም አካባቢ፡፡ ከነዚህ አካባቢዎች የተገኙ ጎበዝ አትሌቶችንም ታዝበናል፡፡ አገር አቀፍ ውድድሮች ላይ ውጣ ውረዶችን ተሻግረው በውድድር ሲሳተፉ ከዚያም በጎ ውጤት ሲያስመዘግቡ አይተናል፡፡ በዓለም አቀፍ መድረክ ግን አናያቸውም፡፡ ለምን? መጠርጠር ጥሩ ነው፡፡ በርግጥ ከጫካ የወጣው ገዢ ቡድን የዐማራ ህዝብ ላይ ጫካ ውስጥ ሆኖ ካረቀቀው የቂም በቀል ፖሊሲ አንጻር ስንቃኘው ጥርጣሬው ውሃ ያነሳል፡፡ ሊደረግላቸው የሚገባውን ድጋፍና ክትትል ብንተወው እንኳ በግላቸው ጥረት መሰናክሉን አልፈው እንዲወዳደሩ በሩ ቢከፈትላቸው ከነ“ገብሬ” ያነሰ “ፐርፎርም” እንደማያደርጉ አምናለሁ፡፡ ከክልሉ በጥረት የወጡ አትሌቶች ዐማራ በመሆናቸው ምን ያክል እንደሚገለሉና እንደሚገፉ ከአትሌቶቹ ጋር በቅርበት ተወያይቶ ያጫወተኝ የስፖርት ጋዜጠኛ ወዳጄ ለዚህ እማኜ ነው፡፡ እግር ኳሱም ከዚህ የተለየ ዕጣ የለውም፡፡ ስፖርት አንድን ህዝብ ለማስተዋወቅና ጥሩ ገጽታ ለማጎናጸፍ መልካሙ መንገድ መሆኑ እሙን ነው፡፡ በተለይ የሊግ ኳስ ከላይ በዓለም ዐቀፍ አውድ እንዳየነው አንድን ማህበረሰብ፣ ዘውግ፣ ተመሳሳይ ስነ ልቦናዊ ስሪት ያለው ህዝብ፣ ከተማ የመወከልና የማስተዋወቅ እድሉ ከፍተኛ ስለሆነ ሴረኛው መንግስት በዚህ በኩልም ሲደቁሰን እንደኖረ እናምናለን፡፡ እነ ይድነቃቸው ተሰማና መንግስቱ ወርቁን የመሰሉ ብርቅ የአገራችንና የአፍሪካ የእግር ኳስ ምልክቶች የወጡበት ህዝብ ለምን ያለ ተወካይ ሊቀር ቻለ? እውነቱ ከጥያቄው መልስ ውስጥ አለ፡፡ አሁን ፋሲልና ወልድያ ከዚህ ፍቱን መጠይቅ ጀርባ ያለውን ደባ እየሸረሸሩ በስፖርቱ መድረክ ገነው፣ ህዝባቸውን ከጎናቸው በማሰለፍ ብሄርተኝነትን እያቀነቀኑ፣ ፖለቲካዊና ህዝባዊ ጥያቄዎች እየተስተጋቡባቸው ይቀጥላሉ፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዋነኛ ዓላማ ፋሲል ከነማን በዚህ ነጥብ ረገድ መዳሰስ ነውና ወደዚያው ልለፍ፡፡

የፋሲል ከተማ

ምንም እንኳን በዚህ ዓመት ወደስኬት ይምጣ እንጂ ፋሲል ብዙ አስርተ አመታት ያስቆጠረ ታሪክ አለው፡፡ ጠንካራ ህዝባዊ መሰረትም አለው፡፡ በተጫዋቾች ትጋት፣ በደጋፊው ደጀንነት፣ ዓመቱን በስኬት አጠናቋል፡፡ የፋሲል የአምና ጉዞ ከስፖርትነት ባለፈ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች የተስተናገዱበት ክዋኔ ነበረው፡፡ በዓለም መድረክ ላይ እንዳየነው እግር ኳስ የተለያዩ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ሌሎች እሳቤዎችና ጥያቄዎች የሚስተናገዱበት መድረክ ነው፡፡ ፍቅርንም ጥላቻንም ማስተናገድ ይቻላል፡፡ በአንድ ወቅት የኢራን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት አፍሺህን እግር ኳስ ህዝብን ለማስተሳሰር ያለውን ጉልበት ሲናገሩ “ዓለምን ወደአንድ ለማምጣት ሁለት ነገሮች ያስፈጋሉ- ፍቅርና እግር ኳስ” ብለው ነበር፡፡ ለዛም ነው በስፖርታዊ መድረኮች ህዝባዊ ጥያቄዎችን ማንሳት የተለመደ የሆነው፡፡

ዘንድሮ ፋሲል ወደፕሪሚየር ሊግ መግባቱን ተከትሎ ድጋፉ እንደሚግል ይጠበቃል፡፡ የተቀጣጠለው የዓማራ ብሔርተኝነትም ሆነ ህዝባዊና ፖለቲካዊ ጥያቄዎች በተደራጀ መልኩ ይቀርቡበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ፋሲል ከክለብም በላይ ነው፡፡ ከላይ ባርሴሎና ክለብ ብቻ አይደለም እንደተባለው፤ የማንነት መጠየቂያ መድረክም እንጂ፡፡ እናም ፋሲል የዓማራነት መወከያ ነው፤ የተገፋ ህዝብ ጋሻ፤ የተንቋሸሸ ታሪክና ማንነት መመለሻና ማደሻ፡፡ ይህ ዓማራዊ ማንነትና ብሶት በደጋፊዎቹ ይዘመራል፤ ፋሲል በደጋፊ መሰረት ላይ የታነጸ ክለብ ነውና፡፡ እንደኛ ሃገሩ ቡና እና እንደአውሮፓ ታላላቅ ቡድኖች የደጋፊ ልዩነት ፈጣሪነት ፋሲል ላይ ግዘፍ ይነሳል፡፡ ህዝባዊ እምቢተኝነትና ፋሲል ከነማ ጎን ለጎን የሚሄዱ ሁነቶች ናቸው፡፡ ፋሲል የጎንደር ክለብ ነው፤ ጎንደር- የዐማራ ተጋድሎ የተጠነሰሰባትና የተቀጣጠለባት ምድር ናት! በተዋህዶ የከበረች ምድር፤ አንድም በጀግንነት አንድም በጨዋነት- በተዋህዶ መክበር የምልህ ይሄንን ነው፡፡ ጀግንነት ብትል መፈጠሪያው ጎንደር፤ እንግዲያስ ጨዋነት (ማተብ ይልሃል! ሃቀኝነት- ሰው አክባሪነት፣ እንግዳ ወዳድነት፣ አዛኝነት)፡፡ ይሄንን እንግዲህ በኳሱ መድረክ አብረን የምናየው ይሆናል፡፡ ኳስ የበሬ ግንባር በምታክል ሜዳ ቅሪላ ከማንከባለል የዘለለ ነው የሚባለውም ለዛ ነው፡፡ የገሃዱ ዓለም እውነት ነው፡፡ ኳስ የዓለምን ቢዝነስ ይመራል፣ የዓለምን ፖለቲካ ይመራል፣ የዓለማችንን ሁሉ ነገር በቅጽበት መቀየር የሚችሉ አቋማሪዎችና ማፍያዎች ኳሱ ውስጥ አሉ፡፡

አሁን በዘመነ ደደቢት ዐማራነት በራሱ ፖለቲካ ሆኗል፡፡ ቀሪዋ ኢትዮጵያ በገዢዎች አምባገነናዊ ዱላ ስትመታ ዐማራ ግን ከዚህም ያልፍና በዘሩ ብቻ ደደቢት በርሃ ውስጥ በተነገፈለት የበቀል አጀንዳ ላለፉት 40 ዓመታት (በይበልጥ 25 ዓመታት) የሚገደል፣ የሚሳደድ፣ በድህነት ውስጥ ይኖር ዘንድ የተፈረደበት፣ በስነ ልቦና የሚመታ፣ ትምህርት/ጤና/መሰረተ ልማቶች የተነፈጉት፣ የሚሰደብ፣ የዘር ማጥፋት የታወጀበት ህዝብ ሆኗል፡፡ ይህም የሚሆነው ዐማራ ስለሆነ ብቻና ብቻ ነው፡፡ እናም የዐማራነት ጥያቄ የመኖር-አለመኖር ጥያቄ ነው፤ የህልውና ጥያቄ፡፡ ይህን ለመዋጋት የዐማራ ብሔርተኝነት ወሳኙ መንገድ ሲሆን ንቃተ ህሊና ደግሞ መንገዱን ይጠርጋል፡፡ ለዚህም መድረኮች ያስፈልጉናል፡፡ በማኅበራዊ ሚዲያው፣ በቡድን ውይይት፣ በመደራጀት፣ በ“አክቲቪዝም” እና ሌሎች መንገዶች ከሚደረገው የንቃተ ህሊና ማዳበሪያ መድረኮች በተጨማሪ ኳስ (ስፖርት) አንዱ ሆኖ ይቀርባል ማለት ነው፡፡ ይህን ንቃተ ህሊና የሚፈጠርበት፣ የሚሟሟቅበት፣ የሚዳብርበት መድረክ ይሆናል- ፋሲል ከነማ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም በሁሉም መድረኮች ዐማራ ስም አጠራር እንዳይኖረው ላለፉት 25 ዓመታት እየተጋ ያለው ስርዓት ካቅሙ በላይ በሆነ ህዝባዊ መነሳሳትና ወኔ ፋሲል ፕሪሚየር ሊጉን መቀላቀሉ ደደቢቶቹን ውስጥ ውስጡን እርር ድብን እንዳደረጋቸው መገመት ቀላል ነው፡፡ በተለይ ፋሲልና ወልድያ የሰሜን ተወካዮችን ከስር ጥለው መምጣታቸው ንዴታቸውን ሊያንረው ይችላል፡፡ እናም እነዚህ የዐማራ ተወካዮች በመጡበት አግራቸው ተመልሰው እንዲወርዱ “ፕሮፌሽናል” ሴራ ሊያሴሩ ይችላሉ፤ ከዳኝነት እስከ ፌዴሬሽን ቢሮክራሲ፡፡ ስለሆነም ይህንን ጉዳይ ነቅቶ መከታተል ክለቦቹን ከመደገፍ ጋር ጎን ለጎን ትኩረት ሊቸረው የሚገባ አቢይ ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ጽሑፍ/እይታ ፋሲል ከነማን ማዕከል አርጎ ይጻፍ እንጂ በተመሳሳይ ወልድያ ከነማንም ይወክላል፡፡ እነዚህ ሁለት ቡድኖች የዐማራ ብሔርተኝነት ማቀጣጠያ ሆነው ከዐማራነት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች የሚነሰሱባቸው መድረኮች ይሆኑ ዘንድ ይጠበቃል፡፡ ፋሲልና ወልድያ ማንነታችን ያነጥሩልናል፤ ታሪካችንን መልሰው፣ ውለታችንን አወራርደው፣ ወደሰገነታችን ያወጡናል፡፡ በሰላማዊው መድረክ ዐማራ ይነግሳል፡፡ ፋሲልና ወልድያ የዐማራ ባርሴሎናዎች ሊሆኑ እንደሚችሉ ይጠበቃል፡፡

ቸር ያሰማን!

ስኬት ለፋሲልና ወልድያ ከነማ!

ኢሳት አምስተርዳም- የዕለቱ ዜና

$
0
0

ኢሳት አምስተርዳም- የዕለቱ ዜና

Esat - Satenaw

አቶ ገዱ ለምን አለቀሱ? ሀገር በደምና በአጥንት እንጅ በእምባ አልተገነባችም (ከይገርማል)

$
0
0

gedu-andargachew-satenaw-news-b-78

የሰው ልጅ እንባ በተለያየ ምክንያት ሊፈስ ይችላል:: የአይን ህመም ያለባቸው ሰዎች እንባ የመቋጠር ችግር ሊያጋጥማቸው ይችላል:: ጤነኛ አይን ያላቸውም ቢሆኑ በተለያየ ምክንያት እንባ ሊያፈሱ ይችላሉ:: በሀዘን የተነሳ ይለቀሳል: በእልህና በብስጭትም እንዲሁ እምባ ገደቡን አልፎ ሊፈስ ይችላል:: አንዳንድ ሰዎች የሆነ ነገር ላይ አትኩረው ሲያዩ አይናቸው እንባ ይቋጥራል:: ከልብ ፍርስ ብለው የሚስቁ ሰዎች አይናቸው እንባ የሚያቁርበት ጊዜ አለ:: እምባ በደስታም በመከራም: በጨዋታም በቁምነገርም በጉንጭ ኮለል እያለ ወርዶ ደረትን ያርሳል:: ተዋናያን የወከሉትን ገጸባህሪ ተላብሰው በሚያስቀው ሲስቁ በሚያስለቅሰው ስቅስቅ ብለው ሲያለቅሱ ስናይ እነርሱን ተከትለን በሳቃቸው ተደስተን የምንስቅ የውሸት ሀዘናቸው ተጋብቶብን በለቅሶ የምንንሰፈሰፍ ብዙወች እንኖራለን:: ልቅሶ ውስጣዊ ብሶትን ማስተንፈሻ: የደስታም ይሁን የሀዘን ስሜት መግለጫ: የውሸትም የእውነትም እምባ የሚፈስበት ሊሆን ይችላል::

በአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም (አብቁተ) የስብሰባ አዳራሽ የባሕርዳር ወጣቶችን ሰብስበው በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያነጋገሩት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከወጣቶች  በቀረቡላቸው ጥያቄወች ምክንያት እንዳለቀሱ ከተለያዩ ድረገጾች አነበብን:: የአቶ ገዱ ልቅሶ ከምን የመነጨ ነው?

የአማራ ወጣቶች የወያኔን አፈናና መከራ ከምንም ሳይቆጥሩ በድፍረት ያቀረቧቸው ጥያቄወችና የሰነዘሯቸው አስተያየቶች ከደርግ የቀይ ሽብር ጀምሮ በኢትዮጵያ ላይ የወረደውን አፍዝ አደንግዝ የሰበረውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት የሚያጠናክር የዘመኑን ወጣት ቁርጠኛነት ያበሰረ የለውጥ ድምጽ ነው:: የአባቶችን ለጠላት ያለመንበርከክ ባህሪና የሀገር ፍቅሩን ተላብሰው ኢትዮጵያን ወደነበረችበት የክብር ማማ ለመመለስ በቁጭት የተነሱ መሆናቸውን የሚያሳይ የጽናት መገለጫ ነው:: ይህን በትግሬ ወያኔወች የከፋፍለህና የአደህይተህ ግዛ ዘረኛ ፖሊሲ የተማረረ ወጣት በተራ ሽንገላና በቃላት ጨዋታ አቋሙን እንዲቀይር ወይም እንዲያፈገፍግ ማድረግ የሚቻል አይደለም:: የአማራ ወጣቶች በወያኔ ጠላት ተብሎ ከተፈረጀው አብራክ የተገኙ በዘር ማጥፋት ፖሊሲ የግፍ ሰለባ የሆነው የመከረኛው የአማራ ልጆች ናቸው::

ወያኔ ስልጣን ላይ ከወጣ ጀምሮ በአማሮች ላይ የደረሰው መከራ በቃላት ሊገለጽ ከሚችለው በላይ ዘግናኝ ነው:: በአንድ ወቅት ጎበዛዝትና ቆነጃጅት ሆነው የሀገርን ዳርድንበርና የሕዝብን አንድነት በደምና በአጥንታቸው ያስከበሩ ያሁኑ አዛውንቶችና አሮጊቶች በጡረታ ጊዜያቸው “ኧሁ!” ብለው ሊያርፉ እድሉን አላገኙም:: ጡት ጠብተው ያልጠገቡ ሕጻናት ሳይቀሩ ከወላጆቻቸው እቅፍ ላይ አሸልበው በሰላም ለመነሳት አልታደሉም:: ወያኔ በፈጠረው ዘረኝነት የተነሳ ትንሽ ትልቅ ሳይል ለማየትም ሆነ ለመስማት በሚከብድ ግፍ አማራ በመሆናቸው ብቻ እጅግ ብዙ አማሮች ታርደዋል:: የዘር ምንጠራው አሁንም ቢሆን አልተገታም::

ወጣቶች:- ማየት ለተሳናቸው የአይን ብርሀን: ለደከሙት ምርኩዝ: ተስፋ ለራቃቸው ተስፋ: ለተጠቁት ደምመላሽ: ለወገንና ለሀገር አለኝታወች ናቸው:: የወገናቸው ሰቆቃ እረፍት  የነሳቸው የአማራ ወጣቶች ጸረ-ሕዝብና ጸረ-ሀገር የሆነውን ወያኔን ተፋልመው በማስወገድ ህዝባዊ ስርአት ሊያሰፍኑ በእልህ ተነስተዋል:: ለአቶ ገዱ ያቀረቧቸው ጥያቄወች የሚያመለክቱት ህዝባቸውንና ሀገራቸውን ለመታደግ ማንኛውንም መስዋእትነት ለመክፈል ግምባራቸውን የማያጥፉ ቁርጠኛ መሆናቸውን ነው:: አቶ ገዱና ድርጅታቸው ይህን የወጣቱን የቁጭት መነሳሳት የሚደግፉት እንዴት ነው?

በጎንደርና በጎጃም አካባቢ ጸረ-ትግሬ እንቅስቃሴ እየተቀጣጠለ ነው በማለት ትግሬ የሆኑት ሁሉ በወታደር ታጅበው በክብር በአውሮፕላንና በመኪና ሲጓጓዙ አይተናል:: ተፈናቀሉ ለተባሉት ትግሬወች የመቋቋሚያ ብር ከየክልሎች በገፍ እየፈሰሰ እንደሆነ እየሰማን ነው:: የአማራ ክልል ንብረታቸው ለወደመባቸው ካሳ ለመክፈል ቃል ገብቷል:: በየአካባቢው ወድቀው ለቀሩት አማራ  ወገኖቻችን የህሊና ጸሎት እንኳ ተደርጎላቸው ያውቃል? አማሮች ሰው አይደሉም? ሀብት ንብረት ለወደመባቸው ካሳ የከፈላቸው መቋቋሚያ የለገሳቸው አለ? ሌላው ቀርቶ አማራን እወክላለሁ የሚለው ብአዴን እንኳ የጥፋት ተባባሪና ሽፋን ሰጭ ሆኖ ከማገልገል ውጪ የአማሮችን ጩኸት ሲጮህ መከራቸውን ሲጋራ ታይቷል?

ግን አቶ ገዱ ለምን አለቀሱ? በፍርሀት ምክንያት ነው ያለቀሱት እንዳይባል አማራን የሚያህል ሕዝብ ይዞ መፍራት ትርጉም የሚሰጥ አይደለም:: አማራው ሲፈጥረው ወታደር ነው:: አባቶቻችን አለምን ጉድ ያሰኙ ገድሎች የፈጸሙት ዘመናዊ የውትድርና ትምህርት ስለነበራቸው ወይም ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቁ ስለነበሩ አይደለም:: የአማራው የአሸናፊነት ሚስጥር ልበ-ሙሉነቱ ነው: ጀግንነቱ ነው:: ይህን ህዝብ እየመራሁ ነኝ የሚል ሰው የህወሀትን ሀይል ፈርቶ የሚያለቅስ አይሆንም:: ልቅሷቸው የወጣቶችን የትግል ወኔ በመረዳት ከተሰማቸው ደስታ የመነጨ ከሆነ አማራን ከጥፋት ለመታደግ እየተሰሩ ባሉ ስራወች በሚያበርክቱት ድርሻ ወደፊት በተግባር የምናያቸው ይሆናል:: ብአዴን እስከቀበሌ ድረስ ያለውን አደረጃጀቱን ተጠቅሞ የአማራው ሕዝብ ተደራጅቶና ታጥቆ መብቱን እንዲያስከብር የበኩሉን እገዛ ሲያደርግ ያን ጊዜ የአቶ ደጉ እምባ የብሩህ ተስፋ አብሳሪ: የአንድነትና የመከባበር ቡቃያ አብቃይ ጠል (ዝናብ) ነው ማለት እንችላለን:: ከዚያ ውጭ የአማራ ክልል ፕሬዚደንት ነኝ ተብሎ ተቀምጦ እወክለዋለሁ የሚለው ሕዝብ በዘረኛ ቡድን ሲሰቃይ እያየ  እጅን አጣጥፎ ቁጭ ብሎ ሀዘንን በዘለላ እምባና በከንፈር መጠጣ መግለጽ የሕዝብ ልጅነትን: የወገን ተቆርቋሪነትን የሚያሳይ አይሆንም::

እንደሚሰማው ከሆነ አብዛኛው የብአዴን የታችኛውና የመካከለኛው አመራር በሕዝቡ ላይ የሚደርሰውን ግፍ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ የስርአቱ አራማጅ የሆነውን ወያኔን እና አስከፊ አገዛዙን የሚጠላ እንደሆነ ነው:: ይህ ማለት ከሕዝቡ ጋር ተቀራርቦ የሚሰራው አመራር የወያኔ ስርአት እንዲያበቃ ከሚፈልጉት ወገኖች መሀል የሚደመር ነው ማለት ነው:: ታዲያ ይህን አመራር በአግባቡ ከተጠቀምንበት ህዝቡን የማንቃት: የማደራጀት: መሰረታዊ የወታደራዊ ስልጠና የመስጠት: የማስታጠቅና ራሱን ለመከላከል የሚያስችል የውጊያ ሞራሉን የመገንባት ስራው  በቀላሉ ሊሰራ ይችላል ማለት ነው:: ከላይ ያለው አመራር  ያለመካከለኛውና ያለታችኛው አመራር ሊሰራው የሚችል ምንም ነገር አይኖርም:: አማራውን ከፈጽሞ ጥፋት ለመታደግ ስንነሳ መስዋእትነት አይኖርም ማለት አይደለም:: የሚከፈለው መስዋእትነት እጅና እግርን አጥፈን ተቀምጠን ሞትን በጸጋ የምንቀበልበት ሳይሆን ገድለን የምንሞትበት ስለሚሆን ገዳያችን ከመናቅ ወደማክበር: ከመድፈር ወደመፍራት: ከትእቢት ወደአስቦ መስራት እንዲወርድ የምናስገድድበት ወሳኝ እርምጃ ነው::

ማንም እንደሚያውቀው ወያኔ የአማራ አካባቢወችን በማናለብኝነት ወደትግራይ ክልል ሲያጠቃልል የገጠመው ፈተና (resistance)ዝቅተኛ ነበር:: በዚህም የተነሳ ሌሎች ተጨማሪ መሬቶችን ለመውሰድ ቅድመ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል:: የራስዳሸን ተራራ በትግራይ ክልል እንደሚገኝ በተማሪወች መጽሀፍ ተጽፎ ለ10 አመታት ያህል ትምህርት የተሰጠው ለጨዋታ አልነበረም:: የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት የሚገኙት በትግራይ ክልል እንደሆነ ለቱሪስቶች የማስተዋወቅ ስራ የተሰራው በስህተት አልነበረም:: ከዚህ በፊት ራያና ወልቃይት ያላግባብ ወደትግራይ ሲካለሉ “ለምን?” ብሎ የሞገታቸው ስላልነበረና በኋላም ቢሆን እንዲመለሱ የተደረገ ጫና ስላልነበረ ነው አማሮች ሞኞች ናቸው ብለው ሌላ ተጨማሪ መሬት ለመውሰድ ዕቅድ የነደፉትት:: የትግራይ ትልቁ ተራራ ራስ ዳሸን ነው ብለው በመጽሀፍ አውጥተው ከ10 አመታት በላይ ያስተማሩት አሁን እንደሚባለው በስህተት ሳይሆን የሕዝቡን ስሜት ለመለካት የተጠቀሙበት ዘዴ: ሁላችንም ቀስ በቀስ እየለመድነው እንድንሄድ የታሰበበት መላ ነበር:: የወልቃይት ወገኖቻችን ካለአጋር ብቻቸውን ለአመታት ጮኸው ከወደቅንበት የድብርት አለም ባያነቁን ኖሮ ራስ ዳሸን እና ላሊበላ አካባቢ የሚኖረውን የአማራ ሕዝብ ቀስ በቀስ አፈናቅለው ትግሬወችን ካሰፈሩ በኋላ በሂደት የትግራይ ክልል አካል አድርገው ሲያበቁ ሀፍረትና ይሉኝታ የሚባል ነገር ስለማያውቁ ደግሞ ሌላ መሬት ለመውሰድ መክጀላቸው አይቀርም ነበር::

ከወያኔ ጋር የሚደረገው ትግል ገና አልተጀመረም:: ወልቃይትና ራያን በፈቃዳቸው ይመልሱልናል የሚል ሀሳብ ማናችንም የለንም:: በተለያየ ስልት አማራውን ለማጥፋት የሚያደርጉትን ደባ ያቆማሉ የሚል እምነትም የለንም:: ወያኔ እስካለ ድረስ ሰላም: እኩልነት: ፍትህ እና  ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ ምድር የሚታሰቡ አይሆንም:: የኢትዮጵያ ሕዝብ ተከባብሮ በሰላምና በፍቅር እንዲኖር ከተፈለገ የክፋት ምንጭ የሆነው ወያኔ መጥፋት አለበት:: ወያኔ የሚጠፋው በእንባ ሳይሆን በትግል ነው:: ለትግል ከመነሳታችን በፊት ከመሀል የተሰገሰጉትን ወያኔወችና ማሰቢያ የሌላቸው ፍርፋሪ ቃራሚ (ተስፈኛ) አማራወችን ለይቶ በስልት እንዲገለሉ ማድረግ ያስፈልጋል:: መሰናክል ይፈጥራሉ የምንላቸውን በከፍተኛ አመራር ላይ የተቀመጡ የወያኔ ጉዳይ አስፈጻሚወችን በስብሰባ ወቅት እጅ ወደላይ ብሎ መሰወር ይቻላል:: የክልሉ የጸጥታ ሰራተኞች: የአካባቢ ሚሊሽያና የአማራ ፖሊስ የወያኔን ተልእኮ ለማስፈጸም የተሰለፉ ሀይሎችን ትጥቅ ማስፈታት አይከብዳቸውም:: በመከላከያና በፌደራል ደህንነት ውስጥ ለሚሰሩ ወሳኝ ሰዎች ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመተባበር ሚሽን ቢሰጣቸው መልካም ነው:: በአማራ ክልል የሚደረገውን የነጻነት ትግል ዝግጅት ለማቀላጠፍ በአዲስአበባ ላይ አተኩሮ ውጥረት መፍጠር በክልሉ የሚሰሩ ስራወችን ለመሸፈን ይረዳል::  አላማው ለበጎ እስከሆነ ድረስ ብዙ ብዙ ሊደረግ ይችላል:: የሚያስፈልገው ቁርጠኝነት ብቻ ነው:: ትግሉ ቀላል የማይባል መስዋእትነት የሚጠይቅ ሊሆን ይችላል:: ቢሆንም ቀበቷችንን አጥብቀን መፋለም ግድ ይለናል:: ወያኔ የፈጠረው ችግር ይብዛም ይነስ በሁሉም ኢትዮጵያዊ ላይ የደረሰ በመሆኑ ከሌሎች ክልሎች ጋር የመናበብና የመደጋገፍ ስራ መስራት ተገቢ ነው:: ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን ደፍረን መስዋእትነት ለመክፈል ስንቆም ያኔ ነጻነታችንን ማስመለስ እንችላለን:: እኛ ስንፈራ እነሱ ይጀግናሉ: እኛ ስንደፍር እነሱ በፍርሀት ይርበደበዳሉ:: ስለዚህ ባርነትን ለመሸከም የማንፈቅድ ሁሉ መስዋእትነት ለመክፈል አናመንታ::

አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በርሳቸው የስልጣን ዘመን በወያኔ ገዳይ ቡድኖች ተመተው ለወደቁት አማሮች አዝነው አልቅሰው ከሆነ ቢያንስ ለወገን ያላቸውን ተቆርቋሪነት ያሳዩ የመጀመሪያው የክልሉ ፕሬዚደንት ናቸው በሚል እናከብራቸዋለን:: አግባብ የማይሆነው ከእንግዲህ በኋላም እያስገደሉ ሀዘናቸውን በእንባ ለመግለጽ ቢሞክሩ ነው:: ከባለፈው ተምረው ለሕዝባቸው በጎ ነገር ያደርጋሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን:: እርስዎና ድርጅትወ የህዝብን ትግል መደገፍ ከቻላችሁ የሚከፈለውን መስዋእትነት ያለጥርጥር ይቀንስልናል:: እንጅ ለውጡ እንደሆነ በምንም ታምር አይቀርም:: ከህዝብ ጎን ለመቆም ብትቆርጡ እሰየው ነው:: ከህዝብ ጎን ለመቆም ፍላጎት ካላሳያችሁ የፈለገውን ያህል መስዋእትነት ተከፍሎም ቢሆን ነጻነታችንን አረጋግጠን ዴሞክራሲያዊት ሀገር መመስረታችን ስለማይቀር ከተጠያቂነት አታመልጡም::

የተከበሩ አቶ ገዱ:-

ለሕዝብና ለሀገር ቁምነገር ሊያበረክቱ: ስምወን በማይነጥፍ ቀለም በኢትዮጵያ ታሪክ ሊያሰፍሩ እድል ስልጣን ላይ አስቀምጣወታለች:: ይህን እድል ካመከኑት ለልጅ ልጆችወ መጥፎ ስም አውርሰው በሀፍረት አንገታቸውን ሰብረው እንዲኖሩ ያደርጋሉ:: ሕዝብወን አሰልፈው ጥሎ ለመውደቅ ከቆረጡ አይደለም ተወላጆችወ: አማራ ነኝ የሚል ሁሉ ስምወን እንደነ አጼ ቴወድሮስ: አጼ ሚኒሊክና እንደበላይ ዘለቀ ከልጅ ልጅ እያስተላለፈ በክብር ሲያነሳወ ይኖራል:: መጥፎ ሰው የሚኖረው ለራሱ ነው:: እሱ ካለፈ በኋላ ለተወላጆቹ ዕዳ ይሆናል:: መልካም ሰው ግን የሚኖረውም ሆነ የሚሞተው ለመልካም ተግባር ስለሚሆን በህይወት እያለም ይሁን ከማይቀረው ሞት በኋላም በስሙ የሚማልበት በስራው የሚከበሩበት ይሆናል:: ይወቁበት:: ካለፈ በኋላ ቢቆጩ ትርጉም የለውም:: ማን ማን እንደሆነ ይለዩ:: ለህዝብ ቆመዋል የሚሏቸውን አመራሮች ለማግኘት መስመር ይዘርጉ:: ለጠላት መሳሪያ ሆነው ሕዝብን ለጥቃት የሚያጋልጡትን ሰዎች ማስመከር በምክር ሊመለሱ ያልቻሉትን ደግሞ ማስወገድ የሚከፈለውን መስዋእትነት መቀነስ: የትግሉን አላማ ለማሳካት መሰናክሎችን መጥረግ ነው:: ትንፋሻችንን ውጠን ታግሰን አይተነዋል:: መከራውን ተቀብለን አልቅሰን አይተነዋል:: መከራችን ግን ቀን ከቀን አመት ከአመት እየባሰ ሄደ እንጅ አልተሻሻለም:: አባቶቻችን ፈተናን በትግል እንጅ በልቅሶ አላሸነፉም:: ሀገር በደምና በአጥንት እንጅ በእምባ አልተገነባችም:: የሕዝብ አንድነት በደምና በአጥንት እንጅ በእምባ አልተመሰረተም:: እኛም በተግባር እንዳየነው እምባችን የፈየደው ምንም ነገር የለም:: ከእንግዲህ ወዲያ የሚፈሰው እምባችን ሳይሆን ደማችን መሆን አለበት:: በደም የተከበረው ማንነታችን በደም ይጸናል::

ትንሳኤ ለኢትዮጵያ!

ኢሳት ነገር [አቻምየለህ ታምሩ]

$
0
0

esat

ኢሳት «የአማራ ተጋድሎ» ወይንም Amhara Resistance የሚል አገላለጽ ላለመጠቀም ቆርቧል። የአማራ ተጋድሎ ከተጀመረ ከሁለት ወር በላይ ሆኖታል። አማራው የሚያስተዳድረው ኢሳት ግን አንድ ቀንም እንኳ የአማራ ተጋድሎ የሚለውን የትግል መቅድም መጠቀም አልፈለገም። የአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው ክፍል፣ OMN፣ ኢትዮቱብ፣ ወዘተ… አማራው በየጎበዝ አለቃው ተደራጅቶ ከዳር እስከዳር እያደረገው ያለውን ትግል የአማራ ተጋድሎ ወይንም Amhara Resistance ብለው ዘግበውታል። ኢሳት ግን አማራው በአማራነቱ ተደራጅቶ ከዳር እስከዳር እያደረገው ያለውን ትግል የአማራ ተጋድሎ ወያኔ እንደሚያደርገው «የጎንደር አመጽ»፣ «የጎጃም አመጽ» እያለ በማሳነስ የአማራውን ትግል ይከፋፍላል። በተቃራኒው በወለጋ፣ በሐረር፣ በአርሲ፣ ወዘተ የሚካሄደውን ህዝባዊ ተቃውሞ Oromo Protest እያለ ይዘግባል!

የሆነው ሆኖ ከዚህ ሰዓት በላይ ለአማራው የራሱ የሆነ ሜዲያ የሚያስፈልግበት ጊዜ የለም። በአማራው ገንዘብ የሚተዳደረው ኢሳት ለአማራው የአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው ክፍልን፣ የOMNና የኢትዮቱብን ያህል ሽፋን ሊሰጠው አልቻለም። ኢሳት ከየት አምጥቶ ነው የጎንደር አመጽ ወይንም Gondar uprising እያለ የሚዘግበው? ለምንስ አላማ ነው? ኮሎኔል ደመቀ የጎንደር አመጽ መሪ ነኝ ብሏል? የወልቃይት የአማራ ማንነት ኮምቴ መሪው ኮሎኔል ደመቀ ያነሳው ጥያቄ የጎንደሬነት ጥያቄ ነው ወይንስ የአማራነት ጥያቄ ነው? «ማንነታችን አማራ፣ ቋንቋችን አማራ፣ ፍላጎታችን አማራ፣ ባህላችን አማራ፣ ወዘተ…» ብሎ ትግል የጀመረውን የአማራ ተጋድሎ ምልክት ኢሳት ለምን ጉዳይ ወያኔ ወደሚፈልገው ደረጃ አውርዶ «የጎንደር አመጽ መሪ» ሊያደርገው ፈለገ? ወያኔ አማራው የሚያደርገውን ተጋድሎ ለማሳነስ «የአማራ ተጋድሎ» ማለት ስለማይፈልግ በአማራነት የሚደረገውን ትግል «የጎንደር አመጽ»፣ «የባህርዳር አመጽ»፣ ወዘተ በማለት እያቃለለ ይጽፋል፣ ፕሮፓጋንዳም ይሰራል። ኢሳትም እያደረገው ያለውን ያንን ነው።

ባጭሩ ኢሳት የአማራንው ተጋድሎ አቃልሎ ወያኔ ትግሉን ለማሳነስ በሚጠራበት አግባብ እየገለጸው ይገኛል። ኢሳት በአማራው ትግል ላይ እየፈጠረው ያለውን አሉታዊ ሚና ብናገር ወረቀት አይበቃኝም። ወያኔ የወሰደውን ወስዶ የተረፈውን «የአማራ ክልል» በማለት ያጠረውን ክልል ኢሳት የአማራ ክልል እያለ በድፍረት ይጠራዋል። ወያኔ የአማራ ክልል ብሎ የፈጠረውን አካባቢ ኢሳት ተቀብሎታል። በሌላ በኩል ደግሞ ኢሳት ስለወልቃይት ጠገዴ ያወራል። ቢያስን ኢሳት የአማራ ክልል ብሎ ከዘገበ ላይቀር ከተከዘ በመለስ ያለውን አካባቢ «የአማራ ክልል» ብሎ በሚጠራው አካባቢ ወልቃይትን፣ ጠገዴን፣ ሁመራንና ጠለምትን በማካተት ከወያኔ የተሻለ የአማራ ክልል ካርታ ማሳየት ይችል ነበር።

ሌላ ጊዜ ኢሳት «በአማራ ክልል በጎጃም፣ በአዊና በጎንደር…» ብሎ ዜና ይሰራል። አዊ ግን ጎጃም ውስጥ ነው። ወያኔ አዊን ክልል የማድረግ እቅድ ስላለው አዊን ከጎጃም መነጠል ይፈልጋል። ኢሳትም ያደረገው ይህንን የወያኔ ፍላጎት ማስተጋባት ነው።

ኢሳት ውስጥ ያሉ ሰዎች መተከል የጎጃም አካልና የአማራ መሬት እንደሆነ ያውቃሉ። ዜና ሲሰሩ ግን «በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተከል ዞን» ይላሉ። ወያኔም የሚል ይህንን ነው።

ጎንደር የተካሄደውን የአማራ ተጋድሎ ኢሳት «ስብሀት ሆይ ኢትዮጵያ አትፈርስም!» ወደሚል እቃ እቃ አወረደው። በኢሳት generosity «ወልቃይት የአማራ» የሚለው ወያኔ እንዲሰማ የማይፈልገው የተጋድሎው መነሻ ደብዝዞ «ስብሀት ሆይ ኢትዮጵያ አትፈርስም!» ወደሚል ቅጥያ ወርዶ የወልቃይት የአማራነት ጉዳይ non-issue ወደ መሆን ተገፋ። ዝርዝሩ ብዙ ነው። ለአማራው ከዚህ ወቅት በላይ የራሱ ሜዲያ የሚያስፈልግበት ጊዜ የለም! ሁላችሁም አስቡበት!!


የቀድሞ የአንድነት ፓርቲው አናኒያ ሶሪ በፋና ሞጋቾች አስገራሚ ሙግት

ፕሮፌሰር መስፍን  ወለማሪያምና መሀሪ የውሀንስ ምንና ምን ናቸው ????? [ከአስገደ ገብረስላሴ]

$
0
0

18 / 1 / 2009 ዓ ም መቀሌ

Mesfin 9 - satenaw
ፕሮፌሰር መስፍን  ወለማሪያም

መሀሪ የውሀንስ የሚባለው የመቀሌ ዩንቨርሲቲ የፓለቲካ ሳይንስ አስተማሪና ተመራማሪ  ነው ይባላል ። እኔ ለመሀሪ የውንስ የማውቀው በፌስ ቡክ  ነው ።መሀሪ የውሀንስ የሚል ፕሮፋይል ትክክለኛ ስሙ ነው ወይ ሌላ ለጠፍ ስም መሆኑ አላውቅም ። ከመቀሌ ዩንቨርስቲ ነይ እያለ ግን ይናገራል ። በእንተርኔት  የጻፈው እመለከታለሁ ። በትግራይ ካሉ የገዥ  ፓርቲ  የመንደር ሬድዮ ጣብያዎች ሲናገር እሰማለሁ ። አልፎ አልፎም በአመሪካ ሬድዮ  ጣብያ እንደ አንድ የፓለቲካ ሳይንስ ተመራማሪ  ተንታኝ  ወይ ኤክስ ፐርት ሆኖ ሲናገር እሰማለሁ  ። የሚሰጠው ሀሳብና ትንታኔ  ዋናው ግምገማው ለአድማጩና አንባቢው  የሚሰጥ ሆኖ ፡ በእኔ ትእዝብት ግን  እንደ የዩንቨርሲቲ አስተማሪ ቡዙ ወጣቶች ያንጻል የሚባለው እንደ ፖለቲካ ሳይንስ ተመራማሪ  ስመለከተው ለራሱ የሚሰጠው ግምት እንተወውና ለመቀሌ ዩንቨርሲቲ እና በዛው ለሚገኙ በሽ ለሚቆጠሩ  ሙሁራን ወይ ሊህቃን  ሚዛናቸው እጅጉን ያወርደዋል ።  ምክንያቱም የመቀሌ ዩንቨርስቲ ያህል አንጋፋ ድርጅት ከ25000 በላይ ተማሪዎች ተመራማሪዎች አቅፎ የሚያስተምር ዩንቨርሲቲ አነ መሀሪ የውሀነስ  ናቸው ተመራመሪዎቹ  ሲባል  የትምህርት ቤቱ አመኔታ ያወርደዋል ።
መሀሪ የውሀንስ የሚናገረውና  የሚጽፈው አሁን ላለው ስርአት ያሰደስታሉ ፡የሸሙኛል  የሚላቸው አድርባይና   ለሎሌነት የሚያገኝበት ፡ በተለይ ወደ ህወሀት አመራር ያስጠጉኛል የሚሏቸው ይጽፋል ይናገራል ።  በተጨማሪም ህወሐት የሚጠሏቸው ግለሰዎችና ቡዱኖች ስም ያጠፋል ። አንድ አንድ ጊዜ ደግሞ  አንባብያን እንዳይነቁበት  ለህወሀት አመራር ሀሜት የሚመስል አሽሙር ይጽፋል   ይናገራል  ። ግን ደግሞ ለህወሐት   አይጓዱም ።

ሌላ መሃሪ የውሀንስ የሚጽፏቸው ፡የሚናገራቸው  ያልተገረዙና ሙሁራዊ ያልሆኑ ቃላት ናቸው ። ይህሰውዬ የስው  ክብር ይነካል፡የሰው ማንነት ያዋርዳል ።
አንአንድ ጊዜ  ይህሰውዬ የተወለደውና  ያደገው በአክርያ አርባዕተ አስመራ ስለሆነ ፡ በዛ ያደጉ ሰዎች ደግሞ በጣልያን ግብረገብነት የጎደለው ባህል ስለታነጹ መሀሪም ከአባት ከአያት ቅድመ አያት የወረሰው ይነረው  ይሆን እላለው ። ምክንያቱም ከላይ እንደጠቀስኩት ለህወሐት ኢህአደግ ለሚቃወሙ  መጥፎ  እና አስነዋሪ ስድብ ይሳደባል   ይህደግሞ የሞሶሎኒ ባንዳዎች ያወረሱት ይመስለኛል እነዛ ባንዳዎች የሚሳደቡበት ቃላተ ። ፈለዲካኒ ፡ቦርኮ  ወዘተ ነው ።

ይህ ሁሉ የምትነግረን ከማሀሪ የውሀንስ ምን አገናኜህ ትሉኝ ይሆናል ? እኔ ከዚህ ፉጡር ምንም ግንኝነት የለኝም ፣ቂምበቀልም የለኝም ።  ለዚህ  ሰውዬ  በዚህ ጽሁፉ መልስ ልሰጠው የተገደድኩበት ።
1  ከ84 አመት በላይ የእድሜ ባለጸጋና በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ  ወገኖች አስተምረው ከፍተኛ ደረጃ ላበቁ ሊሂቅ ፕሮፌሰር  መስፍን ወለማሪያም  በመሀሪ የውሀንስ የሚባል ፉጡር  በፈስቡክ ስለሰደባቸውና ስለአቋሸሻቸው ስላየሁ ይህ  ሰውዬ መልስ መሰጠት ይገበዋል በሚል እምነት ተነሳስቼ ነው ።
2 ለእኔም ካሁን በፊት ቡዙ  ጊዜ በወረደ ቃላት ስለሰደበኝ ።ዛሬም ለፕሮፌስ መስፍን ወለማርያም በርካሽና በወረደ ቃለት በጽሁፉ ሲሲሰድባቸው አይቸ  የተቃውሞ መልስ  ወይ ኮሜንት በመስጠቴ መጥፎ  ስድብ  እኔን የማይገልጽ ሰድብ ሰለሰደበኝ ። ለዚህ ፉጡር መልስ መስጠት ያስፈልገዋል ከሚል እምነት ነው ። ዝርዝሩ ይቀጥላል ።
የተከበራችሁ አንባብያን እኔ ፕሮፌሰር መስፍን እማውቃቸው ከ25 አመት በፊት እኛ ከበረሀ እንደገባን ለመጀመሪያ ጊዜ ከሀገራችን ሙሁራን አቃም ይዘው ከህወሐት መሪዎች ደፍረው ፖለቲካዊ ክርክር ያደረጉ ፕሮፌሰር መስፍን ወለማርያም  ደጉተር አስራት ወልደየሱስ ፡ደጉተር መኮነን ብሻው ፡ ደጉተር ገሞቹ ነበሩ ።የስም ስህተት ልታሩሙኝ ትችላላችሁ ። እነዚህ ሰዎች አነዚህ ሰዎች ልክ እንደደርግ ነፍጥ የታጠቁ ናቸው ብለው ሳይሰጉ ከመለስ ጋር ለብዙ ቀናት  ፡በሀገር ሉአላውነትና የባህር በር ባለቤትነት ፣በሚመለከት ፡በአይዶሎጅና  በፖሊሲ ወዘተ ከባድ ክርክር አድርገዋል ።
ከዛ በኃላም በቡዙ መድረኮች  ለዚህ ስርአት  እስከ አሁን እየተማጎቱት እያጋለጡት ቆይታል ።
በመሀሪ የወሀንስ ግን በጹፉ በምርምር ያገኙት ደጉትሬት ፡ፕሮፌሰርነታቸው በመንጠቅ ፡ አዬ ጋሼ መስፍን በጃኖሆይ ፡በደርግ ፡በኢህአደግ በተቃውሞ እጅሜው የፈጀ  ያረጀ ያፈጀ ለምን አያርፍም በማለት አንተ እያለ እያብጠለጠለ  ማንነታቸው በሚነካ በባንዳዊ ቃላት ሲሰድባቸው  ስመለከት አዘንኩኝ ።
የተከበራቹ አንባብያን  ለፕሮፌሰሩ እድሜ ልኩ በተቃውሞ  ያሳለፈ ሽማግሌ ብሎ እንደእርኩስ ሲያቋሽሻቸው  ።በእኔ እምነት ግን እኝህ ሊሂቅ ለጃኖሆይ ሰዘውዳዊ ስርአት ፡ለደርግ ፋሽታዊ ስርአት መቃወማቸው አሁን ደግሞ እኛ ተሸክመን ያመጣነው  ጸረ ዲሞክራሲ አንባገነን ሆዳም የበሰበሰ ስርአት መቃወማቸው በአጠቃላይ ለሰወስቱ ሰው በላ ስርአቶች መቃወማቸው ህዝብም እንዲቃወማቸው ማድረጋቸው  ወደ 60 አመት መታገላቸው በሁሉም የኢትየጱያ ህዝብ  የክብር ሽልማት ይገባቸዋል ።
እኒህ ንጹህ ኢትዮጱያዊ ከዘውዳዊው ስርአት ፡ከደርግ ፡ከህወሐት ኢህአደግ ተለማምጠው  ፡ተሰማምተው ትንሽ ስልጣን ቢዩዙ ንሮ በአሁኑ ጊዜ ሰማይ ጠቀስ ህንጻዎች ፡በሞቶ የሚቆጠሩ የደረቅና የፈሳሽ የጭነት ካሜኖች  ባለቤት በሆኑ ነበር ።ዘርመንዝራቸው  ሀብት ባካበቱ ነበር ። በተቀማጥለ የተወሳሰበ ቤት በኖሩ ነበር ፡ስልጣን ቢፈልጉ ቢያንስ የሚንስቴርነት ቦታ ባገኙ ። ኝሮፌሰር ግን  አዲስ አበባ  ከ80 አመት በላይ ተቀምጠው  እስከአሁን በአንድ ያረጀ የቀበሌ ቤት ነው ተካራይተው የሚኖሩት  ። ያች ቤትም አንድ ምኝታ ቤት እንደሳሎን የሚጠቀሙባተ በማኸል አንዲት ጠረቤዛ አስቀምጠው  ፡ሁለት ዙር የመጻሀፍት መደርደርያ ሸልፍ  አሰቀምጠው እየተመራመሩ የሚኖሩ የእድሜ ባለጸጋ ሊሂቅ ናቸው ።
እንደዚህ ያሉ የሀገር ቅርስ የእድሜ ባለጸጋ ሙሁር  በእነ መሐሪ የውሀንስ ያሉ አድርባይና የዚህ ስርአት ዘበኛ የሆኑ ሊብጠለጠሉ   ሊዋረዱ በበኩሌ አልቀበለውም ማንም ዜጋም መቀበል የለበትም  ።
ፕሮፌሰር መስፍን ወለማርያም ከ60 አመት በላይ የስራ  አገልግሎት ዘመናቸው ሰዎች ሊሳሳቱ የሚቹሉዋቸው  ማናቸውም   ስህት ሊኖሩዋቸው ይችላሉ   ለዚህች ሀገርና ዜጎቻ ከሰጡት አገልግሎት  ሲነጻጸር ግን እጅግጉን ትንሽ ነው ።ቢያንስ ግን አገረና የሀገር ሉአሏውነት  ፡የዜጎች ፍትህና ነጻነት ይፈልጋሉ ። የህዝብ ሀብት አልወረሩም ። ለሀገራቸው እንጅ  ለሆዳቸው ሲሉ አይገዙም ።ስለ ህዝብ ነጻነት እንጅ ለራሳቸው ሆድ ለሞምሏት አይራራጡም ።  ጊዚያቸው በምርምር   ያሳለፉና አሁንም አረጀሁ ደከመኝ ሳይሉ  ለዚህ አዲስ ትውልዲ  ተምክሯቸው እየሰጡ ናቸው ።
አሁን ያሉ ወጣትች የፕሮፌሰር መኖሪያ ቤትና የምርምር ላይብረሪያቸው ቢፈትሹ ቡዙ እውቀት ሊሸምቱ ይችላሉ ። ይህ የማይደርቅ ሀብት ግን ለመሀሪ የውሀንስና መሰሎቹ ምናቸው አይደለም ።
የሀወሐት ኢህአደግ አመራርና ታማኝ ካድሬቻቸው  የፕሮፌሰር መስፍን እምቅ  ሀብትና ልምድ እንደ የሀገር ሀብት አይተው ለመማር ተነሻሽነት እንደማሳየት ፈንታ በአንጻሩ የፕሮፌሰር ሀሳብ በጋዜጣ ፡በፌስቡክ ፡በመጽሀፍ ፡ ካዩ አገር እንደ ፈረሰች በመቁጠር የስም ማጥፋት ዘመቻቸውን ያራምዳሉ ።  እንዳውም የሆነ አደረጃጀት ከታዬ ፕሮፌሰር በስተጀርባ አለ ተብለው ከባድ ክትትል ነው የሚደረግሏቸው ።
ይህ ስርአት ግን ፕሮፌስር እንደዚ ተናገሩ ፡ የትምክህት ቁንጮ ናቸው ፡ ስልጣን ናፋቂ ወዘተ  ናቸው  እያላችሁ የሙሁራን ስም ከምታጠፉ ከነ ፕሮፌሰር መስፍን ስነስርአትና  ላብክን ያላፈሰስክበት የህዝብና የመንግስት ሀብትና ንብረት መመዝበር መውረር ሀብት መደለብ ጥቅሙና ጉዳቱ ብትማሩ ያሻችወል ። ምክንያቱም  በሰወስቱ የተባላሹ ስርአቶች  ሀብት ሊወሩ የሚችሉበት እድል እያላቸው ከ84 አመት በላይ የኖሩባት አገራቸው ህልፈታቸው ሲደርስ አስከሬናቸው የምትወጣበት ጎጆም እንኳን የላቸውም ። ንጹህ ሰው ።
መሀሪ የውሀን ለፕሮፌሰር መስፍን ብቻ አይደለም ግብረገብነት የጎደለው ስድብ የሰደባቸው  ለእኔም  መጥፎ ስድብ ሰድቦኛል ።
ስድቡም  አሰገደ  አንተ ያረጀህና ያፈጀህ አታርፍም  ደሞ ለቆሻሻው መስፍን  ወለማርያም በተግርኛ ትሳላበጥ አሎኻ   ( ትለማመጣለህ ) ለኽባጥ  በትግርኛ  በአማርኛ ተጋላባጭ የትምክህተኞች ተላላኪ ብሎኛል ።
ይህሰውዬው አሁንም ልንገረው አዎን እኔ ቢያንስ የ68 አመት እድሜ ባለጸጋነኝ  እድሜ መቁጠር ብቻ ሳይሆን  ከ16 አመት እድሜ ጀምሮ እስከ አሁን  51 አመት እድሜዬ በሚገባ ለዝህች አገር  ሰርቸላት አለሁ ።መሀሪ የውሀንስ ደንቆሮ ሽማግሌ አርፈህ ተኛ ብለኸኛ ። ስለስድብህ ልተዎው  የባንዳዎች ባህሪ ስለሆነ  ።
ሰልባጥ (አቃጣሪ )  (ለኽባጥ ) ተለማማጭ  ያልከኝ እኔ  ለማንም ተለማምጨ አላውቅም    ያንተ ጌቶችና የተግራይ ህዝብ  ፡ ታጋዮች  ያውቁኛል ።ብለማመጥ ነሮ በአሁኑ ጊዜ የማይቆጠር ሀብት በኖረኝ ነበር ።ከህወሀትና አጋሮቹ  ከተለማመጥክ ቢሌነር መሆን እጅጉን ቀላል ነው ። እኔ ከህወሐት 19 አመት ኑሬ ነበር ጊዜዬ በትግል ነው የነበርኩት  ። ከዛ በኃላም የቀን ሰራተኛ እየሰራሁ ልጆቼ ከህዝባቸውጋር አስተምሬ አለሁ በህዝብ ሀብት መዝብሬና ወርሬ  ወደ አመሪካ ከናዳ አውሮፓ  ቻይና አላኩም  ። በህጋዊ መንገድ የተመራሁት ለ22 አመት ያህል በቆርቆሮ ታጥሮ  የሚኖርና ቦሎፎንና መሻሻታ የለው ሰርቢስ  ቤት  አለኝ
ከህወሀት ሆዳሞች ብጠጋና ብሰላበጥ ንሮ ያቺ መሬቴ ሰማይ ጠቀስ ህንጻ በሰራሁባት ነበር ።
ሌላ መሀሪ የውሀንስ  ያረጀህ ያፈጀህ  አርፈህ ተኛ ብለኸኛል ። አበደን ነው እምልህ እኔ በአሁኑ ጊዜ ከማሃሪ የውሀንስ በእጥፍ እጥፍ የሚበልጥ ጭንቅላት አለኝ ።አንተ እንዳልከው ደንቆሮ አይደለሁም  እስከህልፈተ ሂወቴ ለደንቆሮች ፡ለሆዳሞች ፡ ለጥገኞች በመጋለጥ እታገላለሁ ።ለማን ሊመቸው ነው ተኛ የምትለኝ ? መሀሪ እኔ ስልጣን ብፈልግ ንሮ ፡ከዋሸሁ እንዳንተ አድራሽ ወይ ተላላኪ ብሆን ንሮ ስልጣን በሽ ነው ። እኔግን የምፈልገው ፖለቲካዊ አስተሳሰብ ወይ አይዶሎጂ ለውጥ  ለማምጣት ፡ለዜጎች መብትና  ነጻነት  አንድነት የሚቆም ወጣት ቡቁ ሙሁራን ተመራማሪዎች  ስርአቱ ለውጠው ስልጣን ከጨበጡ እኔ ስልጣን እንደያዝኩ ነው የምቆጥረው  ።
ሌላ መሀሪ የውሀንስ  ተቀባይነት የለብህም አብቅታሀል ብለኸኛል?ስለተቀባይነት መላው የኢትየጱያ ህዝብ በተለይ በቅርብ ያለው የትግራይ ህዝብ እድሜ ጾታ ሀይማኖት በማይለይ  ተቀባይነት የለህም የምትለን ያለህ ቦታ የለውም አይለኝም  ። ይለቁንስ የራስህ ኦዴንስ ፈተሸው ።
የተከበራቹ አገር ወዳድ ወገኖቼ  መሃሪ የውሀንስ ፕሮፌሰር መስፍን እንደ መነሻ አድርጎ ባነሳው አጀንዳ  ለፕሮፌሰር መጣበቅ ወይ በመወገን በሰጠሁት መልስ  እርግጠኛ ነኝ በትግራይ የሚገኙ የመንደር የህወሐት ሬድዮ ጣብያዎችና መሀሪ የውሀንስና መሰሎቹ ቅጥረኞች  እንደሚጩሁብኝ የታወቀ ነው ። ግን ደግሞ እንታገለው አለን ። እነመሀሪ የውሀንስም ተዘጋጁ ።ከእንዲህ ወዲህ  በደቡቁን ደቡቁን  አንጓዝም ።
አንበረከክም !!!
18 /1 / 2009 ዓ  ም  መቀለ

የትግራይ ህዝብ እና የህውሓት ግኑኝነት ነባራዊ ገፅታ [ከሰለሞን ነጋሽ]

$
0
0

መግቢያ

የትግራይ ህዝብ እና የህውሓት ግኑኝነት በተመለከተ በተለያዩ ሰዎች የሚሰነዘሩ አስተያየቶች እስከዛሬ ድረስ አወዛጋቢ ሆነው ቀጥለዋል። እስከዛሬ ድረስ አወዛጋቢ መሆኑ በራሱ በጣም የሚያሳዝንና የሚያሳስብ ነገር ነው። ከዚህ ቀደም በርካታ ሰዎች ለጉዳይ ትኩረት ሰጥተው የጻፉ፡ የሚድያ ሽፋን የሰጡ፡ የግል ምስክርነታቸውንና ግንዛቤያቸውን በተለያየ መንገድ የገለጹ ቢሆንም፡ ወቅቱ የሚጠይቀው ርዕሰ ጉዳይ በመሆኑ እኔም የራሴን እይታ ማስቀመጥ እንዳለብኝ በማመን ይህን ጽሁፍ አዘጋጅቻለሁ። ጽሁፉ ምናልባትም ከዚህ ቀደም ያልነበራችሁን ግንዛቤ እንደሚያስጨብጣችሁ ተስፋ አደርጋለሁ።

ቅድመ እይታ

በአንድ በኩል ህውሓት ደጋግሞ “እኔና የትግራይ ህዝብ የማንነጣጠል አንድ አካል ነን” የሚል ፕሮፓጋንዳ ሲነዛ ይታያል። በሌላ በኩል ደግሞ ከህዝቡ መካከል በግልጽ “የለም እኛና እናንተ ለየቅል ነን፡ ገዢና ተገዢ ወይም ጨቋኝና ተጨቋኝ ነን” የሚላቸው በጣም ጥቂት ነው። ጥቂት በመሆኑ የተነሳ እና በህውሓት የረዥም ጊዜ የፕሮፓጋንዳ ስራ የተነሳ፣ በአብዛኛው ሌላው ኢትዮጵያዊ ዘንድ ፕሮፓጋንዳው ተቀባይነትን አግኝቶ ቆይቷል። ህዝቡና ድርጅቱ የማይነጣጠሉ ናቸው ተብሎ ተደምድሟል።
“ህውሓት እኔና የትግራይ ህዝብ አንድ ነን ይላል፡ አይደለንም ብሎ የሚከራከር ሰው አልተገኘም። ስለዚህ እነሱ አንድ ነን ካሉ እኛ እንዴት አንድ አይደላችሁም ልንል እንችላለን” ተብሎ ለሚነሳ ጥያቄ አጥጋቢ ምላሽ ለመስጠት አስቸጋሪ ሁኔታ ነበረ። በተጨማሪም “የትግራይ ህዝብ ከሌላው በተለየ በዚህ ስርዓት ተጠቃሚ ነው፣ ከዚህ የተሻለ ሌላ ሊጠቅመው የሚችል ስርዓት አይኖርም፣ ስለዚህ ጥቅሙን ለማስከበር ከስርዓቱ ጎን የግድ ይሰለፋል” ብለው የሚከራከሩም ጥቂት አይደሉም።

TPLF Tigray Flags in Ethiopia
የትግራይ ህዝብ ልዩ ተጠቃሚነት i

የተለየ አፈናበሌላ በኩል ደግሞ “ህዝቡ ህውሓት እኛን አይወክልም ብሎ ለመናገር ያልቻለው ከሌላው በተለየ በትግራይ አፈናው ስለሚያይል ነው።” እንዲህውም “ህዝቡ በተለየ ተጠቃሚ ሊሆን ቀርቶ ከሌላው በባሰ የባርነትና የድህነት ህይወት ውስጥ እየኖረ ነው።” ብለው ምስክርነታቸውን የሚሰጡ ቁጥራቸው የማይናቅ ነው። የዛሬ ዓመት ትግራይን እንዲጎበኙ የተደረጉ አርቲስቶች አብዛኞቹ ራሳቸውን ከዚህ ጎራ መድበዋል። እነ አትሌት ፈይሳ፣ ፕ/ርመስፍን ወ/ማርያም፣ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ እና ለሌችም የትግራይ ህዝብ የሚኖረው እንደማንኛው ኢትዮጵያዊ ነው በሚል አቋማቸው እናውቃቸዋለን። እኔም ራሴን ከዚህ ጎራ እመድባለሁ። ክልሉ ውስጥ እንዳደገ፣ እንደተማረና እንደሰራ ሰው ነባራዊውን ሁኔታ ኖሬበት የማውቀው ነውና ይህን አቋም ብይዝ የሚገርም አይሆንም። ማስረዳት ግን ይጠበቅብኛል። እንሆ፥

ቀጥተኛ አፈና

ትግራይ ከሌሎች ክልሎች ለየት የሚያደርገው በህውሓት ቀጥተኛ አፈና ስር መሆኑ ነው። ህውሓት በአገሪቱ የፖለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነቱን የተቆናጠጠ ብቸኛ “ሉአላዊ” ድርጅት እንደመሆኑ መጠን፡ ይህን የበላይነቱን ለማስጠበቅ ቁልፍ ቁልፍ የመንግስት ስልጣኖችን በመያዝና ሁሉንም መንግስታዊ መዋቅር በቁጥጥሩ ስር በማድረግ አገሪቱን በእግር ብረት ጠፍሮ እየገዛ እንደሆን ይታወቃል። በሁሉም ክልሎች ተመሳሳይ የሆኑ የጋራ የአፈና ዘዴዎች ተዘርግተዋል። የጸጥታ ሀይሉ፣ መከላከያው፣ የፍትህ ተቋማቱ፣ የደህንነት ክፍሉ ወዘተ በህውሓት ቁጥጥር ስር ውለው የኢኮኖሚና የፖለቲካ የበላይነቱን ለማስጠበቅ የሚጠቀምባቸው የፖለቲካ መሳሪያ መሆናቸው እሙን ነው።
ያም ሆኖ ሌሎች ክልሎች በህውሓት ቀጥተኛ አፈና ስር አይደሉም ያሉት። አፈናው በሌላ third party (ወይም ጠፍጥፎ በሰራቸው ተላላኪ ድርጅቶች) አማካኝነት የሚገለጽ ነው። እነዚህ ፓርቲዎች የህውሓትን ያክል ጥንካሬና aspirations ኖሯቸው ህውሓት በሚያፍነው ወይም ማፈን በሚፈልገው ደረጃ ህዝብን የሚያፍኑ አይደሉም። እንዳውም አንዳንዴ የሚገዳደሩበት (resist የሚያደርጉበት) ሁኔታ አለ። በነዚህ ክልሎች ውስጥ ለሚኖር ህዝብ ይህ ክፍተት ተቃውሞውን በተለያየ መንገድ ለመግለጽ በአንጻራዊነት የተሻለ ዕድል ፈጥሯል። ለምሳሌ የግል ፕሬሶችን በመክፈትና ህዝብን በማነቃቃት፣ የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶችን በመመስረትና በህጋዊ ተቃዋሚነት በመንቀሳቀስ፣ ብሎም በአደባባይ ተቃውሞን በማነሳሳት ረገድ በሌሎች ክልሎችይህ ክፍተት ጉልህ ሚና ተጫውቷል።

 

ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ ትግራይ በቀጥታ በነሱ ቁጥጥር ስር መሆኑ እና ደግሞ በዚህ ክልል ተቃውሞ ከተነሳባቸው ለህልውናቸው የመጨረሻ አደገኛ በመሆኑ፣ እነዚህ በሌላ ክልል የሚታዩ የህዝብ የresistance መገለጫዎች ለረዥም ጊዜ በትግራይ እንዳይፈጠሩ ማድረግ ችለዋል። የግል ፕሬስ ትግራይ ውስጥ ከነ አካቴው እንዳይፈጠር አድርገዋል። በሌሎች አካባቢዎች አልፎ አልፎ ብቅ የሚሉ የግል ህትመቶችና መጻህፍቶች የትግራይን ምድር እንዳይረግጡ እገዳ ተጥሎባቸዋል። የግል ሚድያ ለመፍጠር የሞከሩ አንድ ወይም ሁለት ወጣቶችን ገና በለጋነታቸው ሳይበራከቱ ልክ አስገብተዋቸዋል። በትግራይ የሚናገረው ህውሓት ብቻ ነው። የሚደመጠው  ህውሓት ብቻ ነው። ሌላ ድምፅ የለም።

በትግራይ ለረዥም ጊዜ ተቃዋሚ ፓርቲ እንዳይመሰረትና በክልሉ እንዳይንቀሳቀስ ግልጽ በሆነ አፈና አግደውታል። ዓረና ትግራይን ዘግይተውም ቢሆን የፈቀዱት አንድም የመድብለ ፓርቲ ስርዓት በክልሉ እንደተጀመረ ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ለመጠቀም፣ ሁለትም መስራቾቹ የቀድሞ የህውሓት ታጋዮች በመሆናቸው ህዝብ ከኛ በተለየ መልኩ ሊቀበላቸው አይችልምና ለስልጣናችን አደጋ አይሆኑም በሚል እሳቤ መሆኑ ይታወቃል። ያም ሆኖ ሰርጎ ገቦችን ከትተው በየጊዜው ሲያፍረከርኳቸው ይስተዋላል። ስርዓቱን አምርረው የሚቃወሙ ወጣቶች አማራጭ ፓርቲ ሊመሰርቱ ቀርቶ ብሶታቸውን የሚጋሩበት፡ተቃውሞና ትችታቸውን የሚናገሩበት መድረክ ፈጽሞ አያገኙም። የህውሓት ቀይ መስመር በትግራይ ደመቅ ይላል። ህውሓት ተቃውሞ በትግራይ ፈጽሞ አይፈቅድም። እስከመቼውም ድረስ ሊፈቅድ አይችልም።

የመረጃ አማራጭ ከሌለ፣ በክልሉም ሆነ ከክልሉ ውጪ ህውሓት እየሰራቸው ያሉ ወንጀሎች ህዝቡ የሚያውቅበት መንገድ ከሌለው፣ ህዝቡ ለነጻነቱ እንዲቆም በሰላማዊ መንገድ የሚያነሳሱና የሚያስተምሩ ወጣቶችና ፓርቲዎች ከሌሉ፣ በራሱ ጊዜ ህዝብ ተነስቶ ለመቃወም እድሉ ጠባብ ይሆናል። ወይም በጣም ጊዜ የሚጠይቅ ይሆናል። በአንድ በኩል ህዝቡ ከመታፈኑ በተጨማሪ በጥላቻ የተሞሉ ፕሮፓጋንዳዎችን በየቀኑ ሲለፍፉበትና ሲያሴሩበት ስለሚውሉ በፍርሃት እንዲሸበብ  ተደርጓል። በሌላ በኩል ደግሞ በብዙዎች ዘንድ ባልተነቃባቸው ተዘዋዋሪ የአፈና መሳሪዎችን በመጠቀም ህዝቡ በተለይ የገጠሩና የከተማ ድሃው ክፍል ሰጥ ለጥ ብሎ ለህውሓት እንዲገዛ ተደርጓል።

ተዘዋዋሪ የአፈና መንገዶች

የትግራይ እግሪ ምትካል /ትእምት/EFFORT/

ይህ ድርጅት የህውሓትን የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጡንቻ ያፈረጠመ ጠንካራ ድርጅት ነው። ስልጣን ላይ ለመቆየት የመንግስት መዋቅሮችን መቆጣጠር ብቻውን በቂ አይደለም በሚል እምነት የቆመና የራሱን የኢኮኖሚ ኢምፓየር በአገሪቱና በውጪ አገራት የዘረጋ ድርጅት ነው። እንደ ድርጅት financial freedom ከሌለውና እንደ መንግስት በውጭ እርዳታ የቆመ ከሆነ፣ ህውሓት በፈቀደው መንገድ አገሪቱን መግዛት አይችልምና ከጅምሩ የዚህ ዓይነት ምሰሶ መትከል ነበረበት።
ይህ ድርጅት ፓርቲው በማንኛውም ጉዳይ ፈርጣማና ፍሌክሲብል የሆነ ጡንቻውን እንዲጠቀም ከማስቻል በተጨማሪ፣ በስነልቦና ጦርነት ረገድ የማይናቅ ድልን አቀዳጅቶታል። ዛሬም ድረስ በርካታ ወጣቶች EFFORT የህዝብ ንብረት ነው በሚል ተስፋ ይኖራሉ። ይህን የህዝብ ንብረት “ከጠላት” የመጠበቅ አደራና ግዴታ አለብን ብለውም ያምናሉ። ይህ የህዝብ ሀብት ባለበት ሊጠበቅ የሚችለውና ህዝቡን ተጠቃሚ ማድረግ የሚቻለው ህውሓት ሲኖርና ችግሮቹን በግምገማ በተሃድሶና በመሳሰሉት እንዲፈታ ማድረግ ስንችል ብቻ ነው ብሎ የሚያምነው ቁጥሩ ቀላል አይደለም። ህውሓት ከስልጣኑ ከተነሳ ይህን ሀብት እናጣለን በሚል ስጋት ትግላቸው ለጥገናዊ ለውጥ ብቻ ይሆናል።
በእርግጥ ዛሬ በትግራይ ተቃውሞ አለ ከተባለ ከዚህ የዘለለ ተቃውሞ አይደለም ሊታይ የሚችለው። ይህ ደግሞ ለህውሓት ድልን አጎናጽፎታል። እኔ ከሌለሁ ትጠፋለህ ከሚለው ፕሮፓጋንዳ ጋር ስምም የሆነ አካሄድ በመሆኑ፣ ህዝቡ ህውሓት ላይ እንዳይነሳ ራሱን የቻለ አንድ ምክንያት ሆኗል። ባጭሩ በተዘዋዋሪ መንገድ የማፈኛ መሳሪያ ሆኖ አገልግሏል። ይሄ ወደፊትም አደጋ ያለው አካሄድ በመሆኑ በEFFORT ጉዳይ ላይ በግልጽ መነጋገር ለነገ የሚተው ጉዳይ መሆን የለበትም። በዚህ ዙሪያ ግልጽ የሆኑ ውይይቶችን ማድረግ በሚከተሉት ሁለት ምክንያቶች ተገቢ ነው፥ በመጀመሪያ ደረጃ በዚህ ምክንያት ጥገናዊ እንጂ መሰረታዊ ለውጥ አያስፈልግም ብሎ ለሚያምነው ክፍል መልስ ለመሰጠት ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ በድህረ ህውሓት ለምትኖረን ኢትዮጵያ ይህ ኩባንያ ያልተጠበቀ ችግር ሳይፈጥር በፊት ውይይቱን ከወዲሁ መጀመር የነገ አካሄዳችንን ፈር ለማስያዝ ይረዳል።

ማሕበር ረድኤት ትግራይ /ማረት/REST/

ይህ ድርጅት ላይ ላዩን በእርዳታና በልማት ስራ የተሰማራ ሲቪክ ተቋም ይምሰል እንጂ በብዙዎች ዘንድ ያልተባነነበት mighty የፖለቲካ ድርጅት ነው። በክልሉ ከፍተኛ የፖለቲካ ስልጣን ያለውና ህዝቡን በቁጥጥራቸው ስር ለማድረግ የሚጠቀሙበት ቁጥር አንድ የፖለቲካ መሳሪያቸው ነው። የመሳሪያዎቹ ዝርዝር ከቀላል ወደ ከባድ፥

1• ማረት በህዝብ ስም እርዳታ ይጠይቃል። እርዳታ የፖለቲካ መሳሪያ ነው። የህውሓትን ትዕዛዝ የማያከብር ድሃ በእርዳታ ይቀጣል። ከምግብ ለስራ ይሰናበታል። ወዘተ። ድሃን በጉሮሮው ከቀጣኸው ጉልበት ኖሮት ሊቃወምህ አይችልም። ስለዚህ ቀዳሚው የህውሓት ስራ አብዛኛውን የህዝብ ክፍል አደህይቶ የመግዛት ፖሊሲውን ማስቀጠል መቻሉ ነው። በቁጥጥሩ ስር በሆነ የማረት ተቋም እርዳታና የምግብ ለስራ እድሎችን በመስጠትና በመንፈግ በቀላሉ ህዝቡን ለማንበርከክ የተዋጣለት ከፖሊሲው ጋር የተቀናጀ የፖለቲካ መሳሪያ ሆኖ አገልግሎታል።

2• ህውሓት ማንኛውም ዓይነት የውጭ ግብረሰናይ ድርጅት (NGO) ትግራይ ውስጥ ራሱን ችሎ እንዳይንቀሳቀስ ገና ጫካ እያለ ጀምሮ በህግ አግዷል። ፕሮጀክታቸውንና ገንዘባቸውን ይዘው መጥተው ለማረት በማስረከብ፣ በማረት አማካኝነት ፕሮጀክቱ ተፈጻሚ እንዲሆን የሚጠይቅ አሰራር ይከተላል። መያዶቹ ከተስማሙ የፕሮጀክቱን ሂደት አልፎ አልፎ ሱፐርቫይዝ ለማድረግ ብቻ ይፈቀድላቸዋል። ካልተስማሙ ገንዛባቸውንና ፕሮጀክታቸውን ይዘው ወደ መጡበት እንዲመለሱ ያደረጋል። ህዝቡ መሃል ገብተው በራሳቸው እቅድና የአፈጻጸም መንገድ እንዲሰሩ ህውሓት ፈጽሞ አይፈቅድላቸውም፤ በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች፥ የመጀመሪያው የውጪ ድርጅቶች ህዝቡን ቀርበው በማነጋገር ህዝቡ ያለበትን ትክክለኛ ሁኔታ እንዳያወቅ፣ አውቀውም ወደ ውጪ እንዳይወጡት በመፈለግ ሲሆን ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ከህውሓት ቁጥጥር ውጪ የሆነ ገቢ ህዝቡ እንዲኖረው ስለማይፈለግ ነው።

እነዚህ ሁለቱ ምክንያቶች ህውሓት በክልሉ የሚኖረውን ሃይል ማዳከም የሚችሉ መሆናቸውን ልብ ይሏል። ዛሬ NGOዎች ስፖንሰር ያደረጉትን ፕሮጀክት ሱፐርቫይዝ ሲያደርጉ የሚያነጋግሩት ህውሓት ያዘጋጀላቸውን ካድሬዎችን ብቻ ነው። ህውሓት ያላዘጋጃቸው በዕጣ የተመረጡ ተራ ሰዎች ስለሚኖሩበት ህይወት በትክክል እንዲናገሩ አይደረግም። ድንገት ተመርጠው ከሆነም ካድሬ በመሃከላቸው እንዲገኝ ተደርጎ ስለሚናገሩት ነገር እየተሰለሉ ነው። በተናገሩት መሰረት ከተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች እንዲገለሉ እንደሚደረጉ ስለሚያውቁ ያሉበትን ሁኔታ በትክክል ለመናገር ይፈራሉ። በዚህ ምክንያት በተለይ ለውጭ ሚድያዎችና የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ክልሉ ዝግ እንደሆነ እስከዛሬ ድረስ አለ። በሌላ በኩል ደግሞ ከህውሓት ቁጥጥር ውጪ የሆነ ገቢ የሚያገኝ ሰው፣ በህውሓት መታዘዝን አሻፈረኝ ሊል ይችላልና ለፖለቲካ ህልውናቸው አደጋ ነው። ስለሆነም ህውሓቶች ይህን ሊፈቅዱ ፈጽሞ አይችሉም።

3• ማረት ከእርዳታ ውጪ በ”ልማት” ትርፍ በሚያስገኙ የንግድ ስራዎች ላይ የተሰማራ ድርጅት ነው። “የልማት” ስራው ባብዛኛው ፕሮጀክቶችን ቀርጾ በፕሮጀክት ስም ከውጪ ለሚያገኘው ገንዘብ እንደ ሽፋን የሚጠቀምበት የማጨናበሪያ መንገድ ሲሆን፣ ጎን ለጎን ደግሞ የማሳያውን ልማትም ቢሆን የሚሰራው ለድርጅቱ ታዛዥ የሆኑ አካባቢዎችንና ግለሰቦችን ታርጌት ባደረገ መልኩ ነው። ያም ሆኖ አንዱን የልማት ስራ ከሶስት ወይም አራት የተላያዩ ፕሮጀክቶች ሂሳብ እያወራረደ ኪሱን የሚሞላበት አሰራርን ዘርግቷል። በዚህ መንገድ የሚገኘው ትርፍ የህውሓትን ኪስ ከማደለብ ባሻገር ህዝቡን በሚከተለው መንገድ ለማፈን ይጠቀሙበታል።

4•  ማረት የብድር ሰጪ ተቋም (ደደቢት) በውስጥ ስላለው በዚህ ተቋም አማካኝነት በተለይ ድሃው ገበሬ በተለያዩ ምክንያቶች ብድር እንዲወስድ በህውሓት ይገደዳል። የብድሩ ምንጭ የማረት ትርፍ ነው። የማረት ትርፍ የሚመጣው በተጨናበረ መንገድ ነው። ገበሬው ያለፈቃዱና ያለ በቂ ስልጠና ተገድዶ ለማዳበሪያ ለምርጥ ዘርና ለመሳሰሉ የምርት ግብዓቶች እንዲህውም መጤ የግብርና ፓኬጆች ብድር እንዲወስድ ይደረጋል። ማዳበሪያና ምርጥ ዘር እንዲህውም ሌሎች ግብዓቶችን የሚያቀርበው ጉና ነው። ጉና በEFFORT ስር ነው። ጉና ምርቱን ለገበሬ አስገድዶ በመሸጥ ያተርፋል። ገበሬው በራሱ ጥሬ ገንዘብ መግዛት ስለማይችል፥ ብድር ከማረት በከፍተኛ ወለድ እንዲወስድ ይደረጋል። ማረት ሌላ ትርፍ ያጋብሳል። ገበሬው ብድሩን ለመክፈል ፍዳውን ያያል። ብድሩን ለመክፈል የግድ በእርዳታና በምግብ ለስራ ፕሮጀክቶች ስር መታቀፍ መቻል ይኖርበታል። በነዚህ ስር ታቅፎ ተጠቃሚ ለመሆን ደግሞ፣ ለህውሓት ታዛዥነቱንና አሜን ባይነቱን ማረጋገጥ አለበት። ወዘተ።

በዚህ ሁኔታ ነው ገበሬውን ሸብበው የያዙት። በተለይ ትግራይ ውስጥ 85 በመቶ የሚሆነው ህዝብ (ገበሬው) በኛ ቁጥጥር ስር ነው ሲሉ ደጋግመው የሚፎልሉትም በዚህ ምክንያት ነው። ገበሬው መቼም ቢሆን አንገቱን ቀና ማድረግ እንዳይችል የተወሳሰበ አሰራር ዘርግተው አስረውታል። ዛሬ የጎንደር ምሊሻ ገበሬና የኦሮሚያ ገበሬ ለነጻነቱ እንደቆመው ዓይነት ተቃውሞ ከትግራይ ገበሬው ይነሳባቸዋል ብሎ ማሰብ ይከብዳል። ገበሬው ካልተነሳ ደግሞ ሌላው ያን ያክል ስጋት ላይ የሚጥላቸው ባይሆንም ለሱም የሚቀጥለውን መሸበቢያ አሰራር ዘርግተዋል።

 ማሕበር ልምዓት ትግራይ /ማልት/TDA/

ይህ ድርጅት ሲቋቋም በተለይ በዳያስፖራ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች በጦርነት የተዳከመችዋን ትግራይ ተረባርበው እንዲያለሙ እድል ይስጣል በሚል ዓላማ ነበር። ነገር ግን በዚህ መንገድ ለበርካታ ዓመታት ከዳያስፖራ ተጋሩ፣ በውጪ አገራት የትግራይ ወዳጆች እና በአገር ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የሚኖሩ የትግራይ ተወላጅ ባለሃብቶች ከፍተኛ ገንዘብ የተሰበሰበ ቢሆንም መድረሻው ሳይታወቅ እንደተነነና ይህም ጥያቄ አስነስቶ እንደነበር ይታወቃል። በዚህ ምክንያት ድርጅቱ አንዴ እንዲፈርስ፣ ሌላ ጊዜ ተመልሶ እንዲቋቋም ሲደረግ ቆይቷል። ከጅምሩ ዓላማው ፖለቲካዊ እንጂ ልማታዊ ባለመሆኑ፣ አስፈላጊ በሆነበት ጊዜ ሁሉ ዳግም እየመጣ የህዝቡን የልብ ትርታ የሚያዳምጡበት ሁነኛ የፖለቲካ መሳርያ ሆኗል። እንግዲህ የኔ ጥርጣሬ በዚህ ድርጅት የተሰበሰበው ገንዘብ፣ ብዙዎች እንደሚሉት በግለሰቦች ተመዝብሮ ድራሹ ጠፍቷል ሳይሆን ወደ EFFORT ወይም የህውሓት ካዝና ገብቷል የሚል ነው። ይህም ማለት በልማት ስም የሚሰበሰበው የመዋጮ ገንዘብ በራሱ ህውሓትን በማደለብ ጥቅም ላይ የሚውል ነው። የህውሓት የገንዘብ ምንጭ መሆኑ በራሱ የፖለቲካ መሳሪያ ቢሆንም ይህ ቀላሉ ጉዳይ ነው።

ከባለሀብት የተጀመረው ለማልት መዋጮ የመሰብሰብ አሰራር፣ ብኋላ የመንግስት ሰራተኛንና ተማሪውን የሚያሳትፍ እንዲሆን ተደርጓል። ከተማሪም ይሁን ከመንግስት ሰራተኛ የሚሰበሰበው ገንዘብ ያን ያህል የረባ ገንዘብ ባይሆንም በማልት ስም ህውሓት ለሚያቀርብላቸው ጥያቄ ባለሀብቶቹ፣ ሰራተኞቹና ተማሪዎቹ የሚሰጡት ምላሽ አወንታዊ ነው ወይስ አሉታዊ የሚለውን የሚለኩበት የፖለቲካ መሳሪያ ነው። አሉታዊ መልስ የሚሰጡት በርከት ያሉ እንደሆን “ሳይቃጠል በቅጠል” እንዲሉ አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃዎችን ይወስዳሉ። እርምጃዎቹ ግለሰብ ተኮር ቅጣቶች በመሰንዘር ወይም systematic የሆኑ የአሰራር ለውጦችን በመከተል ሊፈጸሙ ይችላሉ። ማልት የህዝቡን የልብ ትርታ እያዳመጡ ከስር ከስር እርምጃ የሚወስዱበት መሳሪያ በመሆኑ ከEFFORT እና ከማረት ቀጥሎ ሶስተኛው የተዋጣለት የፖለቲካ መሳሪያ ነው ማለት ይቻላል።

ከነዚህ ሶስቱ ተቋማት በተጨማሪ እንደማንኛውም ክልል በትግራይ ሌሎች የማፈኛ መንገዶች ስራ ላይ ናቸው። 1ለ5 ጥርነፋ፣ የጸጥታ ሀይሉና መከላከያው በቁጥጥራቸው ስር መሆን፣ የፍትህ ተቋማትና ደህንነት በነሱ ስር መሆን፣ አስገድዶ አባል ማድረግ፣ አባል ላልሆነ ዜጋ የስራ ዕድልና ሌሎች ነገሮችን መከልከል፣ በአንጻሩ ደግሞ አባል ለሆነና ለሚደግፋቸው በተለያዩ መንገዶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ወዘተ በሌላው ክልል እንዳለ ሁሉ በዚህ ክልልም አለ። ለየት የሚለው ከላይ የተጠቀሱት ሶስቱ ተቋማዊ የአፈና መሳሪያዎች ናቸው።

የትግራይ የተለየ ተጠቃሚ

እንግዲህ ከላይ የተዘረዘሩትን የአፈና መሳሪዎች ላነበበ የትግራይ በተለየ ተጠቃሚነት ሊዋጥለት የሚችል አይሆንም። ትግራይ ከሌላው በተለየ ተጠቃሚ አይደለም። እንዳውም በተለየ የታፈነ ህዝብ ነው። ይህ ማለት ግን በተለየ የተጠቀመ ክፍል የለም ማለት አይደለም። በፍጹም። እንዳውም በተገላቢጦሽ በስርዓቱ በተለየ ተጠቃሚ የሆነው ክፍል የወጣው ባብዛኛው ከዚህ ክልል ነው። በቁጥር ጥቂቶች ናቸው ነገር ግን ፍጹም የፖለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነቱን ተቆናጠውቷል። ህውሓት ዓይኑን ጨፍኖ ሊያሞኘን እንደሚሞክረው በኢህአዴግ ስር እንዳሉት እንደ ማንኛውም ድርጅቶች እኩል አይደለም። የተለየ ተጠቃሚምና ፍፁም የፖለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነትን የተቆናጠጠ ብቸኛው ሉአላዊ ፓርቲ ነው።

ፌቀደም ሲል እንደተጠቀሰው ቁልፍ ቁልፍ የመንግስት ቦታዎችን በቁጥጥሩ ስር አድርጓል። ሁሉንም የመንግስት መዋቅሮችና የገቢ ምንጮችን በቁጥጥሩ ስር አውሏል። መከላከያ፣ ደህንነት፣ ፖሊስ፣ ፍርድ ቤት፣ ምርጫ ቦርድ፣ አየር መንገድ፣ አየር ሀይል፣ ጉምሩክ፣ ናሽኛል ባንክ፣ ሚድያ፣ ት/ት ሚንስቴርና ከፍተኛ የት/ት ተቋማት፣ አስመጪና ላኪ ድርጅቶች፣ ግብር ሰብሳቢ ባለስልጣን፣ ቱሪዝም ኢንዱስትሪ፣ የውጭ ምንዛሪ (ጥቁር ገበያ)፣ የመሬት ንግድ፣ የተፈጥሮ ሃብት፣ ገንዘብ አጠባ (money laundary & illicit financing) ወዘተ በህውሓትና በህውሓት ሰዎች ያልተያዘና ከቁጥጥራቸው ውጪ የሆነ አንድም ዘርፍ የለም። ባጭሩ አገሪቱ የግላቸው ንብረት ሆኗለች። ፓርቲውና ከፍተኛ ካድሬዎች የልዩም ልዩ! ተጠቃሚዎች ናቸው። የነዚህ ሰዎች ልዩ ተጠቃሚነትና የበላይነት፣ ከአጠቃላይ የትግራይ (ህዝብ) የበላይነት ጋር ተምታቶ ሲቀርብ ይታያል። ይህ ስህተት ነው። ሊታረም ይገባል።

ማጠቃለያ

ፕ/ር መስፍን እና ሌሎችም ከዚህ በፊት እንዳሉት የመጨረሻው የድህነት ወለል ላይ ያሉት፣ ቤት ንብረታቸውን ጥለው በአዲስአበባና ሌሎች ከተማዎች ጎዳና ላይ ሲለምኑ የሚውሉ የኔ ቢጤዎች በብዛት ከትግራይ የተሰደዱ ናቸው። ይህ ብቻ አይደለም፣ የሚላስ የሚቀመስ የሌለው፣ የህውሓትን ይሁንታና ምጽዋት ሲጠባበቅ የሚኖረው ህዝብ በትግራይ ያለ ማጋነን ከ80 በመቶ በላይ ይሆናል። ምጽዋት የማይጠብቁ የሚባሉት የመንግስት ሰራተኞች ራሱ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ኑሮ ሲኖሩ ይታያሉ። በተዘረጋባቸው የፖለቲካ መሳሪያ አማካኝነት ታፍነው ይኖራሉ። ብሶታቸውን ለመግለጽ ይፈራሉ። እንደምንም ወደ ውጭ ቢወጡ እንኳን፣ ከወጡ ብኋላም ፍርሃቱ አይለቃቸውም። ህውሓትን ይፈራሉ፣ በዘራቸው ምክንያት እንዳያጠቃቸው ሌላውን ይፈራሉ። የአጣብቂኝ ህይወት ውስጥ ይኖራሉ።

በእርግጥ በዛው ልክ ደግሞ ከህውሓት ጋር አሸሸ ገዳሜ የሚሉ፣ በህዝብ ስም የሚነግዱ፣ በህዝብ ስም ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር የሚጋጩ፣ በሌላው ሀዘን ላይ የሚጨፍሩ፣ በሌላው ደስታ ላይ ማቅ የሚለብሱ፣ ሆን ብለው ህዝቡ በሌላ እንዲጠላ የሚሰሩ የህውሓት ገረዶች አሉ። ህውሓት የሚፈልገው ስለሆነ ያሰማራቸው ካድሬዎች ናቸው። በተጠና መንገድ ተግባራዊ እየሆነ ያለ፣ ትግራይንና ትግራዋይን ከሌላው የመነጠል ስራ ነው።

የፖለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነታቸውን በኢትዮጵያ ማስጠበቅ ካልቻሉ፣ ቢያንስ በትግራይ ማስጠበቅ ይኖርብናል ብለው ያስባሉ። ምሽጋቸውን ትግራይ ላይ እየቆፈሩ ነው። ትግራይን ቄጤማ አድርገዋታልና በከፋ ቀን ጉዝጓዛቸው ትሆን ዘንድ በዝግጅት ላይ ነች። የዚህ እንድምታ ለብዙዎቻችን ምናልባት በደንብ አልገባን ይሆን ይሆናል። ምናልባት ሊታወቅ የማይችል ሊሆን ይችላል። ዛሬ ደርሰው የዓፈርንና የሶማሌን ብሄርተኝነት የሚያራግቡት፡ የተቀረውን ኢትዮጵያዊ በዘር ከፋፍለው በማበጣበጥ እነሱ በትግራይ ለመሸሸግ ይመስላል። ምናልባት ሌላው ሲባላ እነሱ ደልቷቸው የሚኖሩ መስሏቸው ሊሆን ይችላል። ፍላጎታቸው ምንም ይሁን ምን ትግራይንና ኢትዮጵያን ከዚህ ድርጅትና ከነዚህ ሰዎች ማስጣል የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሀላፊነትና ግዴታ ሊሆን ይገባል።

በሌላው ክልል እንደምናዬው በአጭር ጊዜ ውስጥ በራሱ ተነሳሽነት የትግራይ ህዝብ በተቃውሞ ይነሳል የሚለው እምነቴ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሸረሸረ መጥቷል። ምክንያቱም ህዝቡ ህውሓትን ይፈራል፣ ሌላውን ወገኑንም ይፈራል። በተቃውሞ ለመነሳት አንዳቸውን መፍራት የግድ ማቆም አለበት። ሌላውን ወገኑን መፍራት እንዲያቆም በሌላው ወገኑ በኩል የአወንታ ምልክቶችና የትግል አጋርነቶችን ማየት አለበት። ህዝቡን ማግለልና ከህውሓት ጋር ደርቦ መፈረጅ ስህተት ስለሆነ ሊታረም ይገባል። ይህ ካልሆነ ግን ሌላውን ወገኑን እየፈራ ህውሓትን ሳይፈራ ለመታገል ይከብደዋል። ምክንያቱም ሌላውን እየፈራ ህውሓትን ሳይፈራ ጭቆና በቃኝ ብሎ ለመነሳት፣ ጠንካራ ትግራዋይነትን (ትግራዋይ ድርጅትን) መፍጠር ይጠበቅበታል። ከህውሓት ብኋላ ህልውናውን ለማስጠበቅ በደንብ መደራጀት እንደሚኖርበት የግድ ማመን ካለበት፣ ያንን ለማሳካት ጊዜ ይፈጃልና በቅርቡ ተቃውሞ ሊያስነሳ አይችልም። ከጊዜው አንጻር የተሻለው አማራጭ ትግራይንም ያካተተ፣ ትግራይን ከህውሓት ነጻ ለመውጣት ጭምር ያለመ ኢትዮጵያዊ ትግል ማካሄድ ነው። ይህን ማድረግ ግድ ይላል።ህውሓት እንደ ድርጅት እስካለ ድረስ የትኛውም የኢትዮጵያ ክፍል በሰላም ሊኖር አይችልምና ህውሓት ከኢትዮጵያ ምድር እስከወዲያኛው ማስወገድ ብቸኛው የማታገያ መንገድ ሊሆን ይገባል።

በመጨረሻ በተለይ ህዝባችን ያለበት ሁኔታ የሚያሳስበን በውጪ የምንኖር የትግራይ ተወላጆች ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ጋር በመተባበር በህውሓት ምክንያት ዜጎች እየደረሰባቸውን ያለ ግፍ በጋር በማውገዘ የትግል አጋርነታችንን በግልፅ ማሳየት አለብን። በትግራይ ያለዉን እውነተኛ ገፅታ ለሌላው ኢትዮጵያዊ ማስረዳት ይጠበቅብናል። የትግራይ ህዝብም ለነፃነቱ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ እንዲቆም ማነሳሳት ይጠበቅብናል። በቃኝ የሚልበትን ጊዜ ለማፋጠን ብዙ መስራት ይጠበቅብናል። በፕ/ር መስፍን የቀረበ የመፍትሔ ሀሳብ በማካፈል ፅሁፌን ላጠናቅቅ።

የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ንግግር በአስመራ በትህደን 2ተኛ ጉባዬ

$
0
0

Enter your email address to follow this blog and receive notifications of new posts by email.

Join 8,285 other followers

ዳግማዊ  ዘመነ መሳፍንት በኢትዮጵያ [ሞት ቡሃላ]

$
0
0

EPRDFበጎንደር መቀመጫውን ያደረገው የማዕከላዊ መንግስት ንጉሰ ነገሰት የነበሩት ዳግማዊ ኢያሱ ባጋጠመቸው ያልተጠበቀ ሞት ምክንያት ልጃቸው ኢዮዋስ (የንግስና ስሙ አዲያም ሰገድ) በ1755 የማዕከላዊ መንግስቱ ንጉሰ ነገስት ሆነው በሰሎሞናዊው ስርዓት መሰረት እንዲሾሙ ምክኒያት ሆኖል፡፡ ይሁን እንጂ ልጅ አዲያም ሰገድ ከየጁ ኦሮሞ በሆኑት አያቱ ምንትዋብ እንደራሴነት እየታገዘ በጎንደር የሚገኘውን የማዕከላዊ መንግስት ማስቀጠል የቻለው እስከ 1969ዓም ለአስራ አራት አመታት ብቻ ነበር፡፡  ምን ተፈጠረ እንደምትሉኝ ተስፋ አደርጋለው፤ የአድያም ሰገድ ልጅ እግርነት እና የአባቱ ሞት ያስከተለውን የአስተዳደር ክፍተት በመጠቀም የትግራዩ ራስ ሚካኤል ስሁል ንጉሰ ነገስቱን  በ1769 በማስገደለል(በድጋሚ) የጎንደር ማዕከላዊ መንግስት ተደማጭነትን ለአንዴና ለመጨረሻ ግዤ እንዲያከትም በማድረግ ለዘመነ መሳፍንት መፈጠር ምክንያት( Immediate factor) ሆነ፡፡ በነገራችን ላይ ራስ ሚካኤል ስሁል እንደሟች መለስ ዜናዊ  አናታቸው መላጣ ነው( መቼስ የዘንድሮ ሰዎች ካላያቹ አታምኑም አይደል?  ፎቷቸውን  ከታች ማየት ትችላላችሁ)፡፡

በመሆኑም በሀገራችን ታሪክ ከ 1769 ዓም እስከ 1855ዓም ያሉት 86 አመታት ዘመነ መሳፍንት (“Age of Princes”) በመባል ይታወቃል፡፡  የዚህ ዘመን ዋነኛ መገለጫ ባህሪው የማዕከላዊ መንግስቱ ተፅኖ መፍጠር ያለመቻሉ(ጥርስ አልባ ውሻ መሆኑ)  እና ሀይ የሚላቸው ያጡ የአካባቢ መሳፍንት የእርስ በእርስ ጦርነቱን ያጧጧፉበት ግዜ መሆኑ ነው፡፡ በተለይ ሀገራችን ከምንግዤው በላይ አንድነቷ የተዳከመበት፣ በየአካባቢው የሚገኙት ገዢዎች እራሳቸውን ችለው የውጭ ግንኙነቶችን በድብቅ የሚያደርጉበት እና ፍትህ የሌለበት ግዜ መሆኑን ብዙ የታሪክ ፀሃፊዎች ይስማማሉ፡፡ በተጨማሪም መሳፍንታቱ በጎንደር በሚገኛው ማዕከላዊ መንግስት የአነሱን ፍላጎት የሚያራምድ ለይስሙላ የሚቀመጥ ንጉሰ ነገሰት ለማንገስ አስከመፋለም የደረሱበት ግዜ መሆኑን ከታሪክ ድርሳናት መመልከት ይቻላል (እንደ አሁኑ ሀይለማርያም(ሀይለ ህወሓት ) መሆኑ ነው፡፡

ወደ ሀገራችን የቅርብ ታሪክ ልመለስና ወታደራዊው የደረግ መነግስት በወደቀ ማግስት ሲጠሩ አቤት እንዲሁም ሲታዘዙ ወዴት የሚሉ እና ብሄርን የሚወክሉ የህዋሃት እንደራሴዎች ተፈጥረዋል፡፡ እኝህ የህወሓት እንደራሴዎችን/ የጭን ገረዶችን በበላይነት ለመምራት አንዲሁም የመጨረሻው ተደማጭ ግለሰብ ለመሆን በሚደረገው ስውር ግብግብ የትግራይ ህዝብ ተወካዮች ነን ባዮቹ በ1983ዓም ለሁለት ተሰንጥቀዋል፡፡ ከህወሓቱ የ1983 መሰንጠቅ የተረፈው አቶ መለስ ዜናዊ (አስተዋዩ መሪያቸው) የትግሉ አጋር የሆኑ ታጋዮችን በመብላት እንዲሁም አልፎ አልፎ ብቅ የሚሉ ስጋት የሚሆኑ የፓርቲ አባላትን ከጫወታ ውጪ በማድረግ ለህዋሃት እንዲሁም ለማዕከላዊ መንግስቱ መዳከም ጉልህ ሚና ተጫውቷል፡፡ አንድ ወዳጄ መለስና የማንችስተሩ ፈርጉሰን ተተኪ(ዘላለማዊ አጥቂ) አላፈሩም እያለ የሚቀልደደው ቀልድ ኪዚህ ጋራ የሚጣጣም ይመስለኛል፡፡ ያልተጠበቀ ሞት መኖሩን ያልተገነዘቡት ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ግለሰባቢ ሀያልነታቸውን አውን ለማድረግ ሙያዊ ብቃት የሌላቸውን እንዲሁም ግለሰባዊ ልዕልና የሚጎድላቸውን ሰዎች በዙሪያቸው በመሰብሰብ ፀሓይ ሆኖ ለመታይት ብዙ ጥረት አድርገዋል፡፡ በዙሪያቸው የሰበሰቧቻውን ግለሰቦች ዘለቄታ ያለው ታዓማኒነትና ታዛዥነት ለማግኘትም መንግስታዊ ሌብነትን እያዩ እንዳላዩ በማለፍ እንደመሳሪያነት ተጠቅመዋል፡፡ እንዲያዉም ሌብነት አስካልተያዝክ (መታዘዝና መታመን እስከቻልክ) ድረስ ስራ መሆኑን በይፋ አውጀዋል፡፡

በመሆኑም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት ቡሃላ ያለው የሀገራችን ሁኔታ ከቀድሞ የዘመነ መሳፍንት ክስተቶች ጋራ የቀረበ ተመሳሳይነት ስላለው ዳግማዊ ዘመነ መሳፍንት ቢዬዋለው፡፡ ለዚህም እንደማሳያነት የሚከተሉት መግለፅ ይቻላል፡-

የመጀመሪያው ሀይለማሪያምን ከፊለፊት በማሰለፍ ሀገሪቷን የሚመራው የማዕከላዊ መንግስት ጊዤ በሄድ ቁጥር ተፅኖ ፈጣሪነቱ እና ህዝባዊ ተደማጭነቱ እየቀነሰ መሄዱ ተጠቃሽ ነው፡፡ ባለፉት አስር ወራት በኦሮሚያ እና በቅርቡ በአማራ ክልል በተከሰተው ህዝባዊ  ቁጣ  በሀይለማሪያም  ፊትአውራሪነት የሚመራው የማዕከላዊ መንግስት ህዝቡን ለማስፈራራት ቢሞክርም  ሰሚ ካለማግኘቱም በላይ ህዝቡ  በሶሻል ሚድያ የሚተላለፉ የትግል ስልቶችን አምኖ በመቀበል ህዝባዋዊ እምቢተኝነቱን አለማቋረጡን ለአብነት ማንሳት ይቻላል፡፡በተጨማሪም የማዕከላዊ መንግስቱ በተለያዩ ጊዚ ያወጣቸውን የፖሊሲ ማዕቀፎች እንዲሁም መንግስታዊ አቋሞች በህዝቡ እንቢተኝነት ለማዘግየት መገደዱ በአንድ በኩል የማስፈፀም አቅሙ መዳከሙን በሌላ በኩል ህዝባዊ አመኔታ ማጣቱን ያመላክታል፡፡  በቅርቡ እንኳ የአዲስ አበባ እና አጎራባች ከተሞች ማስተር ፕላን እንዲሁም የከተማ ታክሲ አሽከርካሪዎች አዋጅን  ይቅርታ በመጠየቅ ማራዘሙና እንዱሁም በወልቃየት ዙሪያ የተነሳውን የማንነት ጥያቄ አስመልክቶ የሚስተዋለውን ወጥነት የጎደለው  የመንግስት አቋም መመልከት ይቻላል፡፡

ዋናዎቹ የኢሐዲግ አባል ድርጅቶች ለይስሙላ የጠቀመጠውን የማዕከላዊ መንግስት ጠቅላይ ሚኒስቴር የሃላፊነት ቦታ ከተቻለ አጠቃሎ ለመያዝ አሊያም ተፅኖ ፈጣሪነታቸውን እውን ለማድረግ የሚያካሂዱት የውስጥ ሴራ ሌላው ከመጀመሪያው ዘመነ መሳፍንት የሚያመሳስለው ክስተት ነው፡፡  ከጠቅላይ ሚኒስተሩ ሞት ቡሃላ ባለችው ሀገራችን ህወሓት በማዕከላዊ መንግስቱ የነበረውን የበላይነት አስጠብቆ መሄድ የታሰነው ሲሆን ዋናዎቹ አባል ድርጅቶች( ኦህዴድ እና  ብአዴን) የታዛዥነት ሚናቸውን አምኖ ላለመቀበል ውስጥ ውስጡን ድብቅ ትግል በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ በተለይ ህወሓት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት ምክንያት ያጣውን ቦታ አሳልፎ ላለመስጠት የታለያዩ  የምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ክላስተሮችን በመፍፀጠር ተፅኖ ፈጣሪነቱን ለማስጠበቅ እንዲሁም ለወደፊቱ መደላድል ለመፍጠር ቢሞክርም መንገዱ ግን አልጋ በአልጋ አልሆነለትም፡፡

ሌላው ከምንጊዜው በበለጠ ሀገራዊ አንድነታችን አደጋ ላይ የወደቀበትና ፍትህ የተጓደለበት ወቅት  መሆኑ ነው፡፡ በአንድ ሀገር የሚኖሩ ህዝቦች ምንም እንኳ የተለያየ ቋንቋ እና ባህል ቢኖራቸው ደስታና ሀዘናቸው የጋራ ነው፡፡ አባቶቻችን ይህንን ሁኔታ አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል ለካ እያሉ ይገሉፁታል፡፡  ይሁን እንጂ ላለፉት አስር ወራት ከ600 መቶ በላይ የሚሆኑ የኦሮሞ ወጣቶች በወገን ጥይት እየተመጡ ሲወድቁ  እንዲሁም በቅርቡ በአማራ ክልልና ኮንሶ እናቶች የወደፊት ተስፋ የሆኑ ልጆቻቸውን ከየመንገዱ እያነሱ ሲቀብሩ አይተን እንዳላየን መሆናችን አልፎም ጠባብና ትምከተኛ እያልን ስም ማውጣታችን ሀገራችን ከምንጊዜውም በላይ ውስጣዊ አንድነቷ መዳከሙን ያሳል፡፡ በተጨማሪም በጋምቤላ የሚኖሩ ንፅህን   ዜጎች በውጭ ወራሪ በጅምል ሲታረዱ እንዲሁም ሴቶቻችን በየ አረብ ሀገራት የሰብአዊ መብታቸው በተደጋጋሚ ሲገፈፍ መመልከታችን እነደ ሀገር ተፅኖ ፈፃሪነታችን አና ክብራችን መጉደፉን  እንዲሁም ፍትህ አለመኖሩን አመላካች ነው፡፡  እንዳንዶቻችሁ እንኳን  የአረብ ሀገራትን ታላቋን አሜሪካ እንኳ ሰሞኑን ሀይለማሪያም ሲያስፈራራ አላየህም እንደማትሉኝ ተስፍ አድረጋለው፡፡ ጅብ በሰው ሀገር ሄዶ ቁርበት አቅርቡልኝ አለ ….አሉ……..ይባላል፡፡

በመጨረሻም የእኔን ጥያቄ አንግባቹህ ሳትመለሱ ከመንገድ ለቀራችሁ ውድ ኢትዮጵያዊን ወንድሞቼ አፈሩ ይቅለላችሁ(Biyyoon isinitti haasalphatu )፡፡ ልጄ በሰላም ወደቤት ተመልሶ ይገባ ይሆን  ብላችሁ ለምትጨነቁ የሀገሬ ወላጆች እንዲሁም ታጋዮች  የኤቢሳ አዶኛን  “ሃቲ ዲራ ሂንቦሲ” የሚለውን ቀስቃሽ ዘፈን (https://www.youtube.com/watch?v=DOmV8RfsQ8k) እየጋበዝኩ ልሰናበታቹህ፡፡ የመፍትሄ ሃሳቡን ይዤ ብቅ እላለው በድጋሚ፡፡

የወይንሸት ልጅ ተወልደ!!!

በየትኛውም አለም ታሪክ ላይ የፈለገ ግዙፍ መንግስት ቢሆንም አንዳቸውም ህዝብን አሸንፍውው አያውቁም

$
0
0

amhara-organizations-satenaw-newsበኢትዮጵያ ፖለቲካ ዉስጥ አንድ አንዶች ያልገባቸውና ሊገባቸው የምያችል ነገር ቢኖር የህዝብን ሀይል ና ፍላጎት አለማክበር ወይም ንቀት ስላለባቸው ብቻ ነው እንጂ አንዳቸውም ለዚህች ሃገር ከልባቸው አስበው አያውቁም ሁሉም እየተነሳ ፓርቲ ገለመሌ ይመሰርታል ትንሽ የሆነ የትምህርት ማእረግ ካለውማ በቃ ካለሱ የሚያውቅ የለም እንደሱ ካላሰብክ ኢትዮጵያ አይደለህም ወይም ወያኔ ነህ ብሎ ይፈርጅሃል።

የተማረ ይግደለኝ የሚል ነገር ከ አማርኛ ጥቅሶች ውስጥ መሰረዝ አለበት!!!
እንደምናየው ይህችን ሃገር ተማርኩኝ ያለው ነው አሁን ያለችበት መዘዝ ዉስጥ ያስገባት በተለይ በተለይ ይሄ ከሃይለሰላሴ በሁአላ ያለው ጀነሬሽን የነ መለስ ዜናዊ, የነ መንግስቱ ,የነ ኢሳያስ ,የነ ሌንጮ ,የነ ስብሃት ነጋ ,የነ ተፈራ ዋልዋ ,ብርሃኑ ነጋ ,ሌንጮ ባቲ ወዘተረፈ ሁሉም የ አንድ ዘመን ሰዎች ሁሉም በ ዮጎራቸው የራሰችውን ፖለቲካ ከ ማርክሲዝም እስከ ካፒታሊዝም ተፈራረቁባት ተማርን ብለው ጭንቅላታቸውን አሳዩን።

ዒትዮጵያ ዉስጥ ስር የሰደደ የፖለቲካ ለውጥ መምጣት አለበት ለዚህ ደሞ ይሄ አጥፊ የሆነ ለስልጣን ብቻ የተጠማ ጀነሬሽን ተቃዋዊም ደጋፊውም ጠቅልሎ ለወጣቱ ትውልድ ማስረከብ አለበት።
ይህን ጥያቄ ጠይቄ የተመለስልኝ “ይህ የኔ ትውልድ ፈሪ እና እሹሩሩ መባል የሚወድ ነው እናንተ ወጣቶች መምራት ከፈለጋቹ መጀምሪያ መመራትን መማር አለባቹ ነበረ መልሳቸው።”
እውነቱን ስናየው ግን እንደዚህ አሁን ያለው ጀነሬሽን የቆሰለ የደማ የለም!!! ገንዘብ ስትፈልጉ መጥታቹ ጀግና ትሉታላቹ ጥያቄ ሲጠይቃቹ የኔ አስተሳሰብ ደሞ ይሄ ነው ሲል ይሰደባል የተለያየ ስም ይሰጠዋል።
አማራ ወጣት ተጎዳሁ ሲል ትምክህተኛ ዘረኛ ይባላል ግን ደሞ በዚሁ ወጣት ደም ተረማምደው ወደ ስልጣን ለመውጣትና የራሳቸውን ህልም እና የግለሰብ ነጻነት ለማሳክት ሲሆን ደሞ ና ዉጣ አንተ ፈሪ ወጣት ይሉታል ከ ባህር ዳር ተቀምጠው። ሃገር ቤት ያለው ሃገር መሪ ነኝ ባዩ ደም ደሃውን ወጣት መልቀም።
እንደው እስቲ ከምር ከልባቸው ህዝቡ አሳዝኖአቸው ቢሆን የህዝቡን ልብ ትርታ ለመስማት እዛው ከህዝቡ አጠገብ ቁመው ልክ ፈሪ እያሉ እንደሚሰድቡት ወጣት ፊት ለፊት የራሳቸውን ሃገር ገዢ ነኝ ባይ የ እድሜ እኩዮቻቸውን አይፋለሙም።
ህዝቡን ወያኔ እንዴት ሃያ አምስት አመት ይገዛሃል ወንድነትክ የት ጠፋ ጀግና አልነበርክ ወይ ይላሉ እውነታው ግን ይሄን የሚሉት ሰዎች የት ነው ያሉት ደም ሲፈስ ብቻ ወጥተው አቃቂ ዘራፍ ማለት በንጋታው ደም የኔ መንገድ ብቻ ነው መንገድ።
**********************************************
በ አማራዎች መካከል ያለውን ልዩነት የሚታየኝ ለኔ የስልጣን ሽኩቻ ብቻ ነውውውውውው። ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም። የናንተ አንድ ግለሰብ ህልም እና ፍላጎት እየሞተ ያለውን ወጣት ደም ይበልጣል ማለት ነው ምን ያህል በ አስተሳሰብ ብትለያዩ ነው ወንድሞቻቹ እዚህ ጋር እየሞቱ እናንተ እኔ ይሄን መስርቼ ገብቼ ወጥቼ ወርጄ ታላልች ሌላው መጥቶ ደሞ በቃ የራሴን እንቅስቃሴ መሰርታለው ብሎ ይነሳል ይሄው 4 ሆነዋል ደሞ።
መቼ ነው የ ሃሳብ ልዩነታችሁን ወደዛ ማለት የምትችሉት መቼ ነው ልታይ ልታይ የሚያስብል የስልጣን ጥማታችሁን ወደዛ ጥላቹ ህዝቡ ምን ይፈልጋል ብላቹ ለህዝቡ አገልጋይ ለመሆን የምትነሱት መቼ ነው ጭቅጭቃቹን ልዩነታቹን ወደዛ ጥላቹ አንድ ለመሆን የምትነሱት።
የ አማራውን ህዝብ ትግል ደሞ የ አምሃራ ህዝብ ትግል በሉት እንጂ የ ጎንደር የ ጎጃም ትግል አትበሉት አማራው አንድ ነው የ አምሃራ ትግል በሉት አትነጣጥሉት። #Amhararesistance
***********************************************
ሌላው ደሞ ለምን ወይም ኢትዮጵያዊ አይደለሁም ኢትዮጵያ ጨቁናኛለች ብሎ ይሄን መንግስት አስቀምጦብን ለ ኢትዮጵያዊያኖች ገና የ መቶ አመት የቤት ስራ ሰተናቸዋል ካለው ጋር ተስማምታቹ ኢትዮጵያን ህዝብ ነጻ ለማውጣት ከሱ ጋር ታብራላቹ ተብላቹ ስትጠየቁ የተመልሰው መልስ አማርጭ ሳይኖራቹ መጥታች ይሄን ጥያቄ አትጠይቁ በሚል ለተሰጠው መልስ የ ጎንደር አማራ ገበሬው አሳያቹ ሌላ አማርጭ።
***********************************************
ወጣቱ ኢትዮጵያዊ መቼም ከዚህ ውዥንብር አይኑን ከፍቶ ይሄን የ አዛውንቶች የጃጃ ያረጀ የገማ ፖለቲካል አይዲኦሎጂ ጀነሬሽንን ወደ አዛውንቶች ጡረታ ቤት አስገብቶ ሃገሩን መረከብ አለበት ይሄ በወጣቱ ደም መንቦጫረቅ ይብቃ ኢትዮጵያ አዲስ ዘመን ወጣትና ብሩህ የሆኑ ልጆችዋን ቦታቸውን ይያዙ።
እኔ መቶ በ መቶ እርግጠኛ ነኝ ከነዚህ ተቃዋዊም ወይም ከገዢ ጎራ ካሉት ሽማግሌዎች ወጣቱ በሚሊዮም እጅ የሚበልጥ ስራ መስራት ይችላል ጊዜውም አሁን ነው ያለበለዚያ ሰዎቹ ገና ቤተመንግስት ነው የምንቀበረው ነው የሚሉት ቀስ እያሉ።
አንድ ቀን ደሞ አምላክ ጊዜው ሲደርስ ይህችን ሃገር በ ሃይማኖትና በዘር የበታተናቹባትን ደሞዝ ይከፍላቹል በየ በሃሩ በየ በረሃው በ የ አረብ አገሩ እየወደቀ ያለው የ ኢትዮጵያዊው ወጣት ደም ይፋረዳቹአል።
በዚህ ጊዜ እንኩአን አንድ መሆን ያልቻላቹ ወጣቶች በተለይ የ አምሃራው ቁጭ ብላቹ ነገረn በደንብ አስቡበት የኔ አስተሳሰብ ሊዩነት እየሞቱ ያሉ ካሉት ወጣቶች ደም ይበልጣል ወይ ብላቹ ራስቹን ጠይቁ ይህችም ጥንጥዬ ስልጣን ተብላ ትንጫጫላቹ እርስ በ እርስ ትጨቃጨቃላቹ በዚህ በኩል ወግንህ እየሞተ አሳፋሪዎች!!!!
እየተቦጫጨቃቹ ወጣቱን አማራጭ ሲያጣ ወደዛ ወደ ሽማግሌዎቹ ነው የሚሄደው ጉልበቱን ብሩን ይዞ ግን እዛ ደሞ ጭንቅላቱ አይፈለግም ጉልበቱና ብሩ ብቻ።

ተጨማሪ መረጃዎች ስለ “ደህንነቱ|” መሥሪያ ቤት [ታደሰ ብሩ]

$
0
0
ዶ/ታደሰ ብሩ
ዶ/ታደሰ ብሩ

“ስለ ‘ደህንነቱ’ መሥሪያ ቤት ከማውቀው በጥቂቱ” በሚለው አጭር መጣጥፍ ላይ በርከት ያሉ የውስጥ መልዕክቶች ደርሰውኛል። በበጎም ይሁን በክፉ የፃፋችሁልኝ ሁሉ አመሰግናለሁ፤ በግልም አመሰግኛቸዋለሁ።

ከተላኩልኝ አስተያየቶች በተለይ አንዱ ትኩረቴን ስቦታል። በውስጡ ተረብ ያለበት ሆኖ “የፃፍከው በአጠቃላይ ጉዳዮች ላይ ነው፤ ‘ከማውቀው በጥቂቱ’ አልክ እንጂ ከአጠቃላይ ጉዳዮች ያለፈ የምታውቀው ዝርዝር ነገር የለም፤ ቢኖርህ ኖሮ ለነገ የምታቆይበት ምክንያት አይኖርህም ነበር፤ ቢያንስ ደጋፊዎችህን ለማስጠንቀቅ ሁለት ሶስት ስሞችን ትጠራ ነበር” የሚል ነው የመልዕክቱ ይዘት ነበር። አስተያየት ሰጪው እልህ ውስጥ ሊያስገናኝ የፈለገ ይመስላል። እኔ በቀላሉ እልህ ውስጥ የምገባ ሰው አይደለሁም፤ ሆኖም ቆም ብዬ እንዳስብበት አደረገኝ።

ስለ ህወሓት መሥሪያ ቤት ተጨማሪ ነገሮችን መናገር ህወሓትን ለማሸነፍና በምትኩ ነፃነት፣ ፍትህ፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ የሰፈባት አገር ለመመሥረት ለምናደርገው ትግል ምን ያህል ይጠቅማል? ተጨማሪ ነገር ብጽፍ በዚህ እኩይ መሥሪያ ቤት ያሉ ቅን ሰዎችን ይጠቅማል ወይስ ይጎዳል? የሚለውን እንዳስብበት አደረኝ። በእኔ ስሌት ከጉዳቱ ጥቅሞ በልጦ ስላገኘሁት እነሆ ተጨማሪ ነገሮች ማለት ፈለግሁ።

ከቁንጮ ልጀምር ፀጋዬ በርሄ – የጠቅላይ ሚ/ሩ የደህንነት አማካሪ ነው። ይህ ሰው ከህወሓት ሹማምንት በደነዝነት ቀዳሚውን ወንበር የያዘ ነው፤ ሆኖ ትልቅ የአዕምሮ ሥራ የሚፈልገውን “የደህንነት አማካሪነት” ሥራ ይዟል። ለኔ ኢንተለጀንስ የአዕምሮ ሥራ ነው፤ የመጀመሪያውና ወሳኙ ጦርነት የስነልቦና ጦርነት ነው፤ ጠላትን በስነልቦና፣ በአዕምሮ ማሸነፍ ይገባል። ፀጋዬ ጭንቅላት የፈጠረበት ስለመሆኑም እንኳን እጠራጠራለሁ።

ጌታቸው አሰፋ: የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል ነው። ይህ ሰው ውስብስብ ነው፤ ባሁኑ ሰዓት ህወሓት ጌታቸውን የሚያህል ሰው ያለው አይመስለኝም። አገራችን የገባችበት አጣብቂኝ የመረዳት አቅም አለው ብዬ አምናለሁ። ሆኖም የህወሓት ልምዱ ውስን አማራጮችን ብቻ እንዲመለከት አድርጎታል ብዬ አስባለሁ። ከህወሓት ውጭ ያለውን ዓለም አያውቀውም፤ ያስፈራዋልም። የህወሓት የቁልቅለት ጉዞ ይታየዋል፤ ግን ስለኢትዮጵያ ቅን የሚያስቡ ሰዎች ከኢህአዴግ ውጭ አሉ ብሎ ለማመን ይቸግረዋል። በዚህ ኃላፊነቱ ላይ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል መሆኑ ምን ያህል እንደጎዳው መገንዘቡን እጠራጠራለሁ።

በጀነራል ዳይሬክተሩ ስር አምስት ምክትል ዳይሬክተሮች አሉ። አምስቱም ቦታዎች የጦርነት ቦታዎች ናቸው። በህወሓት ውስጥ ያለው ሽኩቻ ለማጥናት እነዚህን አምስት ወንበሮች መመልከት ይበቃል። አሁን ህወሓት ውስጥ ሁለት ዋና ዋዋ መስመሮች አሉ፤ አንዱ በሳሞራ የኑስ የሚመራው የመለስ ሌጋሲ አራማጆች [እንብላ፣ እንዝረፍ፣ እንጠቅልል ባዮች] ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በጌታቸው አሰፋ የሚመራ “ተው ረጋ ብለን እናስብ” ባይ ነው። እናም በዚህ ፍትጊያ ሳቢያ አምስቱ ምክትል ዳይሬክተሮች በየጊዜው ይፐወዛሉ። ስለዚህ እነሱን ሳልጠራ ልለፋቸው፤ ገና ያልተረጋጋ ቦታ ነው፤ አንዳንዶቹን ግን ከታች በሌሎች አጋጣሚዎች አነሳቸዋለሁ።

በቀጥታ ወደ ዋና ዋናዎች የህወሓት ሰላዮች እና ምድባቸው አመራለሁ። ከዚህ በታች ስማቸውን የምዘረዝራቸው ሰዎች ሁሉም ማለት ይቻላል እድሜዓቸው ከ 60 በላይ ነው፤ አሁንም ሁሉም ማለት ይቻላል የህወሓት አባላት ናቸው፤ “የኢንተለጀንስ ትምህታቸውን ያጠናቀቁት” በባዶ 6 ንፁሀን ዜጎችን በመግረፍ ነው። ከእነዚህ ውስጥ 70% የሚሆኑት ማንኛውንም ዓይነት ለውጥ ይጠላሉ።

1. ጥበቃ ዋና መምሪያ: መኮንን (ወዲ ኮበል) ይህ የVIP ጥበቃን ጨምሮ አየር መንገድንም ይቆጣጠራል
2. ክንፈ ማሰልጠኛ: ታደለ ፀጋዬ ዳይሬክተር፤ ዶ/ር ሀሽም ተውፊቅ ም/ዳይሬክተርና የአስተዳደርና ፋይናንስ ኃላፊ
3. የቴክኒክ መረጃ: ማዕሾ ( ማዕሾ ከአምስቱ የጌታቸው ምክትሎች አንዱ ነው) የሚመራው ቢሆንም ጌታቸው በቀጥታ ይቆጣጠረዋል
4. የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ዋና መምሪያ: ገ/ዮሃንስ ተክሉ ዋና ዳይሬክተር
5. የውጭ መረጃ ዋና መምሪያ: ሀደራ ( ሀደራው ሌላው ከአምስቱ የጌታቸው ምክሎች አንዱ ነው) ይመራው የነበረ ሲሆን አሁን ገና ቋሚ ሰው አልተተካም። ልዑል ታፈረ ምክትል ነው።
6. የውስጥ ደህንነት ጥበቃ ዋና መምሪያ: አማኑኤል ኪሮስ ዋና ዳይሬክተር ሲሆን ደርበው ደመላሽ ምክትሉ ነው
7. ፀረ ሽብር መምሪያ: ተስፋዬ ዑርጌ ኃላፊ ሲሆን (አግ7፣ ኦነግ፣ አልሸባብ ወዘተ.) ሲሆኑ ምንም እንኳን የራሱ ዋና ክፍል ቢኖረውም አርበኞች ግንቦት-7 ን የመምሪያው ኃላፊ በቀጥታ ይከታተላል።
7.1. የአርበኞች ግንቦት-7 ዋና ክፍል ኃላፊ ሸዊት በላይ ነው [ይህንን ጽሁፍ በመመርመር ጽህፍ እንደሚበዛበት፤ ዛሬ ሰክሮ እንደሚያድር እገምታለሁ]
8. የክትትል መምሪያ ኃላፊ: አፅብሃ ግደይ
9. የፀረ ስለላ መምሪያ ኃላፊ: ነብዩ ዳኘ
10. የኦፕሬሽን መምሪያ ኃላፊ: ቢኒያም ማሙሸት
11. የአስተዳደርና ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ: ፍቅሩ በቀለ
12. የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ክትትል ኃላፊ: አብይ ኃይሉ [እጅግ ከሚያሳዝንኝ ነገሮች አንዱ የዚህ ክፍል ሥራ ነው። ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆችን መማሪያዎች ሳይሆን እስር ቤቶች ያደረጓቸው የዚህ ክፍል ሠራተኛች ናቸው። የዚህ ክፍል ሠራተኞች የሚሠሩት ደባ ለተከታተለ 32 ዩኒቨርስቲ ሳይሆን 32 እስር ቤቶች እንደተገነቡ ይገባዋል]
13. የፖለቲካ ፓርቲዎች ክትትል ዋና ክፍል ኃላፊ: አመለወርቅ ገ/ሃዋሪያ (አቶ)፤ ይስሃቅ ይህደጎ ም/ኃላፊ [ይህ ክፍል ፈቃድ ተሰጧቸው የሚንቀሳቀሱትን ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በጠላትነት ፈርጆ ሊያጠፋቸው ሌት ተቀን ይሠራል]
14. የኢኮኖሚ ደህንነት መምሪያ ኃላፊ: መድህኔ ታደሰ ኃላፊ፤ ፍቃዱ መረሳ ም/ኃላፊ
15. ጥናት መምሪያ ኃላፊ: በላይ አሰፋ ሲሆን አሁን ለምን እንደሆነ ባልገባኝ ሁኔታ እየፈረሰ ያለ መምሪያ ነው
16. የክልሎች ማስተባበሪያ መምሪያ ኃላፊ: ግርማ ተገኝ ሲሆን 9 ን ክልሎችና አዲስ አበባንም ይመራል:: ከእነዚህ መካከል፦
16.1. የአማራ ክልል ኃላፊ: እንግዳው አበባው
16.2. የደቡብ ክልል: እዮብ ተወልደ
16.3. ኦሮሚያ ክልል: አዲሱ በዳዳ ያስተባብራሉ
17. የአዲስ አበባ ደህንነት ዋና ክፍል: ጎሃ አፅብሃ ገ/ሂወት ሲሆን 10ሩን ክ/ከተማዎች ያስተባብራል
17.1. አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ: ጋሻው አበበ ኃላፊ
17.2. ቦሌ ክ/ከተማ ኃላፊ: ምስጋናው አየለ:
17.3. ን/ላፍቶ ክ/ከተማ ኃላፊ: ሲሳይ ገ/ፃዲቅ ኃላፊ
17.4. ልደታ ክ/ከተማ ኃላፊ: አሸናፊ ነጋሽ ኃላፊ
17.5. ኮልፌ ክ/ከተማ ኃላፊ: ሀይሉ ታደሰ ኃላፊ
17.6. ቂርቆስ ክ/ከተማ ኃላፊ የሺጥላ ካሳ ኃላፊ
17.7. አራዳ ክ/ከተማ ኃላፊ: ሀጎስ ሀለፎም ኃላፊ
17.8. የካ ክ/ከተማ ኃላፊ: ክፍሎም በየነ ኃላፊ
17.9. ጉለሌክ /ከተማ ኃላፊ: ሳሙኤል ታፈሰ ኃላፊ
17.10. አዲስ ከተማ ክ/ከተማ ኃላፊ: አዲስ አለነ ናቸው::


የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ንግግር በአስመራ የትህዴን 2ተኛ ጉባዬ

$
0
0

Enter your email address to follow this blog and receive notifications of new posts by email.

Join 8,285 other followers

ፕሮፍ. መስፍን፡- የአማራ ድል የትግሬ እጅ ላይ አይደለም፡ ሆኖም አያውቅም!

$
0
0

ምስጋናው አንዱዓለም (ከዳግማዊ የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት)



mesfin-woldemariam-obama
አሁን በቅርቡ የተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ ለትግራይ ህዝብ ሰጥ ለጥ ብሎ እንዲገዛ እና የትግራይን ከኢትዮጵያም አልፎ ፍጹም የበላይነት ለህዝብ ለማሳመን በወተወቱበት ጽሁፍ ለትግራይ ከመቆርቆር በላይ የሆነ መቆርቆርን አሳዩ፡፡ በእርግጥ ለወገን መቆርቆር ጥሩ ነው፡፡ ግን ለትግራይ ለመቆርቆር በኢትዮጵያ ካባ ውስጥ መደበቅ ሀጢአት ነው፡፡ ይህ ከትግራይ አልፎ ለኤርትራ የተረፈው መቆርቆርዎ አልትራ ትግራይ የማንነት ቀውስ (Ultra Tigray Complex) ልንለው የምንችለውን ባህርይ የተላበሱ መሆንዎትን ያሳያል፡፡

በጽሁፍዎ ውስጥ ደብረ ቢዘን ገዳምን እንደትልቅ ምሳሌ በማውሳት ለኤርትራ ያለዎትን አድልዖ ይገልፃሉ፡፡ አላማዎ ይሄ ኤርትራዊ ገዳም የኢትዮጵያ ማለትም በእስዎ አመለካከት የትግራይ ዋና ማእከል (Vital value) እንደሆነ ማሳየት ነው፡፡ ያው እነ አቦይ ስብሀት የአማራ ብለው አከርካሪውን ለመስበር የሚዶልቱትን የኦሮቶዶክስ ክርስትና በደብረ ቢዘን ሰበብ ለትግራይ የበላይነት ማረጋገጫ ሊጠቀሙበት አስበው ይመስላል፡፡ ሀይማኖትን ለድብቅ የፖለቲካ አላማ በማዋልም ከእነ አቦይ ስብሀት ረቀቅ ያለ ዘዴ መከተልዎን ያመለክታል፡፡

ግን በአማራ መናንያን ልብ ዘንድ ደብረ ቢዘን ገዳም ያን ያህል ቦታ ኖሮት አያውቅም፡፡ የአቡነ ሐራን፣ የአቡነ ተክለ ኃይማኖትን፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባን፣ ሀይቅ እስጢፋኖስን፣ የክርስቶስ ሠምራን፣ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን፣ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስን እና የኤዎስጣቴዎስን ገድላት እናውቃለን፡፡ ዋና ዋናዎቹ የታሪክ አውዶችም ዋልድባ (ዋሊ ዱባ) ገዳም [ገዳመ ዋሊያ]፣ ሐይቅ እስጢፋኖስ፣ ዋካት ሚካኤልና አውካ አምባ፣ ግሸን ደብረ ከርቤ፣ ወንቅሸት ገብርኤል፣ ደብረ ሊባኖስ፣ ጣራገዳም ማርያም፣ ጎንድ ተክለ ኀይማኖት፣ ላሊበላ፣ ምድረ ከብድና ዝቋላ፣ እና የጣና ሀይቅ ገዳማት ናቸው፡፡ ስለሆነም እርስዎ ሊሰብኩን እንደሚሞክሩት ደብረ ቢዘን ገዳም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሕይወት ውስጥ የጎላ ሚና የለውም፡፡ በመካከለኛው ዘመን በነበረው የፖለቲካ ትግልም ሚና አልነበረውም፡፡ ገዳም ከመሆኑ በቀር እና አፄ ምኒልክ ከጣልያን ጋር ሲዋዋሉ በኢትዮጵያ ይዞታነት እንዲቆይ ከመደረጉ በቀር፡፡ እርስዎ ግን ደብረ ቢዘን ገዳምን ይኸን ያህል የሚያንቆለጳጵሱት እና የተለየ እንደሆነ የሚሰብኩበት ምክንያት የእርስዎን የትግራይ ብሔረተኛነት ያመለክት እንደሁ እንጅ ከትግራዩ ደብረ ዳሞ እንኳ ያነሰ ታሪክና ዝና ነው ያለው፡፡ በእርግጥ ይሄ ያለቅጥ ለትግራይና ኤርትራ ያደረው አገላለጽ የትግራይ ትግርኝ ግዛት ህልምን እንድናስታውስ ያደርገናል፡፡ እናም ደብረ ቢዘን ከ70 ሺህ በላይ ከሆኑት የኢትዮጵያ አብያተ ክርሥቲያናት ተነጥሎ እንዳለ አንድ ገዳም ሊታይ ካልሆነ በቀር እርስዎ እንደሚደሰኩሩት በሁለቱ አገሮችም ሆነ በእርስዎ ትግራይ ፖለቲካዊና ታሪካዊ ሕይወት ውስጥ እምብዛም ሚና ይኖረዋል የሚል ግምት የለም፤ ከተዋረሱት የገዳምን ስም እየጠሩ በመገዘት ያልሆነን ነገር እንደትልቅ ጉዳይ ለማስቆጠር ከመንደፋደፍዎ በስተቀር፡፡

እናም በዚህ ጽሑፍዎ ከገዳሙም ከምኑም በመዝገን ትግራይ ከኢትዮጵያ እንደምትበልጥ አፅንዖት ሰጥተው ፅፈዋል፡፡ አማራው ወይም መላው ኢትዮጵያዊ የሰራውን አገራዊ ታሪክም ለወገንዎ ትግሬ ሸልመዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከትግራይ የምታንስ መሆኗን የትግሬ ካድሬዎች እንጅ በፕሮፌሰርነት የሚንቀሳቀስ ሰው ሲናገር ለመጀመሪያ ጊዜ መስማታችን ነው፡፡ ይሁንልዎ፤ ምኞት አይከለከል፡፡ ትግራይን ለማሳበጥ አማራን ማጉበጥ ግን ተገቢ አልነበረም፡፡ የታሪክ ሽሚያውን በይደር እናቆየውና ወደሌላው ነገርዎ እንሂድ፡፡

ጽሁፍዎን በትግራይ ጀምረው በትግራይ እስኪደመድሙ ድረስ አማራ ላለማለት ግን ከባድ ትግል ገጥመው ይታያል፡፡ ኦሮሞን ኦሮሞ እንዲሁም ትግሬን ትግሬ ይሉና አማራ ላይ ሲደርሱ ጎንደርና ወሎ ይላሉ፤ ሊያውም እጅግ በተደጋጋሚ፤ ለፌቸሪንግም (ለአስመስሎ-ማጀቢያ) አፋርን ያስገባሉ፡፡ በጣም ተንኮለኛ ስለሆኑ ለወደፊቱ አማራ የድሮ ግዛቱን ሲያስከብር አፋርም በአማራ መጠቃለሉን ስለሚያውቁ ልክ ጎንደር፣ ወሎና አፋር እያሉ እየለያዩ አፅንዖት ሰጥተው ይፅፋሉ፡፡ ሚስጥሩ ግን አብዛኛው አፋር በወሎ ራስ ገዝ አስተዳደር ስር ስለነበር፤ በሌላ አነጋገር ወሎ ስለነበር ትግሬና አማራ ቢለያዩ አማራ የአፋርን የግዛት ይገባኛል ጥያቄ ሊያነሳ ስለሚችል ቀድሜ እሳቤውን ልዝጋው ብለው የሚጥሩ ይመስላል፡፡ ይህንን የምንልበት ምክንያት ትግሬ ከተቀረው ኢትዮጵያ ሊነጠል እንደሚችል ደጋግመው እዚህ ጽሁፍዎ ላይ ስላሰፈሩ እና የትግሬ መነጠልም የማይቀር ከሆነ አፋርን ከአማራ ይዞታነት በመነጠል የትግሬ መከራከሪያ ግዛት ለማድረግ ማሰብዎን ያሳብቃል፡፡ አቤት ተንኮል! ትግሬና ኢትዮጵያ ቢለያዩ ኢትዮጵያ ከስታ ትግራይ እንትን ሆና መኖር ይችላሉ ብሎ ያሰበው አዕምሮዎ የአፋርን ጉዳይ በደንብ አላጤነበትም ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው፡፡

ከላይ ያለው አንቀጽ እውነትነት አስረጂ ለአማራ የነበረዎ ጥላቻ እና አሁንም እዚሁ ጽሑፍዎ ላይ ያንፀባረቁት ክህደትዎ ነው፡፡ “አማራ የለም” የሚል አደንዛዥ አስተሳሰብ በማራመድ ሽበትዎን እና የሰምዎን ክብደት በመጠቀም ልሂቃንን በአማራነት እንዳይነጋገሩና በአማራነት እንዳይደራጁ አድርገው ቆዩ፡፡ ይህንን አስተሳሰብዎን በአማራ ልሂቃን ዘንድ ለማስረፅ የቻሉበትን ሁኔታ ስናስብ ይገርመናል፡፡ ነገር ግን ደህናዎቹ የአማራ ልሂቃን በኢሀፓና ደርግ ስም እርስ በእርስ ተዋግተው ስላለቁ የቀሩት ፈሪዎችና ልፍስፍሶች በመሆናቸው ነው በእርስዎ ውኃ የማይቋጥር ሐሳብ እንደበግ የተነዱት የሚል መልስ እናገኝና እንፅናናለን፡፡ ለዚህ አባባል እውነትነት የእርስዎ ስራ ህያው ምስክር ነው፡፡ እንጠቅሳለን፡-

ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር አማራን በተመለከተ ያደረጉት አገር የሚያውቀው ውይይት አለ፡፡ ቪዲዮው ላይ ጠያቂው ‹‹ ‹ሌላው ብሔር ሁሉ ተወካይ ሲኖረው አማራው የለውም› የሚሉ አሉ›› ስለዚህ ጉዳይ የሚሉትን ይጠይቃቸዋል፡፡

እርሳቸውም ‹‹እሄ አማራ ሚባል ነገር…ነገር መነገርና መነጋገር ያለብን…መነጋገር ያለብን ጉዳይ ይመስለኛል፡፡ ውክልና? ለውክልና አስቸጋሪ ነው፡፡ የሌለ ነገር መወከል አይቻልም፡፡ የለም! አማራ እሚባል ነገር! [በንዴት ከንፈራቸውና ድምጻቸው ይንቀጠቀጣል] እኔ እንደማውቀው ጎጃሜ አለ፤ ዳሞቴ አለ፤…ጎንደሬ አለ፤…ሰሜን አለ፤…አርማጭሆ፤…ወልቃይት ጸገዴ አለ፤…ሸዋም እንኳ ትንሸዋ ጋ ስንመጣ መንዝ፣ ቡልጋ፣ ተጉለት፣ ምንጃር፣…ምናምን ተብሎ ይበጣጠሳል፡፡ አማራ ሚባል ነገር እወክላለሁ ብሎ እዛ ኮንፈረንስ ላይ ቢኖር ኖሮ እኔ ወይ አብዷል ያ ሰውዬ…ወይ አንድ ችግር ያለበት ሰውዬ መስሎ ነው የሚታየኝ፡፡ በምንም አይነት መንገድ የሌለን ነገር አንድ ሰው መወከል አይችልም! የለም፡፡››

የዚህ ስብሰባ ዓላማ ዋና መልዕክት የአማራ መኖር አለመኖር አልነበረም፡፡ ‹‹አማራ የለም›› በሚለው ሰም ውስጥ ታሽጎ እንዲተላለፍ የተፈለገው ‹‹ወርቅ›› መልዕክት ሆነ ተብሎ ሌላ አላማ ያለመ ነበር፡፡ አማራ ውክልና እንዳያገኝ ርዕዮተ ዓለማዊ ድጋፍ ለመስጠት ታቅዶበት የተሰናዳ ውይይት ነበር፡፡ እነ መለስ አማራ እንዲወከል አይፈልጉም፡፡ ለምን አማራ አልተወከለም ተብለው ለሚጠየቁት ጥያቄ መልስ ማለትም ማደናገሪያ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ለዛም ፕሮፍ. መስፍንን አቅርበው አማራ ስለሌለ መወከል የለበትም እንዲባል አደረጉ፡፡ ስለዚህ የአማራ አለመወከል ትክክለኝነትን በምሁራዊ ‹‹ትንታኔ›› አስረገጡ ማለት ነው፡፡

ዋናው ቁም ነገር ግን አማራ ተብሎ ይወከል አይወከል ብቻ የሚባለው አይደለም፡፡ በወያኔ ትርጓሜ አማራ የተባሉ ወሎ፣ ጎጃም፣ ሸዋና ጎንደር ውክልና አልነበራቸውም፡፡ ወይም እነሱን የሚወክል ኃይል አልነበረም፡፡ ኦሮሞ፣ ትግሬ፣ ሀድያና፣ ሲዳማ ተወካይ ነበራቸው፡፡ በአማራ ግዛቶች የነበረው ሕዝብ ግን ተወካይ አልነበረውም፡፡ ስለዚህ አማራ የሚባል ስለሌለ ወኪል አያስፈልገውም ማለት አራቱ የአማራ ግዛቶች በወያኔ የሞግዚት ሥር እንዲተዳደሩ ያመቻቸ ውይይት ነበር፡፡ በዚህ ውይይት ላይ መለስ አማራ አለ ይላል፡፡ ያንን የሚልበት ምክንያት የአማራ ወኪል ብሎ የራሱን ሰዎች በብአዴንነት ስላዋቀረ ያ ድርጊት ተቀባይነት እንዳያጣ ነው፡፡ በተጨማሪም አማራ አለ በማለት የይስሙላ የአማራ ጉዳይ የሚያሳስበው ለመምሰል ይጥራል፡፡ የአማራውን ነገር ከይስሙላ በዘለለ በወኪልነት እንደማያሳትፈው የሚያስረዳው ንግግር ከዚህ ጋር አያይዞ የሚፈራውን ነገር የሚገልጽበት ክፍል ነው፡፡ ፕሮፍ. መስፍን ‹‹አሁን አማራ ውጭ አገር እየተፈጠረ ነው… ያ እንዳይጋባብን ያሰጋል›› ሲሉ መለስ ቀበል አድርጎ ይሄ ጉዳይ እንደሚያስፈራው ይናገራል፡፡ አማራነቱ ሳይሆን አመለካከቱ ነው በማለት ለማደነጋገር ሲሞክርም ይታያል፡፡ ከዚህ ፍርሀትና ሴራ አዘል ንግግሩ አማራን አማራ እና የአማራ አመለካከት ብሎ ለሁለት ይከፍለዋል፡፡ ስለዚህ አማራ የሚለው ራሱ የወከላቸውን አማራ ያልሆኑ ሰዎች እና በጊዜው አማራም ሆነው ንቃተ ህሊናቸው ዝቅተኛ የነበሩትን ነው፡፡ ትክክለኛውን አማራነት ግን የአማራ አመለካከት በማለት ሲፈራውና ሲሸሸው ይታያል፡፡ ይህንንም በኋላ እነ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን በመግደል በተግባር ለትክክለኛው አማራ ያለውን ጥላቻና ፍርሀት ገልጽዋል፡፡

ባጭሩ የውይይቱ ዓላማ በእንደዚህ ዓይነት የማደናገሪያ ጭምብል የተለወሰ አማራን አግላይ ፖሊሲ ለማራመድ ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ ሲጀመር ውይይቱ ስለውክልና ሁኔታ ሆኖ ሳለ ወደ አለና የለም ክርክር መገባት አልነበረበትም፡፡ አማራም ተባለ ወይም ጎንደሬ፤ ወሎዬም ሆነ ጎጃሜ አልያም ሸዌ የሆነ ሕዝብ በአገሪቱ ፖለቲካዊ ሥርዓት ውስጥ ውክልና ስለተነፈገ የግድ መወከል ነበረበት፡፡ አለቀ፡፡ ይሄ የአራት ክፍለ ሀገር ህዝብ ውክልና አያስፈልገውም ብሎ ያለ ተከራካሪ እና ተቆርቋሪ እንዲቀር ማድረግ ያው ዋናውን የወያኔ ፀረ-አማራ ፖሊሲ ከማጠናከር የዘለለ ትርጓሜ አይሰጠውም፡፡ በዚህ ንግግር ላይ መለስ አማራን እወክላለሁ ብሎ የመጣ የአማራ ድርጅት የለም ይላል፡፡ ድርጅት ስለሌለው አይወከልም የሚባል ነገር አይሰራም፡፡ በዛ ጊዜ በአራቱ ግዛቶች የሚኖር ሕዝብ አለመወከል ማለት ትልቅ ክፍተት ነው፡፡ የአገሪቱን ለግማሽ አይነፈሪ ሕዝብ አውላላ ሜዳ ላይ የሚጥል ሥርዓት በምንም መመዘኛ ትክክለኛ ሥርዓት አይሆንም፡፡ በዚያ ጊዜ ተወካይ ባይኖር እንኳ ወዲያው ተወካይ እንዲኖር የሚደረግበት አግባብ መሰራት ነበረበት፡፡ ነገር ግን ያ እንዲሆን አይፈለግም፡፡ የዚህ ውይይት ዓላማም ከዚህ በፊት የአማራ ተወካይ አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ እንዳይኖር ርዕዮተዓለማዊ ገደብ መጣል ነበር፡፡ ‹‹የሌለ ነገር በምንም ተዓምር አይወከልም›› የሚለው የፕሮፍ. ንግግር ለወደፊቱ ማሰሪያ ነው፡፡ እንኪያስ ፕሮፍ. አንድ ጥያቄ መጠየቅ አለብዎ፡፡ ይህ የአራት ክፍለ ሀገር ሕዝብ እርስዎ እንደሚሉት አማራ በሚል የወል መገለጫ መጠራት የለበትም ማለትዎን ብንቀበል እና እንዲህ ብንጠይቅዎ፡- በአራቱ ክፍለ ሀገር ውስጥ የሚኖረው ሕዝብስ እንደሕዝብ፣ እንደደሰው፣ ሰው አልነበረም? መብት፡ ውክልና፣ ጥብቅና… አያስፈልገውም? አማራ ማለት ቢከብድዎ እንኳ ለምንድነው የወሎ፣ የጎጃም፣ የጎንደርና የሸዋ ሕዝብም (ሰውም) መወከል አለበት ብለው ያልተከራከሩት? ምክንያቱም እርስዎ በብሄር ሳይሆን በሰው ሰውነት እንደሚያምኑ ይናገራሉና የዚህ አራት ክፍለ ሀገር ህዝብ አማራ መሆን ባይችል እንኳ ሰው መሆን እና መወከል አልነበረበትም!? መልሱን ለራስዎ ይመልሱት፡፡ እኛ እናውቀዋለን፡፡

እግረ መንገዳችንን ይህችን አማራ ‹‹የለም›› የምትል ሀሳዊ ሀይማኖትዎን እንዳስስ፡፡ ስልጣን፡ ባህልና አገዛዝ በሚለው መጽሐፍዎ ላይ እኔ አማራ የለም ስለዚህ ዜሮ ነው እላለሁ፡፡ ሌላው ደግሞ አማራ አለ ይላል፡፡ ስለዚህ አለ የሚል አንድ ነው ብሎ ያሳምነኝ፡፡ እኔ ግን አማራ ዜሮ ነው እላለሁ፡፡ ስለዚህ ዜሮ የሆነ ነገር የለም፡ ስለዚህ ትክክል ነኝ ይላሉ፡፡ ለዚህም ጥናት ማድረግዎን ይገልጣሉ፡፡ ጥናት አድርጌ ስለሚሉም ጽሑፍዎ ከተራ ወግ በዘለለ መልኩ እንዲታይ ይሆናል ማለት ነው፡፡ እንግዲህ አንድ ምሁር ጥናት ሲያደርግ ጥናት የሚያደርግበት ምክንያቶች ይኖሩታል፡፡ ለእውቀት ማለትም ለግል ስሜት እርካታ እና ለችግር መፍትሔ ብሎ ሊያጠና ይችላል፡፡ እርስዎ ደጋግመው እንደሚናገሩት አማራን አጠናሁ የሚሉት ለእውቀት ወይም የአማራ መኖር እና አለመኖር ጉዳይ ልዩ ፍላጎት አሳድሮብዎት አይመስልም፡፡ ከመለስ ጋር ስለአማራ ሲነጋገሩ ጥናትዎ ለተጨባጭ ችግር ተግባራዊ መፍትሔ የሚሻ ነው የሚሆነው እንጅ እንዲሁ ለእውቀት ተብሎ አይደለም፡፡ ስለሆነም የእርስዎ ጥናት የአማራ መኖር ወይም አለመኖር የጥናት አጀንዳ ሆኖ ስላገኙት ጥናት አካሄዱ ብለን እንድናስብ እንገደዳለን፡፡ የዚያ ጥናትዎን ውጤትም መሰረት በማድረግ ለእነመለስ የመፍትሔ ሀሳብ እያቀረቡ ነበር፡፡ መፍትሔውም ‹‹አማራ የሚባል ‹ስለሌለ›፣ አለመኖሩንም በጥናቴ ስላረጋገጥኩ ባትወክሉትም ችግር የለውም›› እያሉ ማረጋገጫ እየሰጡ ነበር፡፡

ከዚህ ተነስተን ነው እንግዲህ ወደዋናው ጥያቄ የምንሄደው፡፡ እርስዎ አንድን ሕዝብ በማኅበራዊ ሳይንስ የጥናት ዘዴ መኖር እና አለመኖር ለማረጋገጥ ጥናት ያካሄዱ የመጀመሪያው ሰው ሊሆኑ ነው፡፡ በማንኛውም የብሔር ማንነት መለኪያ በአራቱ ክፍለ ሀገራት የሚኖረው ሕዝብ አማራ እንደሆነ ሀቅ ነው፡፡ ወደዝርዝሩ አልገባበትም፡፡ ከዚህ በፊት ጽፌልዎት አውቃለሁ (መለክ ሐራ በሚል አካውንቴ፡፡ ያ ጽሑፉ አሁንም እዚህ ልጥፍ ጋር ተያይዟል–ዘሀበሻ ያተመው)፡፡ ስለሆነም አማራ አለና የለም ብለው ጥናት ለማድረግ ሲነሱ የጥናትዎ አላማ ስህተት ነበር ማለት ነው፡፡ የሕዝብን መኖር እና አለመኖር የማሕበራዊ ሳይንስ የጥናት ዘዴን ተከትሎ ስለማይደረግ፣ ተደርጎም ስለማያውቅ፡፡ ስለዚህ የጥናት አጀንዳዎ ከመጀመሪያው ውድቅ እና አላስፈላጊ ነው ማለት ነው፡፡ በዚያ ላይ ሕዝብ በ‹‹አለ››ና ‹‹የለም›› (0 እና 1) ባይናሪ አመክንዮ አይገለፅም፡፡ ያ ሕዝብ ‹‹አለ›› ወይም ‹‹የለም›› ተብሎም ጥያቄ አይቀርብም፡፡ ከቀረበም ከተራ ካድሬ እንጅ ከፕሮፌሰር አይቀርብም፡፡ ምናልባት ‹‹በአራቱ ክፍለ ሀገራት መካከል እንዴት ያለ አንጻራዊ የአማራነት ስሜት አለ›› የሚል ጥያቄ አንስተው ቢሆን ኖሮ የፕሮፌሰር ጥያቄ እንለው ነበር፡፡ (ዛሬ ባጋጣሚ አንድን ህዝብ አለና የለም ብሎ መደምደም ይቻላልን ብየ ፕሮፌሰሬን ጠይቄያት ነበር፡፡ Such an idea is not only a sign of methodological fallacy but also a huge disorientation of research objective which signals scholastic lameness ነው ያለችኝ፡፡)

ዳሩ ግን ስለማያውቁ ነው ማለት ያስቸግራል፡፡ ቢያንስ ይሄ የአማራ ጉዳይ ቀላል ጥያቄ ስለሆነ ለእርስዎ አይከብድም፡፡ ራስዎ ከወያኔ መምጣት በፊት በጻፏቸው ጽሑፎች አማራ እያሉ ሲጽፉ የኖሩ ሰው በመሆንዎ አማራ አለና የለም በሚል አጀንዳ ላይ መዘፈቅ የሆነ ተንኮል ካላሰቡ በቀር ከባድ ሆኖብዎት ነው ለማለት ያስቸግራል፡፡ ወያኔ ሲገባ እግር ጠብቀው ስሙን እየጠሩ ሲፅፉለት የነበረውን አማራ ጭራሽ የለም ሲሉት ለሚያይ ብዙ ጥርጣሬዎችን በእርስዎ ላይ እንዲያነሳ ይገደዳል፡፡ ይሄ ስውር ዓላማዎም ነው እንግዲህ (እንደምንጠረጥረው) ከመለስ ጋር ጉባኤ ያዳበለዎ፡፡ እነመለስ ለምን እርስዎን ማናገር አስፈለጋቸው የሚለው ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሳ ትልቅ ጥያቄ ነው፡፡ ያ ንግግር ለሚዲያ ፍጆታ መዋሉም መቸም የወያኔን ስውር ሴራ የሚያራምድ ስለመሆኑ እንድንጠረጥር ያደርጋል፡፡ ስለዚህ ወደውም ሆነ ተሸውደው የወያኔ ፀረ-አማራ ፖለሲን ድጋፍ አድርገውለታል ማለት ነው፡፡ ይህችን ወረድ ብለን እንያት፡፡

እርስዎ ራሰዎ ወያኔ በጠብመንጃ እንደመጣ ሲፅፉና ሲናገሩ ነበር፡፡ በጠብ መንጃ የመጣ ኃይል ደግሞ በጠብ መንጃ ብቻ እንደሚወርድ አይስቱትም፡፡ በአመፅ ስልጣን የያዘ እንደወያኔ ዓይነት ፋሽስት ኃይል ምናልባት ስልጣን ለሕዝብ ሊያስረክብ ይችላል ብለው አስበው ሊሆን ይችላል ብለን ብናስብ እንኳ ነገሩ አያስኬድም፡፡ ለምን ቢባል ወያኔ በድብቅ ሳይሆን በግልፅ፤ በትግርኛ ሳይሆን በአማርኛ በጠብ መንጃ ብቻ እንደሚወርድ ተናግሯል፡፡ ከ97 በኋላ ፕሮፍ. ብርሀኑ ነጋ እንደጻፈውም መለስ ቃል በቃል ይኸንኑ ነግሯችኋል፡፡ እርስዎ ግን ከዛም ወዲህ እስካሁኑ ሰዓት ድረስ የአማራ ልጆችን በአማራ የለምነት አስተሳሰብ እያጠመቁ ሰላማዊ ታጋዮች በሚል እያሰባሰቡ ለወያኔ አሳልፎ መስጠቱን ቀጠሉበት፡፡ የእርስዎን ሐሳብ በማራመድ ወይም በእርስዎ ድጋፍ በመበረታታት ብዙ የአማራ ልጆች በእስርና በሞት ይንገላታሉ፡፡ ወያኔ ሰላማዊ ትግልን አማራን ለማደን እንደሚጠቀምበት እያወቁ እርስዎ ያንን ዓላማ ወደውም ሆነ ሳያውቁት ለወያኔ በሚያግዝ መልኩ ሲያራምዱ ቆዩ፡፡ በጠብመንጃ ብቻ ነው ስልጣን የምለቀው ያለን ኃይል እንዴት ሰው በጤናው በሰላም እታገለዋለሁ ይላል! በሰላም ታግየ የወያኔን ጸባይ አቀይራለሁ ብሎ ማሰብ መቸም ቀበሮ የበግ ላት ይወድቃል ብላ ስትከተል ዋለች ከተባለው ያነሰ አስተውሎት መሆኑን ይስቱታል ተብሎ አይጠረጠርም፡፡ በዚህ እርስዎ በማይጠፉበት የሰላማዊ ትግል ሰበብም የትየለሌ የአማራ ልጆች በወያኔ ተበሉ፡፡ እርስዎና ሌሎች በኢትዮጵያዊነት ስም ይሰበስቧቸዋል፤ ወያኔ በአማራነት ይበላቸዋል፡፡

እና አሁን ሰሞኑን በፃፉት ጉዳይ ብዙ እርስዎን ለትዝብት የሚጥሉ ነገሮች አስፍረዋል፡፡ ጽሑፉ ሲጨመቅ መላው ኢትዮጵያ በትግሬ እጅ ብቻ መሆኑን እና ያለትግሬ ፈቃድ ወይም ትብብር ለውጥ እንደማይመጣ ሕዝቡ እንዲያምን የተፈለገ ነው የሚመስለው፡፡ ሕዝቡ ወያኔን ከመታገል ትግራይን ወደመማጠን እንዲያዘነብል የሚወተውት ጽሑፍ ነው፡፡ እንግዲህ የሥነልቡና ጦርነት ዘርፍም ሊሆን ይችላል፡፡ እንደ አማራ ሆነን ስናስበው ደግሞ አማራ በአማራነቱ መነሳቱ ብቻውን ለብዙ አማራ ነክ እና ከዛ ወዲያ ያሉ ጥያቄዎች መልስ ነው፡፡ ማንም ብሄርም ሆነ ሀይል ለራሱ ሲል ብቻ ከአማራ ጋር የግድ ተስማምቶ መኖር እንደሚገባው ጠፍቶዎት አይደለም፡፡ ምናልባት እየተነሳሳ ያለውን እና ድል ማድረጉም አይቀሬ የሆነውን የአማራነት እንቅስቃሴ ጠልተውና ፈርተውት በትግሬ የስነልቡና የበላይነት ስር ሊያንበረክኩት እየሻቱ ካልሆነ በቀር፡፡

በነገራችን ላይ በዚህ ጽሁፍዎ ላይ ትግራይ እና ኦሮሚያ የሚሉ ቃላትን ተጠቅመዋል፡፡ ወደዝርዝሩ አንገባም፡፡ ነገር ግን በአንድ አገር ውስጥ ሌሎች የአገር ስሞችን እውቅና መስጠት በራሱ በአገሩ አንድነት አለማመንን ነው የሚያመለክተው፡፡ እንደሚያውቁት ትግራይ የህዝብ ስም ሳይሆን የአገር ስም ነው፡፡ ኦሮሚያም እንደዛው፡፡ ይሄንን የወያኔ አጀንዳ ሳቅማሙ ተቀብለው ንግግርዎን በዛ መዋጀትዎ ለኢትዮጵያ አንድነት ያለዎትን ልባዊ ቀናኤነት… የሆነ ነገር ያደርገዋል፡፡ ያው ከራስዎ ቃል ነው፡፡ ከአያያዝ ይቀደዳል፡ ከአነጋገር ይፈረዳል ይባል የለ፡፡ ለዛ ነው፡፡ ይሁንና ትግራይን እና ኦሮሚያን በአገርነት ተቀብለው ሲያበቁ አማራ ላለማለት ብርቱ ትግል ያደርጋሉ፡፡

እንግዲህ ያው መቸም በፕሮፌሰር አፍ ስለተነገረ ብለን እንጅ ብዙው ስለአማራ የሚያራምዱት ሀሳብ ውሀ አይቋጥርም፡፡ ውሀ የሚቋጥር ነገር የሚያነሱ ቢሆን ኖሮ ሙያዊ ትንተና እና ግምገማ እንሰጥ ነበር፡፡ እርስዎ ወይም ደቀመዛሙርቶችዎ ሀሳብ የሚያንጸባርቁ ከሆነ ግን በእርስዎ ስራዎች ላይ ሰፋ አድርገን ሙያዊ ትንተና ይዘን እንደምንመለስ ቃል እንገባለን፡፡ ላነሱት ሀሳብ ግን ይሄ በቂ መልስ ነው ብለን እናምናን፡፡ Good for the price እንደሚሉት፡፡

ምስጋናው አንዱዓለም (ከዳግማዊ የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት)
አማራ ያሸንፋል!

ተቀምጠው የሰቀሉት ….[በዳንኤል ክብረት]

$
0
0

daniel-kibret.jpg satenawየኢራቅ ኩርዶች እንዲህ ይተርካሉ፤

አንዲት የልዑል ልጅ ነበረች፡፡ አንድ የምታፈቅረው ልጅም ነበረ፡፡ ታድያ ከአንድ የቤተ መንግሥቱ ጠባቂ ጋር ትመካከርና ይህንን ፍቅረኛዋን ክፍሏ ድረስ ታስገባው ነበር፡፡ የቤተ መንግሥቱ ጥበቃ የተወሰነ ገንዘብና ልብስ ትሰጠው ስለነበር በደስታ ምሥጢሩን ይደብቅ ነበር፡፡ አንድ ቀን ግን ያልታሰበ ነገር ተከሰተ፡፡ ልዕልቲቱና ፍቅረኛዋ አፕል ቆርጠው እየተጫወቱ ይበሉ ነበር፡፡ ሁለቱም አፋቸውን ከፍተው የአፕሉን ቁራጭ አንዳቸው ወደሌላቸው አፍ ወርውሮ የማስገባት ጨዋታ ነበር የሚጫወቱት፡፡

እየተሳሳቁ የአፕል ቁራጭ ወደየአፎቻቸው ሲወረውሩ ልዕልቲቱ የወረወረችው የአፕል ቁራጭ ድንገት የፍቅረኛዋ ጉሮሮ ውስጥ ተቀረቀረ፡፡ ውኃ ብትሰጠው፣ ማጅራቱን ብትመታው ሊወርድለት አልቻለም፡፡ ኡኡ ብላ እንዳትጮህ ልጁ ማነው? እንዴትስ መጣ ? ለሚለው ጥያቄ የምትመልሰው የላትም፡፡ በዚህ መካከል ልጁ ትንፋሽ አጥሮት ሞተ፡፡

የልጁ የመውጫ ሰዓት ሲደርስ የጥበቃ ሠራተኛው መጣ፡፡ እንደቀድሞው ግን ልጁን ደብቆ ሊያስወጣው አይችልም፡፡ አሁን ያለው ሬሳው ነው፡፡ ‹እባክህን የምትችለውን ሁሉ አድርገህ ይህንን ሬሳ አውጣልኝ፤ የምትፈልገውን ነገር ሁሉ አደርግልሃለው› አለቺው፡፡ የጥበቃ ሠራተኛውም ‹ምንም ችግር የለውም፤ የምፈልገው ግን ገንዘብ ወይም ልብስ አይደለም› አላት፡፡ እርሷም ‹ምንም ችግር የለም፡፡ ብቻ በቶሎ አውጣልኝ› ብላ ለመነችው፡፡ የጥበቃ ሠራተኛው ሬሳውን ቆሻሻ አስመስሎ ደብቆ አወጣው፡፡ እርሷም እፎይ አለች፡፡

የጥበቃ ሠራተኛው ተመልሶ መጣና ቃል በገባችው መሠረት የሚፈልገውን ነገር እንድታደርግለት ጠየቃት፡፡ ‹ምን?› አለች ልዕልቲቱ፡፡ ‹ካንቺ ጋር መተኛት ነው የምፈልገው› አላት፡፡ ፀሐይ እንደበዛባት ቅል ክው አለች፡፡ ተናደደች፡፡ ‹ምን ደፋር ነህ ከልዕልት ጋር ለመተኛት የምታስብ፤ አሁን ከዚህ ጥፋ› አለቺው፡፡ እሺ ብሎ ወጣና የፍቅረኛዋን አስከሬን ይዞላት መጣ፡፡ ይኼኔ የምታደርገው ግራ ገባት፡፡ ያላት አማራጭ የሰውዬውን ፈቃድ ማሟላት ብቻ ሆነ፡፡ ተሸነፈች፡፡ በአንድ ቀንም ሦስት ነገሮችን አጣች፡፡ ፍቅረኛዋን፣ ክብሯንና የወደፊት ተስፋዋን፡፡ ፍቅረኛዋን በሞት፤ ክብሯንም በአገልጋይዋ እግር ሥር በመውደቅ፤ የወደፊቱንም ተስፋዋን ድንግልናዋን በማጣት፡፡

በዚህ ብቻ አላበቃችም፡፡ ያ የጥበቃ ሠራተኛ እየመጣ ‹አጋልጥሻለሁ› ይላታል፡፡ ያን ቀን ሬሳውን ይዞ የመጣበትን ጆንያም ያሳያታል፡፡ እርሷም ትፈራለች፡፡ በፍርሃትም የማትፈልገው ሰው እግር ሥር ትወድቃለች፡፡ ከእርሱም ጋር ትተኛለች፡፡ ይህ ግን ሊያዛልቃት አልቻለም፡፡ ባርነት ሰለቻት፡፡ ችግሮችን ለመጋፈጥ ካልፈለግህ ችግሮችን እያነገሥካቸው ትሄዳለህ› ይላሉ ኩርዶች፡፡ ችግርን ካታለልከው መልሶ ይይዝሃል፤ ከተጋፈጥከው ግን ጥሎህ ይሸሻል የሚል አባባልም አላቸው፡፡

ልዕልቲቱ አሁንም ችግሩን መፍታት ሳይሆን ማምለጥ ፈለገች፡፡ አንድ ሌሊት የጥበቃ ሠራተኛው ተደብቆ ወደእርሷ ሲመጣ ለአባቷ የምታዘጋጀውን የልዑሉን ወይን አሰናድታ ጠበቀቺው፡፡ በደስታ እየደጋገመ ጠጣ፡፡ ከእርሷም ጋር ከተኛ በኋላ እንደ ተሸነፈ ቦክሰኛ በድካም ተዘረረ፡፡ አርሷም እየጎተተች ወስዳ በልዑሉ መኝታ በር ላይ አጋደመችው፡፡ ሊነጋጋ ሲል ጠባቂዎቹ አዩት፡፡ ጠጋ ብለው ሲያሸቱት አፉ የወይን ጠጅ ይሸታል፡፡ የወይን ጠጁ ሽታ የልዑሉ ወይን መሆኑን ይመሰክራል፡፡ የልዑሉን ወይን ሰርቆ ጠጥቷል ብለው በአደባባይ ሰቅለው ገደሉት፡፡ ነገሩም በዚህ የተቋጨ መሰለ፡፡ ነገር ግን የዕብድ ቀን አይመሽም፡፡ ኩርዶች እንዲህ ይላሉ፡፡ የምትሠራው በር ምንጊዜም ልትሄድበት የምትችል መሆኑን አረጋግጥ፡፡ ለአንድ ጊዜ መውጫ ብለህ በሩን ከሠራኸው ከበሩ በኋላ ወዴት እንደምትሄድ ግራ ይገባሃል፡፡ በሩን ከነ መንገዱ አስበው፡፡ መንገዱን ከነ መዳረሻው፤ መዳረሻውንም ከነመቆያው፤ መቆያውን ከነ መክረሚያው፡፡

የጥበቃው ሠራተኛ በአደባባይ ሲሰቀል፤ የወይኑ ጣዕም አፉ ላይ ቀርቶ ስለነበር እየደጋገመ ከንፈሩን ይልስ ነበር፡፡ የዚህ ምክንያቱ የጠጣው የወይን ጠጅ ጣዕም ነው ተብሎ ተወራ፡፡ ይህንን ወሬ የሰማ የሌላ ልዑል ልጅም ይህንን ወይን ያዘጋጀቺውን የልዑሉን ልጅ ለማግባት ፈለገ፡፡ እናም ወደ ልዕልቲቱ አባት ሽማግሌዎች ላከ፡፡

ይህ ዜና ለአባቷ የምሥራች ለልዕልቲቱ ግን መርዶ ነበር፡፡ ድንግልናዋን አጥታለች፡፡ በኩርድ ደግሞ ድንግል ያልሆነቺውን ልጅ እንኳን ልዑላን ተራዎቹ ሰዎች አያገቡም፡፡ እስካሁን ችግሩን ከመጋፈጥ እየሸሸች፣ ነገር ግን አንዱን ችግር በሌላ ችግር እያለፈች መጥታለች፡፡ አሁን የመጋፈጫው ሰዓት ደረሰ፡፡ ችግርን በመፍትሔ መፍታትና ችግርን በሌላ ችግር ማለፍ ይለያያሉ፡፡ ችግርን በችግር ካለፍከፈው ጊዜ እየገዛህ ነው፡፡ ችግርን በመፍትሔ ካለፍከው ደግሞ ልብ እየገዛህ ነው፡፡ ይላሉ ኩርዶች፡፡

የልዕልቲቱ አባት ጋብቻውን መቀበሉን ስትሰማ እንደተለመደው ልዕልቲቱ አንድ ዘዴ ቀየሰች፡፡ አንዱን ታማኝ አገልጋይዋን ጠራችውና አንድ እፍኝ ወርቅ ሰጥታ እንዲህ ስትል አዘዘችው ‹በመላዋ ኢራቅ ዙር፡፡ በመልክም፣ በቁመትም፣ በጠባይም እኔን የምትመስል ልጅ ፈልገህ ለደንገጡርነት አምጣልኝ›፡፡ ሰውዬውም ለወራት ያህል ከቦታ ወደ ቦታ ዞረ፡፡ በመጨረሻም አንዲት ልጅ አገኘ፡፡ ልዕልቲቱ ስታያት ቁርጥ እርሷን ትመስላለች፡፡ እንዲህ አለቻት ልጅቱን፡፡ አሁን አንቺ ልዕልት ሆነሻል አሉ፡፡ የልዑሉንም ልጅ ታገቢያለሽ፡፡ የጫጉላውንም ጊዜ አብረሽው ታሳልፊያለሽ፡፡ እኔም ያንቺ ደንገጡር ሆኜ አንቺንና ልዑሉን ለጊዜው እታዘዛለሁ፡፡ ልክ የጫጉላው ጊዜ እንዳለፈ ግን ትቀይሪኛለሽ፡፤ እንቺ ወደ ደንገጡርነትሽ እኔም ወደ እመቤትነቴ እመለሳለሁ፡፡ ለዚህ ውለታሽም ለጥሎሽ የሚመጣውን ሀብት ሁሉ ትወስጃለሽ› አለቻት፡፡ ልጂቱም በደስታ ተፍነከነከች፡፡

የሠርጉ ቀን ደረሰ፡፡ ደንገጡሯዋ የሙሽራ ልብስ ለበሰች፡፡ እመቤቲቱ ደግሞ የአገልጋይ ልብስ ለበሰች፡፡ ማንም ሊለያቸው የቻለ የለም፡፡ ልዑሉ መጣ፡፡ ሙሽራዋን ይዞ ሄደ፡፡ አገልጋይዋም ተከትላ ሄደች፡፡ በልዑሉ ቤት የነበረው ድግስ ሲያልቅ ልዑሉና ሙሽራዋ ወደ ጫጉላ ቤት ገቡ፡፡ አገልጋይዋም ከውጭ ቀረች፡፡ ታስበዋለች፡፡ ይህ ዕድል የእርሷ ነበር፡፡ ነገር ግን አሁን አይደለም፡፡ አሁን እርሷ ነበረች እዚያ ውስጥ መሆን የነበረባት፤ ግን ችግርን ለማለፍ ብላ በፈጠረችው ችግር ምክንያት ውጭ ቆማለች፡፡ እዚህ ደረጃ ሳትደርስ ነገሮችን አስተካክላ በክብር ልትወጣ ትችል የነበረባቸውን ዕድሎች ታስታውሳለች፡፡ ዕድሎች ሁሉ አምልጠዋታል፡፡ ችግሮችን በሌላ ችግር በመተካት ዕድሎችን አምክናቸዋለች፡፡ ስለዚህም ክብሯን ለሌላዋ አሳልፋ ሰጠቻት፡፡ ሕዝቡ ጫጉላ ቤት ያለቺው እርሷ መስላቸዋለች፡፡ ግን አይደለችም፡፡ የተመረጠችው እርሷ፣ ወደ ሠገነት የወጣችው ሌላዋ፡፡ የተዳረችው እርሷ፣ ያገባችው ሌላዋ፡፡

የጫጉላዎቹ ቀናት አለፉ፡፡ ልጂቱ ግን ወደ አገልጋይነቷ ልትመለስ አልቻለችም፡፡ አንድ ቀን መታጠቢያ ቤት ውስጥ እመቤትና ደንገጡር ተገናኙ፡፡ ደንገጡሯም ‹አሁን በቃሽ ወደቦታሽ ተመለሽ፡፡ ለውለታሽ ያዘጋጀሁትን ስጦታሽን ውሰጅ; አለቻት፡፡ እመቤቲቱም ‹የዋሕ ነሽ፡፡ ላየው የማልችለውን አሳየሺኝ፤ ላገኘው የማልችለውን ሰጠሽኝ፤ ልደርስበት የማልችለው ቦታ አደረሽኝ፡፡ ያኔ እሺ ስልሽ ይህንን ሁሉ አላውቅም ነበር፡፡ አልጋው እንዲህ የሚመች መሆኑን አልቀመስኩም ነበር፡፡ ክብሩ እንዲህ የሚያጓጓ መሆኑን አላውቅም ነበር፡፡ ምቾቱ እንዲህ ልብ የሚለሰልብ መሆኑን አላውቅም ነበር፡፡ ላንቺ ከደንገጡርነት ወደ እመቤትነት መምጣት ቀላል ይሆናል፡፡ ለእኔ ግን ከእመቤትነት ወደ ደንገጡርነት መውረድ ከባድ ነው፡፡ ይህንን የመሰለ ነገር ከቀመስኩ በኋላ ትተውልኛለች ብለሽ ማሰብሽ ሞኝነትሽ ነው፡፡ አልጋ አንዲህ በቀላሉ የሚተው አይደለም፡፡ ሀብቱ ሁሉ የእኔ መሆኑን እያየሁ ያንቺ ስጦታ የሚያጓጓኝ ይመስልሻል› አለቻት፡፡

“እነሆ” ይላሉ ኩርዶች፡፡ እነሆ በዚህ የተነሣ አገልጋይቱ እመቤት፣ እመቤቲቱም አገልጋይ ሆነው ኖሩ፡፡ ተቀምጣ የሰቀለቺውን ቆማ ማውረድ አቅቷት፡፡

ኤድመንተን፣ ካናዳ

በተለያዩ የዩናይትድ ስቴትስ ከተማ የሚገኙ የኦሮሞ ማኅበረሰብ አባላት በዋናነት ያዘጋጁት የተቃውሞ ሰልፍ ዛሬ በዋሽንግተን ዲስ ውስጥ ተካሂዷል

$
0
0

VOA

ዋሽንግተን — በዚህ ሰልፍ ላይ የተለያዩ የኢትዮጵያ ማኅበረሰቦች፣ የሲቪል ማኅበራት አደራጆችና የመብትና የፖለቲካ እንቅስቃሴ መሪነት እንዲሁም ከተለያዩ ከተሞች የመጡ ተሳታፊዎች የተገኙበት ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል።

የሰልፉ ዋና አላማ የኢትዮጵያ መንግስት በዜጎች ላይ ያደርሰዋል ያሉትን የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ ግድያና እስራት እንዲያቆምና ለዚህ ደግሞ የፕሬዝዳንት ኦባማ አስተዳደር ግፊት እንዲያደርግ የሚጠይቅ ነው። የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት የሚያደርገው የገንዘብ ድጋፍ ዜጎችን ለመግደል እንዳያገለግል ቁጥጥር መደረግ እንዳለበት የሚጠይቅ ጭምር መሆኑን አስተባባሪዎቹ ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

if(typeof(jQuery)==”function”){(function($){$.fn.fitVids=function(){}})(jQuery)};jwplayer(‘jwplayer-1’).setup({“image”:”http://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2016/09/14494807_10209492420440173_5797269669738954424_n.jpg”,”file”:”http://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2016/09/VOA_u12e8u12a2u1275u12eeu1335u12ebu1295-u1218u1295u130du1225u1275-u12e8u121au1243u12c8u121d-u1364u12e8u12a0u121cu122au12abu1295-u1218u1295u130du1225u1275-u12f5u130bu134d-u12e8u121au1320u12edu1245-u1230u120du134d-u1260u12cbu123du1295u130du1270u1295-u1270u12abu1204u12f0_u133du12eeu1295-u130du122du121b_Sept-29-2016.mp3″});

3fb299b6-1c1a-4d8a-b5b3-68d878bfd9d2_w987_r1_s

14494807_10209492420440173_5797269669738954424_n

ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች የማዕረግ ዕድገት ተሰጣቸው ተባለ [ኢሳት]

$
0
0
14457389_1190615007652169_1773971420469769088_nከ30 የሚበልጡ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ሃሙስ የሌተናል፣ የሜጀርና፣ የብርጋዴር ጀነራልነት ማዕረግ እንደተሰጣቸው መንግስት አስታወቀ።
በሃገሪቱ ፕሬዜዳንት ሙላቱ ተሾመ የማዕረግ እድገት ተሰጥቷቸዋል ከተባሉት ወታደራዊ መኮንኖች መካከል የሜጀር ጄነራልነት ማዕረግ የነበራቸው ገብራት አየለ ቢጫ በብቸኝነት የሌተናል ጀኔራልነት ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል።
በብርጋዴር ጀነራልነት ሲያገለግሉ ነበር የተባሉ 12 ወታደራዊ መኮንኖች ደግሞ የሜጀር ጀኔራልነት ሹመትን ያገኙ ሲሆን፣ 25 ኮሎኔሎች እንዲሁ የብርጋዴር ጄኔራልነት ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል።
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሞት ተከትሎ መንግስት ለከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ሹመትን ሲሰጥ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የዛሬውን ጨምሮ ከ120 የሚበልጡ ወታደራዊ መኮንኖች መሾማቸውን ለመረዳት ተችሏል።
ሃሙስ በሜጀር ጄኔራልነት ከተሾሙት መካከል ብርጋዴር ጄኔራል መሃመድ ኢሻ ዘይኑ ትኩዕ፣ ብርጋዴር፣ ጄኔራል ሃለፎም እጅጉ ሞገስ፣ ብርጋዴር ጄነራል ማሾ በየነ ደስታ፣ ብርጋዴር ጄኔራል ጥጋቡ ይልማ ይገኙበታል።
በብርጋዴርል ጀአራልነት ከተሾሙት መካከል ደግሞ ኮሎኔል አዲሱ ገብረየሱስ ገብረዮሃንስ፣ ኮሎኔል ኪዱ አለሙ አሰጉ፣ ኮሎኔል ብርሃኑ ጥላሁን በርሄ፣ ኮሎኔል ግርማ ክበበው ቱፋ፣ እና ኮሎኔል ተክላይ ኪዳኔ ተድላ በቅድመ ተከትል ከተቀመቱት መካከል መሆናቸው ተመልክቷል።

ESAT Radio 30 min Sep 29 2016

esat-satenaw-news

Viewing all 2265 articles
Browse latest View live