Quantcast
Channel: Amharic News – Medrek
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2265

ፍትሕ ለወ/ሮ እማዋይሽ እና በእስር ላይ ለሚገኙ የፖለቲካ እስረኛ ሴቶች! (ይድነቃቸው ከበደ)

$
0
0

3291ቀናትን ያለ ምንም ወንጀል በእስር ላይ 🙁 እማዋይሽ አለሙ አንቺ የሁላችንም እናት ነሽ!!!

የሴቶች እኩልነት እና የላቀ ተሳትፎ ለማረጋገጥ ተግቼ እሰራለው የሚለው የህወሃት/የኢህአዴግ መንግስት ላለፉት 26 ዓመታት የገባውን ቃል ኪዳን ወደ ጎን አድርጎ፤ ለሰብዓዊ መብት መከበረ እንዲሁም ዴሞክራሲ ስርዓት በአገራችን እንዲያብብ የበኩላቸውን አሰተዋአዖኦ ለማድረግ ደፋ ቀና የሚሉ ሴቶችን በተለያየ መንግድ ጫና በመፍጠር፣ በአገራቸው ጉዳይ ቀጥተኛ ተሳታፊ እንዳይሆን አለኝ የሚለውን አማራጭ ሁሉ እየተከተለ ይገኛል።ገዢው መንግስት ሴቶች በአገራቸው ጉዳይ መንግስትን በመቃወማቸው እና በመተቸታቸው ብቻ የሚደርሳባቸውን
በደል አስመልክቶ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ፣ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ እና የዴሞክራሲ መብት ተሟጋቾች ፣ እንዲሁም የአለማችን ታላላቅና ለጋሽ ሀገራት ጠንካራ ወቀሳ በገዢው መንግሥት ላይ እያቀረቡ ይገኛሉ።

የሚቀርበው ወቀሳ በምክንያት እና በእውነት ላይ የተመሰረተ ስለ መሆኑ እጅግ በጣም ብዙ ገላጭ የሆኑ ምሳሌዎችን ማቅረብ ይቻላል። እያንዳንዱ ነገር መዘርዝር ለቀባሪው መርዶ እንደማርዳት ስለ-ሚሆን እንደ ማሳያ ይህን ብቻ ማንሳት በቂ ነው ። በአገራችን ከ1983 ዓ.ም የመንግስት ለውጥ በኋል ለመጀመርያ ጊዜ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ መሪውን በሰለጠነ ሰላማዊ መንገድ የመረጠው በ1997 ዓ.ም ነው። የዛሬ 12 ዓመት ሕዝብ ከመረጣቸው መካከል ተዋቂነት ያተረፈችው ወ/ሪ ብርቱ ‘ካን’ ሚደቅሳ አንዷ ናት! ወ/ት ብርቱ ‘ካን’ በሃገሯ ጉዳይ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን የበኩላን አሰተዋአዖኦ ለማድረግ ያደረገችው ጥረት በህወሃት/የኢህአዴግ መንግስት በጎ ምላሽ ሊሰጠው አላቻለም። ይባስ ብሎ ለተደጋጋሚ እስር እና እንግልት እንዲሁም ስቃይ ተዳረገች። በዚህም ምክንያት ከፍተኛ የሆነ የስነ- ልቦና ቶርቸር ተፈጸመባት፣ በመጨረሻ ሰው ናትና አሁን ላይ የሆነው ሆነ። ይህም በመሆኑ ማንም በእሷ ቅር አልተሰኘም! የኢትዮጵያ ሕዝብ ባለውለታውን የሚያከብር ጥንቁቅ ሕዝብ ነው። ተወዳጁ አንጋፉው አርቲስት ደበበ እሸቱ ብርቱካንን የሚጠራት ብርቱ ‘ካን’ እያለ ነው!ለዚህም ነው እሷን በቅርበት የምናውቃት ብርቱ ‘ካን’ የምንለው ።የስሟ አጠራር እንዴት እና መቼ የእሷ መጠሪያ እንደሆነ ወደፊት እመለስበታለው።

የብርቱ ‘ካን’ ከአገር መሰደድ እና። ፖለቲካውን በቃኝ በማለቷ በህወሃት/የኢህአዴግ ሰፈር ከፍተኛ ፈንጠዝያ ለጊዜው ቢያስገኝም ፣ ብርቱ ‘ካን’ ያሰለፈችው የመከራ ጊዜ እንዲሁ ዝም ብሎ የባከነ አልነበረም !ብዙ ብርቱ ‘ካን’ ያፈራ በሃገራችን ከ1983 በኋል እጅግ በጣም ትንታግ የሆኑ ሴቶች ! የሰብዓዊ እና የዲሞክራሲ መብት ተሟጋቾች እና አራማጆች የተገኙበት ወርቃማ ዘመን ነው። ነገሩን ይበልጥ አስገራሚ የሚያደርገው ህወሃት/ኢህአዴግ አዲስ አበባ ገብቶ ስልጣን በያዘ ማግስት የተወለዱ “የኢህአዴግ ዘመን ልጆች” የዚሁ አካል መሆናቸው ነው።እነሱም ቅድሚያ የዜጎች ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲ መብት በማለት በፊት መስመር ተሰልፈው ለሃገራቸዉ እና ለሕዝባቸው የቻሉትን ያህል በጎ አሰተዋአዖኦ ለማበርከት ከመንገድ ላይ ናቸው።ሆኖም ግን እነኚህ የመብት ተሟጋች እና አራማጆች መንገዳቸው ቀና አልነበረም ፣ እንደተለመደው እስሩ፣ስቃዩ እና እንግልቱ ከእነሱ አልተለየም ።በአሁኑ ጊዜ ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ እህቶቻችን የዚህ በደል እና ስቃይ አካል ናቸዉ ።

ከእነዚህም መካከል በእስር ላይ የሚገኙት የአራት ልጆች እናት ወ/ሮ እማዋይሽ አለሙ አንዷ ናቸዉ ። ሚያዝያ 16 ቀን 2001 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤቷ ተይዛ ለእስር የተዳረገቸው ወ/ሮ እማዋይሽ፣ ሕገመንግስቱን በሃይል ለመናድ በህቡዕ ሰርተዋል በሚል በእነ ብ/ጄ ተፈራ ማሞ መዝገብ የተከሰሱ ብቸኛዋ ሴት ናቸው። 25 ዓመት እስር የተፈረደባቸው ወ/ሮ እማዋይሽ አለሙ ዛሬም በቃሊቲ እስር ቤት ይገኛሉ።እኚህ እናት ለዘጠኝ ዓመት በእስር ቤት የመከራ ጊዜ እያሳለፉ ናቸዉ ። አዎ ! ፍትህ ለእማዋይሽ ዓለሙ ! እና በእስር ላይ ለሚገኙ የፖለቲካ እስረኛ ሴቶች በሙሉ ! ወ/ሮ እማዋይሽ ዓለሙ እና በተለያየ እስር ቤት የሚገኙ የሰብዓዊ እና የዴሞክራሲ መብት ተሟጋች እና አራማጆች ፣በአገራችን ኢትዮጵያ ሴቶች የበኩላቸውን አሰተዋአዖኦ ለማድረግ የሚጠሩ ተምሳሌቶች ናቸው ። ይህም በመሆኑ እነዚህ እህቶቻችን እጅግ በጣም ሊወደዱ እና ሊከበር የሚገባቸው ፣ ብርቅዬ የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው። የዘመናችን ጣይቱዎች ናቸዉ ! ስለነርሱ አውንም ሁሌም ድምፃችንን ከፍ አድርገን በህብረት ፍትሕ…ፍትሕ… ፍትሕ… ፍትሕ…ፍትሕ በማለት እንጠይቃለን!!!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!

 

The post ፍትሕ ለወ/ሮ እማዋይሽ እና በእስር ላይ ለሚገኙ የፖለቲካ እስረኛ ሴቶች! (ይድነቃቸው ከበደ) appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News | Breaking News: Your right to know!.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2265

Trending Articles