Quantcast
Channel: Amharic News – Medrek
Viewing all articles
Browse latest Browse all 2265

የኦሮሞ-ሶማሊ አብሮነት መድረክ – የአቋም መግለጫ

$
0
0

መጋቢት 7፣ 2009 ዓ.ም

ከህዳር ወር 2009 ዓ.ም. ጀምሮ ማለትም ላለፉት አምስት ወራት በሶማሊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዚደንት የሚታዘዘው ገዳዩ የልዩ ፖሊስ ኃይል አዋሳኝ የኦሮሚያ አካባቢዎችን በመውረር ብዛት ያላቸው ንፁሀንን በመግደልና በማፈናቀል ላይ እንዳለ ይታወቃል። ጥቃቱ እየተፈፀመ ያለው በአምስት የኦሮሚያ ዞኖችና በ14 አዋሳኝ ወረዳዎች ላይ ነው። በተለያዩ ዘገባዎችና የአይን እማኞች መሰረት እስካሁን ቢያንስ 200 ንፁሀን ተገድለዋል ብዙ ቁጥር ያላቸው ቆስለዋል። ገዢው የህወሓት ቡድን ጥቃቱን በሁለቱ ወንድማማችና እህትማማች የሶማሊና የኦሮሞ ህዝቦች መካከል የተነሳ የድንበር ውዝግብ አድርጎ ለማቅረብ ቢሞክርም፣ እውነታው ግን ከኦሮሚያ የተነሳበትን ህዝባዊ ተቃውሞ ለማዳከም የጠነሰሰው ሴራ መሆኑ ምንም አያጠራጥርም። በሁለቱ ክልሎች መሀከል ያለው ድንበር እ.ኤ.አ. በ2005/6 ህዝበ-ውሳኔ የተሰጠበት መሆኑ ይታወቃል።

ሁለቱ ተጎራባች የሶማሊና የኦሮሞ ህዝቦች ለብዙ ክፍለ ዘመናት በሰላም አብረው የኖሩና የሚፈጠሩ አለመስማማቶችን በመወያየት የሚፈቱበት ባህል ያላቸው ናቸው። የህወሓት መሰሪ ሴራም በሁለቱ ህዝቦች ላይ እየፈፀመ ካለው ወንጀል ተጠያቂነት የሚያድነው አይደለም።
ልዩ ፖሊስ በመባል የሚታወቀው ቅጥረኛ ቡድን ንፁሀንን ማጥቃት የጀመረው በኦሮሚያ ክልል አይደለም፣ ይልቁንም ላለፉት አስር አመታት በህወሓት ቀጥተኛ ትእዛዝ የሶማሊ ክልል ህዝብን ሲያሸብር የኖረ ቡድን ነው። በርካታ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን፤ ግድያን፣ አስገድዶ መድፈርን፣ መንደሮችን ማቃጠልና የመሳሰሉትን ሲፈፅም ቆይቷል።

እናም የኦሮሞ-ሶማሊ አብሮነት መድረክ እነዚህን ህወሓት መራሽ በህዝቦቻችን ላይ የሚፈፀሙ የጭካኔ ተግባራትን እያወገዝን፣ ወንድምና እህት የሆነው የኦሮሞና የሶማሊ ህዝብ በጋራ እንዲቆም ጥሪ እናቀርባለን። እየተፈፀመ ያለው ጥቃት ህወሓት በእጅ አዙር በኦሮሞ ህዝብ ላይ የከፈተው ጦርነት እንጂ በፍፁም በኦሮሞና በሶማሊ ህዝብ መካከል የተፈጠረ ግጭት አይደለም።

በጋራ ሆነን የህወሓትን የ26 አመታት ጭቆና እንመክታለን!
ድል ለኦሮሞና ለሶማሊ ህዝቦች!

ከጥልቅ አክብሮት ጋር!

የኦሮሞ-ሶማሊ አብሮነት መድረክ ተወካዮች:-

ገረሱ ቱፋ
መሀመድ ሀሰን
ነጃት ሃምዛ
ናጌሳ ኦዶ ዱቤ
ጀማል ዲሪዬ ካሊፍ
ጀዋር መሀመድ
አብዱላሂ ሁሴን
ደሀብ መ. አብደላ
ጥበቡ ስሜ
ሀዲ ሉቅማን
ግርማ ጉተማ
ሰለሞን ኡንጋሼ
ፀጋዬ አራርሳ
ጋዲሳ አብራሂም
ኤደኦ ዳወኖ
ለቱ ቡሻን
አማን ማልዴዎ
እንድሪስ ነገዎ

The post የኦሮሞ-ሶማሊ አብሮነት መድረክ – የአቋም መግለጫ appeared first on ሳተናው: Ethiopian Amharic News 24/7- Your right to know!.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 2265

Latest Images

Trending Articles



Latest Images